ከዛሬ 25 ዓመታት በፊት በነበረችው ኢትዮጵያ ሐገርነቷ የዜጎቿ የራሳቸው ሐብት ስለነበረች ዜጎች በየትኛውም የሀገሪቱ ግዛት ተዘዋውረው የሚኖሩባት ፤ሐብትና ንብረት ያፈሩባት፤ ደስታንና መከራን የተጋሩባት፤ ተጋብተውና ተዋልደው ተተኪ ትውልድ የፈጠሩባት፤ ባሕልና ቋንንቋ የተለዋወጡባት፤ በእምነት የተሳሰሩባት በአጠቃላ የሰው ዘር ምንጭ የሆኑት ውህዳን ነገዶችና ጎሳወች ኢትዮጵያዊ ሆነው ለረጅም ዘመናት የኖረባት ታላቅና ታሪካዊት ሐገር ነበረች። በዚህ አይነት የህዝባችንና የሐገራችን የታሪክ ትውስታ ሲዘከር መዘንጋት የማይገባው የአማራው ውህዳዊ ኢትዮጵያዊነት አስተወፅኦ ነው።