የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ አለም አቀፍ የመንገደኞች አየር ማረፊያና ሆቴል ሊገነባ ነው።
በዓመት ሰማንያ ሚሊዮን መንገደኞችን የሚያስተናግድ የመንገደኞች አየር ማረፊያ ከአዲስ አበባ አርባ ስምንት ኪሎሜትር ላይ ከምትገኘው ቢሾፍቱ ከተማ ሊገነባ ማቀዱን ይፋ አደረገ።
የፋና ብሮድካስት ድርጅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስኪያጅን ተወልደ ገብረማሪያም ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው አየር መንገዱ ለሚገነባው አየር ማረፊያና ከጎኑ ለሚገነባው ሆቴል ከኦሮሚያ ክልል ጋር እየመከረ መሆኑ ታውቋል።