ሥነ-ስርዓት! – የአቤል ማስታወሻ ከቅሊንጦ

“they say that time heals all things,they say you can always forget;
but the smiles and the tears across the years
they twist my heart strings yet!”
― George Orwell, 1984
የመታሰሬ ምክንያት መናገሬ ነው ፡፡ መንግሰት በሬ ወለደ “ሽብር” የሚል ክስ ሳይመስርትብኝ በፊት ይጠይቀኝ የነበረው በማህበረሰብ ሚዲያ የምጽፍበትን የምናገርበት አላማ ነበር፡፡ አላማዬ ተፈጥሮአዊ የመናገር መብቴን ማከናወን አንደሆነ ስናገር ከዚህ ተጨማሪ ሌላ ምክንያት ያለኝ ይመስል የተረፈኝ ድብደባ ነበር ፡፡ በዚህ ሂደት ወትሮም ገመምተኛ የነበረውን ግራ ጆሮዬን አጥቻለሁ፡፡ የሚቆጨኝ ነገር የለም፡፡ የሚያስቆጭ ነገር ካለም መቆጨት ያለብኝ የመናገር ነጻነት ያለውና ያን ነጻነቱን የሚጠቀም ሰው ሆኜ በመፈጠሬ ነው ፡፡

ጦማሪ አቤል ዋበላ
አላማዬ መናገር ነው ፡፡ አላማዬ መማር መማማር፣ ግድየለሽነትን በእውቀት ማስወገድ ነው ፡፡ ይህ አላማዬ ከማንም ያልተቀበልኩት ሰው በመሆኔ ብቻ ያገኘሁት ነው፡፡ ይህንን መሰረታዊ የሰውነት መብቴን ማንም አንዲነፍገው አልፈቅድለትም ፡፡ የመንግሰት ሹመኛ ይሁን ተራ ግለሰብ ፣ ተቋም ይሁን ማህበረሰብ የመናገር መብቴን ልሰጠው አልደራደርም ፡፡
የምናገረው በአደባባይ ፣ በገዛ ቤቴ ፣ በማህበራዊ ሚዲያ በእስር ቤት በፍርድ ቤት በፓሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል በአጠቃላይ በአካባቢዬ ያለውን ግለሰብና ቡድን ሳላውክ በሃላፊነት ነገር ግን በማንኛውም ቦታ ነው ፡፡ ይህንን እነዳላደርግ ቁጣ ፣ ማስፈራሪያ፣ የማሰቃየት ተግባር እስርና ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከልከል አላገደኝም ለወደፊትም እንዲያግደኝ አይሆንም ፡፡
ጓደኞቼም ሆነ እኔ አሁን ያለንበትን እስር ማስወገድ እንድንችል ስደትና ሌሎች መንገዶች አንድንመለከት ሥርዓቱ በደህንነት ሰራተኞቹ ጥቆማ ሰጥቶን ነበር፡፡ የመጨረሻዋ ሰአት ስትቃረብ ከልብ የሆነ አእምሮን የሚፈታተን ውይይት አድርገን ነበር፡፡ ከመታሰራችን ቀናት ቀድሞ ሚያዝያ 15/2006 በገጻችን ዞን9 አንዳስነበብነው“ ተፈጥሮአዊና ህገ መንግሰታዊ መብታችንን ማስረከብ “ እጅግ ስለበዛብን የምንከፍለውን ዋጋ እና የስርአቱን ቂመኝነት እያወቅን መናገራችንን አንደምንቀጥል አውስተን ነበር፡፡

የተራዘመው የእስር ጊዜም ይሄንን አቋም አልለወጠውም፡፡ አሁንም መናገር አሁንም ሃሳቤን መግለጽ እፈልጋለሁ፡፡ ይህ ሰው ሆኖ የመወለድ መብት በምንም አይነት ላባክነው አልፈልግም፡፡ግንቦት 19/2007 በዋለው ችሎትም የተፈጸመውም ይሄ ነው፡፡

ይህንን ክስ የሚከታተል ሰው ሁሉ አንደሚያውቀው19ኛ ወንጀል ችሎት በቀረብንባቸው ጊዜያት ዳኞቹ ንጽህናችንን የምናረጋግጥበትን እድል የሚያጣብቡ ውሳኔዎቸን መወሰናቸው ፣ የራሳቸውን ውሳኔ መልሰው መካዳቸው ፣ አቃቤ ህግ በቸልተኝነት የፍትህ ሂደቱን አንዲያዘገይ መፍቀዳቸው ፣ ማረሚያ ቤት የሚደርሱብንን የመብት ረገጣዎች ሰምተው አጥጋቢ እርምጃ አለመውሰዳቸው ሳያንስ ከሁሉም የከፋው ደሞ ችሎት ውስጥ እነዳንናገርና ሃሳባችንን እንዳንገልጽ ማፈናቸው ነው ፡፡

ይህንን ተከትሎ መፍትሄ ይሆናል በማለት ሃሳባችንን በችሎት እንዳንገልጽ መታፈናችንን በመግለጽ የመሃል ዳኛው አንዲቀየሩ አቤቱታም አቅርበን ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ ጥያቄያችንን ውድቅ ቢያደርገውም መሃል ዳኛው በራሳቸው ፍቃድ ከእኛ ( ከነሶልያና ሽመልስ) የክስ መዝገብ ራሳቸው አግልያለው ብለው የነበረ ቢሆንም አሁንም ድረስ የሚሰየሙት ራሳቸው ናቸው :: ችሎቱም አንደተለመደው ለአቃቤ ህግ እንደፈቀደ ለእኛም ሆነ ለዳኞቹ ለራሳቸው የማይገቡ ነገሮች የሚናገርበት እኛም አንዳንዴ ካልሆነ በስተቀር እንዳንናገር የምንታፈንበት ሆኖ በኤሊ ፍጥነት እያዘገመ ነው ፡፡

ይህ መዘግየት አንደሚያሳስበን ዳኞቹ የተረዱ አይመስለኝም፡፡ በነጻነት ልናደርጋቸው የምንፈልጋቸው ነገሮች አንዳሉን ከሚወዱንና ከምንወዳቸው ሰዎች እስር ቤቱ አንደነጠለን ዘንግተውታል፡፡
የአገሪትዋን የማረሚያ ቤቶች ሁኔታ እና የማረሚያቤቶቹን የእስረኞች አያያዝ አያውቁት ይመስል፣ እኛ የተፈጠርንበትን የጉድ ዘመንና የምንተውንበት ወለፈንድ ድራማ አስገርሞን ፈገግ ማለታችንን አይተው እስሩ የተመቸን እየመሰላቸው በቀጠሮ ላይ ቀጠሮ መደራረባቸው አግባብ አለመሆኑን መናገር ነበረብኝ ፡፡ መታሰራችን ጤናማ መንፈሳችንን እያደከመ መሆኑን አቃቤ ህግ እስከዛሬ አለኝ ሲል ያልተደመጠውን በድንገት ያመጣውን አንድ ዶክመንተሪ ሲዲ (አንደኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ ላይ የቀረበ) ለማየት ሃያ ቀናት መውሰዱ ፣ በአጭር ቀናት ውስጥ አይተው በፍጥነት ወደቀጣዩ የፍርድሂደት እንድንሄድ አንዲደርጉ ለመግለጽ በፍርድ ቤቱ ሥርአት መሰረት እጄን አውጥቼ አውጥቼ አሳየሁ። አንደተለመደው እነዳንናገር ዳኞቹ እቀባ በማድረግ የመሰማት እድላችንን ነፈጉን ፡፡ ለመናገር ፍቃድ ስንከለከል ሳይፈቀድልን መናገር ጀመርን ፡፡ “ የምጣዱ ሳለ የእንቅቡ ተንጣጣ” አንዲል ያገሬ ሰው ተበድለን በተናገርን “ስነስርአት አድርጉ” የሚል ትእዛዝ ከዳኞቹ መጣ፡፡ በዚህ ሰአት “እናንተ ራሳችሁ ሥነ-ስርዓት አድረጉ” በማለት ስርአት አልበኛ የሆነው የንጹሃን ዜጎችን መብት ለማፈን የተዘጋጁት እነሱ መሆናቸውን ተናግሬያለሁ፡፡ ይህንን ስናገር ስሜት ተጭኖኝ ይሆናል፡፡ ነገር ግን በዚያ ችሎት የሚፈጸመውን በደል ትውልድ እንዲረዳው ታሪክም መዝግቦ አንዲያቆየው መዘከር ነበረብኝ፡፡

ሥነስርዓት ምን እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ወላጆቼ በገባቸው መጠን ጥብቅ በሆነ ስነስርዓት አሳድገውኛል፡፡ ይህ ታላቅን ብቻ ሳይሆን ታናሽንም ማክበር አንደሚገባ ሥነ-ስርዓትና ደንቦችን መጣስ አንደማይገባ ይጨምራል፡፡ ( በሁለት አመት የዞን9ሥራቸንም ለማንኛውም የአገሪቷንህግ ሳንጥስ ህጋዊ ሆነን የቆየነው ለዚያምጭምር ነው ) ነገር ግን መታፈንን በጻጋ መቀበልና በደልን መሸከምን አይጨምርም፡፡ የማንም ሰብአዊ መብት ተሟጋች ወይም ነጸ አውጪአይደለሁም ፡፡ የግለሰብ መብቴ ሲነካ ግን ዝም ማለት አልወድም ፡፡ በተለይም ደግሞ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብቴ አንዲከለከልአልፈልግም ፡፡ ስለዚህም ይህንነ ከዚህ በፌት ላደረገ ፣ ከአሁን በማድረግ ላይ ያለ ፣ ወደፌትም ለማድረግ የሚያስብን ሁሉ::

– See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41810#sthash.1Dcfgwji.dpuf

“የሰለሞን ዴዜዴራታ!!” – ከኤርሚያስ ለገሰ (የመለስ ትሩፋቶች መጽሐፍ ደራሲ)

በሀገረ አሜሪካ መስፍን በዙ የሚባል ትንሽ ሰው አለ። ይህ ሰው ” ቲጂ ቴሌቪዥን” የሚባል በህውሀት የሚደገፍ ተንቀሳቃሽ መንኩራኩርና እሷን የሚሸከምበት ኮልኮላታ አለችው። የሁለቱም ቴክኒሻን፣ ፓይለት፣ ኮፓይለት፣ አስተናጋጅ፣ ተስተናጋጅ እሱ ብቻ ነው። ማንንም ስለማያምን አያሳፍርም። ለነገሩ የሀገሬ ልጆች እንደሰው ሰለማይቆጥሩት አይጠጉትም። በደንብ የሚያውቁት ደግሞ ” ከራሱ የተጣላ፣ግማሽ ሰው” ይሉታል። ቀትረ ቀላል!
ermias copy
እናም ህውሀት የሸለመውና ግርማ ብሩ ወጪውን የሚሸፍንለት መንኩራኩርና ኮልኮላታ አለው። ታዲያ! መንኩራኩሯን ሲሾፍራት በጣም ስለሚፈራና ድንጉጥ ስለሆነ የቀድሞ ክልል አንድን የሚያክል ባይነኩላር በሁለት አይኖቹ ላይ ይገጥማል። ባይነኩላሩ ካሜራ ስለተገጠመለት የድፍረቱ ምንጭ ሆኖ ያገለግለዋል። በጥርጣሬ ለተመለከተውና መንኩራኩሯን ለተጠጋ ሁሉ ” እስቲ ወንድ ከሆንክ ጫፌን ንካ! ” እያለ በተደጋጋሚ ይማፀናል። ጫፋን ሲነኩት እንደ ጐማ ተጠቅልሎ ለመተኛት እየተዘጋጀ። በነገራችን ላይ ወገቡም ላይ ሻጥ ያደረጋት ዲሞፍተር አለችው። ርግጥ ዲሞፍተሯ ቀጥረው እንደሚያሰሩት ጌቶቹ የክርኑን እርዝመትና ክብደት ማሳየት አልቻለችም። አይቻላትም። ምድሪቷ የጌቶቹ ( የድሮ ጓደኞቼ) አይደለችምና! …ይህ አሜሪካ ነው!!

መቼም የድሮ ጓደኞቼ እንደዚህ አይነት ከራሳቸው የተጣሉ ትናንሽ ሰዎችን ለፕሮፐጋንዳ መጠቀም የመጨረሻ አማራጫቸው እየሆነ መሄዱን ስመለከት ያሳዝነኛል። ርግጥ ምንጩን ስለማውቀው ሀዘኔታዬ ገደብ አለው። ደጋግሜ እንደምናገረው ምንጩ የበታችነት ስሜት ( inferiority complex) ነው። ይሁን እንጂ ይህ ስሜት የሚፈጥረው የፍርሀት ጐርፍ ራሳቸውን ተሸክሞ እንደሚሄድ ስለማውቅ እምብዛም አይገርመኝም። በሌላ በኩል የበታችነት ስሜቱ ዘረኝነት የፈጠረውና ከዘመኑ ጋር መለወጥ እንደማይችል ሳስብ ደግሞ ሀገራዊ አደጋው እየታየኝ እደነግጣለሁ። በየጊዜው የሚፈለፈለው የበቀል እርግዝና ማቆሚያው የት ነው?… ጠመንጃና ጉልበት እስከ መቼ መፍትሔ ይሆናል?… በየቦታው ” ጥቁር ባንዲራ” ይዘው በሚቆሙ ጃርቶች መከበብ ምን ይፈይዳል?……

የቀድሞ ጓደኞቼን ባህሪ ትተን ወደ መስፍን በዙ እንመለስ። መነሻችን እሱ በመሆኑ። የሌላችሁን ባላውቅም ባጋጣሚ የተመለከትኳቸው ” ቲጂ ቴሌቪዥን” ፕሮግራሞቹ ” የሞኝ ዘፈን ሁልጊዜ አበባዬ!” የሚለውን ያስታውሰኛል። የመስፍን “አበባዬ” ክቡር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ ነው። አልፋና ኦሜጋው። በጥላሁን ስም ካልነገደ የራሱን ቀፎነት መደበቅ አይችልም። እስኪሰለቸን ጥላሁን ገሰሰ አሜሪካን ሀገር ቱር ሲያደርግ የሚያዞረው እሱ እንደሆነ ይነግረናል። የማሞ ቂሎ ነገር ጌቶቹን እንዳስቀየመ እንኳን ሳያውቅ ጥላሁን አሁን አምባሻ ያለበትን በንዲራ እንደሚጠላና እንደ ኢትዬጲያ ባንዲራ እንደማይቆጥር ሀይለማርያም ደሳለኝን ፊት ለፊቱ አስቀምጦ ይነግረዋል። ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ ጋሽ ሀይሌ መልስ የመስጠት አቅሙ እንዳሁኑ አልጐለበተም እንጂ ቢጐለብትማ ኖሮ፣

” አምባሻዋን ጠፍጥፈው የፈጠሯት የሰሜን ሰዎች ናቸው። በአንባሻዋ ላይ በሌላው አካባቢ ያለው ህዝብ ምንአይነት ስሜት እንዳለው አያውቁም ነበር” የሚል የግመሏን ምላሽ የሚያስታውስ ታሪካዊ መልስ ይሰጥ ነበር።

መስፍን በዙ ሰሞኑን ለፈፀመው ቂላቂል ስራ እንደሱ ወረድ ብዬ መልስ መስጠት ሳስብ አንድ ነገር አገኘሁ።በአንድ ወቅት ንዋይ ደበበ በድምጳዊ ሰለሞን ተካልኝ ላይ የሰጠው አስተያየት። የሚገርም ምላሽ ነው! ብራቮ ንዋይ!! እንደ እውነቱ ከሆነ መቀነስም መጨመርም አላስፈለገኝም። የመጨረሻዎቹ መስመሮች ” የፓለቲካ ጨዋታ እንዴት በጣም ለትናንሽ፣… ላልበሰሉ… ከሁሉም በላይ ሆዳም ሰዎች” በማለት የገለፀውን ለመስፍን በዙ ምላሽ ይሁንልኝ። አንቀጱ በሙሉ አርቲስት ንዋይ ለተናገረለት ሰው ቋሚ ንብረት ሆኖ ይቀመጥ። ስያሜውንም ” የሰለሞን ዴዜዴራታ” ይበለው።

እነሆ! ንዋይ ” የሰለሞን ዴዜዴራታን” እንዲህ ነበር ያስቀመጠው፣

” … አሁን ላይ ሆኞ ስገመግመው ሙያተኛ ነው?… ወይንስ ፓለቲከኛ ነው?… ወይንስ የትግሉን አምባ ዝም ብሎ እዛም፣ እዛም እየገባና እየሄደ የሚበጠብጥ ያበደ ሰው ነው?… ግራ ይገባኛል። ሰውየውን በቀጥታ ለመተርጐም ግራ ያጋባል። ምክንያቱም እጅግ ከማናችንም በፊት ቀድሞ የከረረ ትግል ለማድረግ የወሰነ የሚመስል ሰው ነበር። እንደውም አሁን በስልጣን ላይ ያለውን መሪ ( አቶ መለስ መሆኑ ነው) የጡት ማስያዣና ፓንት አልብሶ በሲዲው ላይ አድርጐ እየዞረ የመሸጥም ጠንካራ የትግል ስሜት ነበረው። ኧረ! እንደውም እጁን በሰንሰለት አስሮ ፣በብረት ውስጥ ቁጭ ብሎ የእነማንዴላን የትግል አርአያነት ሊላበስ የሞከረ ነው። እኛን ሁሉ መንፈሳችንን የሚያበረታታ ፣ አሳምኖ አብረነው እንድንቆም ካደረገ በኃላ ባልታሰበ ጊዜ ውስጥ ዛሬ እንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ገባ። እንደዚህ አይነት ፍጡር አለወይ የሚያሰኝ ይመስላል። ለምን? …ከማንም በላይ በአትኩሮት ሲከታተሉትና ማንነቱን ሲመረምሩ የነበሩት እነሱ ናቸው። ታሪኩ በሙሉ እጃቸው ላይ አለ።… የፓለቲካ ጨዋታ እንዴት በጣም ለትናንሽ ሰዎች እንደሚጠቅም!… እንዴት ላልበሰሉ ሰዎች እንደሚጠቅም!… ከሁሉም በላይ እንዴት ለሆዳም ሰዎች ምቹ እንደሆነ ነው።…ታሪክና የኢትዬጲያ ህዝብ ጊዜውን ጠብቀው ፍርድ እስኪሰጥ ድረስ መጠበቅ ነው!!…”

– See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41821#sthash.rS75xlxi.dpuf

No legitimacy in denied Democracy! A Press release from Blue Party

Blue Party was clear before entering into 2015 Ethiopian General Election as there are no capable and independent institutions to handle free and fair election even at the minimal standard. It was also clear that the regime is not ready to hold a free and fair election.  Our understanding on non existence of a political platform to conduct a free and faire election was proved by the start of the election process. Our candidates were denied for registration and some others were illegally canceled by the Election Board after they were registered. The regime in fear of losing power has established a controlling system (1 to 5)to undermine freedom of citizens which is designed to make them forcefully vote for the regime otherwise threaten them to punish.

The security forces and cadres of EPRDF continued in harassing, beating, arresting and some cases killing candidates and potential observers of opposition parties without any valid reasons and the order of courts. Independent medias and civic associations were not allowed to exist to teach people about the civil rights and possible alternatives. Public medias were hectic to reject our campaign messages from transmission using censorship which is totally prohibited by Ethiopian Constitution. In due time our active members were fugitive and arrested taken from their working areas or from their living homes. Some of them are still suffering in prison cells.

Any election accompanied by such illegal actions and irregularities in no ways be free and fair.  Consequently the result shows a total sweep and a “100%” win by the regime. This is a message of disgrace ascertaining that a multi party system is over in Ethiopia and the reign of a single party system affirmed to flourish. This is a dark time for Ethiopians and a shame for the friends of Ethiopian Government. As the result is so embarrassing, the government has lost the confidence to publicize the full outcome of the election.

In the first instance, large section of the population including Blue Party’s potential voters were not registered to vote due to losing confidence on the election process. It was only members of the ruling party and some others who were forced to register as voters who had the right to cast their vote. During our campaign, large number of the society became aware of the alternatives presented by Blue Party and all the votes Blue party has gained from this election are a swap from ruling party supporters. We are therefore grateful for all our voters as you choose us willingly not forcefully and for purpose not for any material rewards.

Blue Party would like to extend its gratefulness to all members, candidates, activists and party observers who were beaten, arrested, detained and harassed during the whole election period as you were vital to make our Party popular, reliable and trustworthy by the general public.

Due to all mentioned irregularities and illegal actions taken by the ruling party and by other weak institutions to hold free and fair election, Blue Party does not accept the process as free and fair and at the same time does not accept the outcome of unhealthy and undemocratic election result. The Government to be established by this rigged vote won’t have legitimacy as it denied the will of the people. Blue Party continues on its endeavor to bring freedom and justice to Ethiopians as a whole and calls upon all citizens to join it on its continuing struggle to secure our freedom.

May 29, 2015
Addis Ababa

ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫውን ውጤት እንደማይቀበለው አስታወቀ

‹‹በኃይል የተቀማ ድምፅ የሚመሰረት መንግስት በህዝብ ተቀባይነት የለውም››

• ‹‹በሂደቱ በመቆየታችን የኢህአዴግን አውሬነት አሳይተናል›› ኢ/ር ይልቃል

• ‹‹የአፍሪካ ህብረት ራሱንም ሌላም ማዳን የማይችል የእንጨት ድስት ነው›› አቶ ስለሽ

ሰማያዊ ፓርቲ የ2007 ዓ.ም ሀገራዊ ምርጫ ሂደቱንም ሆነ ውጤቱን እንደማይቀበለው አሳወቀ፡፡ ፓርቲው ዛሬ ግንቦት 21/2007 ዓ.ም በጽ/ቤቱ ‹‹ነጻነት በሌለባት ኢትዮጵያ ሕዝባዊ አስተዳደር መትከል ዘበት ነው!›› በሚል ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ምርጫው ‹‹ከዚህ ቀደም ከተካሔዱት ምርጫዎች ጋር እንኳ ሊወዳደር የማይችል እጅግ ኢ-ፍትኃዊ፣ ወገንተኛና ተዓማኒነት የሌለው በመሆኑ ሰማያዊ ፓርቲ ሂደቱንም ሆነ ውጤቱን አይቀበለውም፡፡›› ብሏል፡፡

በ2007 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ ሲወስን ገለልተኛና ብቃት ያላቸው ተቋማት እንደሌሉና ገዥው ፓርቲም እውነተኛ ምርጫ እንደማይፈቅድ እያወቀ መሆኑን የገለፀው ሰማያዊ በሂደቱ የተሳተፈው የስርዓቱን ችግሮች ለማጋለጥ እንደሆነ አስታውቋል፡፡ የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ‹‹በሂደቱ ውስጥ በመቆየታችን እጩዎቻችን በህገ ወጥ መንገድ ሲታገዱ፣ ታዛቢዎች ሲከለከሉና ሲታሰሩ አሳይተናል፡፡ በሂደቱ በመቆየታችን የኢህአዴግን አውሬነት አሳይተናል፡፡ ከመጀመሪያው ጀምሮም ሆነ በምርጫው ወቅት የነበረውን ማጭበርበር ለኢትዮጵያ ህዝብና ለዓለም አጋልጠንበታል፡፡›› ብለዋል፡፡ የፓርቲው ም/ሊቀመንበር እና የምርጫ ጉዳይ ኃላፊው አቶ ስለሽ ፈይሳ በበኩላቸው ምርጫው መትረየስ ተጠምዶ፣ ብረት ለበስ በየ መንገዱ ቆሞ፣ የአጋዚ ጦር አባላት ከተማ ውስጥ ተሰማርተው ከመካሄዱም ባሻገር ከፍተኛ የድምጽ ማጭበርበር የነበረበት ነው ብለዋል፡፡ የምርጫው ብቸኛ የውጭ ታዛቢ የሆነውን የአፍሪካ ህብረት ታዛቢ ቡድንም ራሱንም ሌላም ማዳን የማይችል ‹‹የእንጨት ድምጽ ነው!›› ሲሉ ተችተዋል፡፡

ምርጫው በህገ ወጥ አሰራሮች የታጀበ፣ በማንኛውም መመዘኛ ፍትሃዊ፣ ነፃና ተአማኒ ሊሆን እንደማይችል ሒደቱ በግልፅ አመላካች ነበር ያለው ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹በውጤቱም በሐገራችን የዲሞክራሲና የመድብለ ፓርቲ ስርዓት መኖርን ወደ መቃብር የከተተና ኢትዮጵያ የአንድ ፓርቲ ስርዓት ሐገር መሆኗን ያረጋገጠ ነው፡፡..ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ የጨለማ ዘመን መምጣቱን ከማሳየቱ ባሻገር ኢህአዲግ በፍርሃት ተውጦ ሁሉንም ለመቆጣጠር ባደረገው ሩጫ ለመግለፅ እስኪያፍር ድረስ የሚያሸማቅቅ ውጤት እንዲከናነብ ሆኗል፡፡›› ብሏል፡፡ በኃይል በተቀማ ድምፅ የሚመሰረት መንግስትም በሕዝብ ተቀባይነት እንደሌለውም ገልጾአል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በአፈና እና ጭቆና ውስጥ ሆነው ድምጽ ለሰጡት መራጮች ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ በምርጫው ሂደት የተንገላቱ፣ የታሰሩትን፣ የተደበደቡና የተሰደዱትን አባላቱንም ፓርቲያቸው በኢትዮጵያ ሕዝብ ተስፋ የተጣለበት እንዲሆን ለደረሰባቸው መከራና በደል ክብር ይገባቸዋል ብሏል፡፡ የዜጎች ነፃነት ሳይከበር ነጻና ፍትኃዊ ምርጫ ሊደረግ አይችልም ያለው መግለጫው ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቻችን እስከሚከበሩ ድረስ ሰማያዊ ፓርቲ በሚያካሂደው የነጻነት ትግል ኢትዮጵያውያን ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አድርጓል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጾአል፡፡

Negere Ethiopia's photo.
Negere Ethiopia's photo.

ስለቀጣዩ ትግል ሳስብ ! – ከይድነቃቸው ከበደ (የሰማያዊ ፓርቲ አመራር)

holeta
ዲሞክራሳዊ ምርጫ ሰላማዊ ወይም ጠበንጃ አልባ የትግል ስልት ከሆኑት ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ሆኖም ግን በአገራችን ለሃያ አንድ አመት ወይም ለ5 ዙር ምርጫ የተካሄደ ቢሆንም ህውሓት/ኢህአዴግ የግንቦት ሃያ 24ኛ አመት በሚያከብሩበት ማግስት 100 % በምርጫ ተወዳዳሪ አሸናፊ ሆኛለው ማላት፣ ህውሓት/ኢህአዴግ ለዲሞክራሳዊ ምርጫ የተዘጋጀ አለመሆኑ በሚገባ ያረጋገጠ አጋጣሚ ነው ፡፡የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር እና አባላት የህውሓት/ኢህአዴግ አምባገነናዊ የምርጫ ሥርዓት እግር-በእግር በመከተል ለማጋለጥ ችለዋል ! ለዚህም አኩራ ተግባራቸው አድናቆት እና ምስጋና መስጠት ተገቢና አስፈላጊ ነው፡፡

ሆኖም ግን ከዚህ በኋላ ሌሎች ጠበንጃ አልባ ወይም ሰላማዊ የሆነ ትግል ስልቶችን በመተግበር ሕዝባዊ መንግስት አስኪቋቋም “በአገር ውስጥ” የሚንቀሳቀሱ የዲሞክራሲ ሃይሎች አማራጭ የሰላማዊ ትግል ስልት በመከተል፣ ከሌላው ጊዜ በተሻለ እና በተቀናጀ መልኩ የተጀመረው ከአምባገነን አገዛዝ ወደ ዲሞክራሲ የሚደረገውን ሰላማዊ ትግል መምራት እንደሚያስፈልግ ከምንፈልገው ለውጥ አንፃር ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ አይደለም፡፡ይህን ሃቅ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር እና አባላት አጥብቀው የሚረዱት እውነት እንደሆነ እምነቴና ተስፋዬ የበዛ ነው፡፡

ለውጥ ፈላጊው የሆነው ጭቁኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሣይሰለች የለውጡ ሂደት እንዲፋጠን ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጎን በመቆም ያሣየው ጥረት እና ፍላጎት እንዲሁም ድጋፍ ለዲሞክራሲ ሃይሎች የሁል-ጊዜ ብርታትን የሚሰጥ ነው !ለዚህም የላቀ ተግባር ከበሬታ መስጠት ድጋፍ ለተቸራቸው የተቃወሚ ሃይሎች በፖለቲካ ሥራችን በግብረ-መልስ የሚሰጡት በጎ ምላሽ መሆን እንዳለበት ማረጋገጥ አለብን ፡፡ ይህም በመሆኑ የህብረተሰቡ የለውጥ ፍላጎት ለዲሞክራሲ ሃይሎች ከምንም በላይ ዋንኛ ግባት ነው፡፡
በውጪ ሀገር የሚገኙ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን በገንዘብ እና በሃሳብ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በአገራችን በሰላማዊ መንገድ የመንግሰት አስተዳዳር ለውጥ እንዲመጣ የከፈሉት መሰዋትነት ቀላል የሚባል አይደለም ! ይህ-ቀረ የማይባልበት የሁል ጊዜ ድጋፋቸውም በቀጣይም ከሰላማዊ ትግል ጎን የማይለይ መሆኑ እርግጥ ነው፡፡

ማስታወሻ ፡- ይህ ፁሑፍ የእኔን አስተሳሰብ እንጂ የፓርቲዬን አቋም የሚመለከት አይደለም፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !!!

– See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41801#sthash.ZhgxIEOW.dpuf

ከገዢዎቻችን ለምን አንማርም ? – ግርማ ካሳ

ethiopian-election-2015

“ኢህአዴግ የግንቦት15ቱን ምርጫ መቶ በመቶ ማሸነፉ ከተገለጸ በሁዋላ የኢህአዴግ ደጋፊዎች ከሁለት ተከፍለዋል። ምንጮች እንደገለጹት በርካታ ፊደል ቀመስ አባሎቹ ኢህአዴግ አሸነፍኩ ያለበትን የድምጽ ልዩነት አልተቀበሉትም። ውጤቱን የሚቃወሙ የግንባሩ አባላት ” ህዝቡ ከእንግዲህ በሰላም መንግስት እቀይራለሁ የሚለው እምነቱ ተሟጦ የሃይል አማራጭን ብቻ እንዲመለከት ከማድረጉም በላይ፣ የሃይል አማራጭን የሚከተሉ ሃይሎች በህዝቡም ሆነ በአለማቀፉ ማህበረሰብም የተሻለ ተቀባይነት እንዲያገኙ ያደርጋቸዋል” በማለት ለድርጅቱ አስተያየታቸውን እየሰጡ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ተገኘ የተባለውን ውጤት ከመደገፍ አልፈው፣ ህዝቡ እንዴት ለተቃዋሚዎች ይህን ያክል ድምጽ ሊሰጥ ቻለ በማለት በቁጭት አስተያየት የሚሰጡ ደጋፊዎች መኖራቸውንም ምንጮች ገልጸዋል።”

የሚከተለው ኢሳት ከዘገበው የተወስደ ነው። ዜናውን ለመቀበል አላዳገተኝም። “የሰላም በር ሲዘጋ የአመጽ በር ይከፋታል” እንዳለው አብርሃ ደስታ፣ ፍጹም አሳፋሪ የሆነው የምርጫው ሂደትና የምርጫው ዉጤት፣ ብዙ ዜጎች ሰላማዊዉን እና ሕጋዊዉን መንገድ ትተው ሌላ የትግል አማራጭ እንዲከትሉ ነው የገፋፋቸውና የሚገፋፋቸው።

ሆኖም አንድ ነገር ጠንቅቀን ማወቅ አለብን። መለስ ዜናዊ የሞተ ጊዜ ተከፋፈሉ ወዘተረፈ እያልን ስናወራ ነበር። ግምገማ ተደራረጉ ብለንም ስለነርሱ ስንተነትን ጊዜ አጠፋን። ምናልባት እነርሱ እርስ በርስ ከተከፋፈሉ በግርግር ለዉጥ ይመጣል ከሚል ተስፋ።

ሰዎቹ እርስ በርስ ይጠማመዱ ይሆናል። ነገር ግን መቼም አይለያዩም። ያውቃሉ፣ አንዱ ከወደቀ ሌላዉም እንደሚውድቅ። እነ አባዱላ ፣ እነ አዲሱ ለገሰ፣ እነ ሬድዋን ሁሴን ፣ ሕወሃት ከሌለ የነርሱ እጣ ምን ሊሆን እንደሚችል ይዉቃሉ። ስለዚህ አንዱ በአንዱ ላይ እንደ መዥገር ተጣብቆ ነው የሚጓዙት። ሥር የሰደደም ልዩነት ቢኖራቸውም፣ ተያይዘው ፣ ጀርባ ለጀርባ እየተታከኩ የግፍ አገዛዙን ይቀጥላሉ።

በነርሱ መካከል እርስ በርስ ልዩነቶች ተፈጥረው፣ ሞደሬት የሆኑት አይለው ቢወጡና አገር መረጋጋት ብትችል ደስ ነው የሚለኝ። ግን የሚሆን ነገር አይደለም። እነርሱ አይለያዩም። አንድ ናቸው።

በተቃራኒው እኛ ግን ትናንሽ ልዩነቶች እያለያዩን በጋራ መንቀሳቀስ አልቻልንም። በአገር ቤት ሰማያዊ፣ አንድነት፣ መኢአድ ፣ ትብብር …እንዲሁም ሌሎች ለምን በአንድ ላይ መስራት አልቻሉም ? መድረኮች ከነሰማያዊ ጋር ለምን መስራት አልቻሉም ? ወደ ዉጭ አገር ስንመጣ ደግሞ ሸንጎ፣ የሽግግር ምክር ቤቱ፣ ግንቦት ሰባት፣ ሶሊዳሪቲ ….ለምን አብረው ፣ አንድ አማራጭ ኃይል አቋቁመው መስራት አልቻሉም? ሁሉም ነጻነት ፈላጊ አይደሉም እንዴ ? ሁሉም ፍትህና ዴሞክራሲን ናፋቂ አይደሉም እንዴ ? ሁሉም ለአንዲት ኢትዮጵያ የቆሙ አይደሉም እንዴ ? ታዲያ ለምን መተባብር ቸገራቸው ?

ወገኖቼ, ደግሜ እላለሁ ገዢዎቻችን አይለያዩም። እነርሱ አንድ ሆነው፣ እኛ ደግሞ ተለያይተን እስከቀጠልን ድረስ ረግጠው፣ አዋርደው ይገዙናል። አራት ነጥብ። በተናጥል በባዶ፣ እንጮሃለን፣ እንኮንናችቸዋለን፣ ዘራፍ እንላለን ፣ የመግለጫ ዉርዥብኝ እናወርዳለን ። ግን የምናመጣው ነገር አይኖርም።

ስለዚህ ለዉጥ ክአገዛዙ ከራሱ ቢመጣ እስየው። ስንማጸንና ስንጎተጎት የነበረ ስለሆነ። ሆኖም ከአሁን በላይ ተስፋን እነርሱ ላይ ሳይሆን፣ አምላካችን እና አምላክ በሰጠን የተባበረው ክንዳችን ላይ መሆን ነው ያለበት። እመኑኝ ስርዓትቱ የበሰበሰ ስርዓት ነው። ገና ድሮ መወገድ የሚችል ስርዓት ነበረ። እስከ አሁን የቆየው እኛ ስለፈቀድንለት ብቻ ነው። አሁንም በአንድነት መንቀሳቀስ ካልቻልን፣ በአፋችን ብንናገረዉም ስርዓቱ እንዲቀጥል እየፈቀድንለት ነው።
ገዢዎቻችን ለክፋት አንድ ከሆኑ፣ እኛ ለመልካም ነገር እንድ መሆን እንዴት ያቅተናል ?

– See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/7378#sthash.mJ2L9q73.dpuf

በምርጫ ቦርድ ውጤት የኢህአዴግ ደጋፊዎች ከሁለት ተከፍለዋል

ግንቦት ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ የግንቦት15ቱን ምርጫ መቶ በመቶ ማሸነፉ ከተገለጸ በሁዋላ የኢህአዴግ ደጋፊዎች ከሁለት ተከፍለዋል። ምንጮች እንደገለጹት በርካታ ፊደል ቀመስ አባሎቹ ኢህአዴግ አሸነፍኩ
ያለበትን የድምጽ ልዩነት አልተቀበሉትም። ውጤቱን የሚቃወሙ የግንባሩ አባላት ” ህዝቡ ከእንግዲህ በሰላም መንግስት እቀይራለሁ የሚለው እምነቱ ተሟጦ የሃይል አማራጭን ብቻ እንዲመለከት ከማድረጉም በላይ፣ የሃይል አማራጭን
የሚከተሉ ሃይሎች በህዝቡም ሆነ በአለማቀፉ ማህበረሰብም የተሻለ ተቀባይነት እንዲያገኙ ያደርጋቸዋል” በማለት ለድርጅቱ አስተያየታቸውን እየሰጡ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ተገኘ የተባለውን ውጤት ከመደገፍ አልፈው፣ ህዝቡ እንዴት ለተቃዋሚዎች ይህን ያክል ድምጽ ሊሰጥ ቻለ በማለት በቁጭት አስተያየት የሚሰጡ ደጋፊዎች መኖራቸውንም ምንጮች ገልጸዋል።
ኢህአዴግ እያሰባሰበ ባለው መረጃ ላይ እንደተገለጸው፣ አንዳንዶች ” ይህ ህዝብ ምን አይነት ልቡ የማይታወቅ ከሃዲ ህዝብ ነው! እንዴት ይሄን ሁሉ ልማት እያዬ ለተቃዋሚ ድምጹን ሊሰጥ ቻለ?” የሚል አስተያየት ሰንዝረዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫ ቦርድ ራሱ ባወጣው ሰሌዳ መሰረት የምርጫውን ውጤት መግለጽ የነበረበት ግንቦት21 ቢሆንም፣ የግንቦት20 በአልን ለማድመቅ እንዲረዳ በሚል ከእቅዱ በፊት እንዲገለጽ መደረጉን ምንጮችን ዋቢ በማድረግ
ዘጋቢያችን ገልጿል።
ኢህአዴግ በየክልሉ ከፍተኛ ወጪ የወጣበት የፌሽታ በዓላትን አዘጋጅቷል። ትናንት የገዢው ፓርቲ ደጋፊ አርቲስቶች ያዘጋጁት የኪነጥበብ ምሽት በብሔራዉ ቲያትር ተካሂዷል፡፡፡ በርካታ የፌዴራል የመንግስት መ/ቤቶች በተለያዩ ሆቴሎች
በዓሉን ለማክበር ጥሪ አስተላልፈዋል።
ምርጫ ቦርድ የኢህአዴግን አሸናፊነት ቢያውጅም መድረክ የተባለው የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ስብስብ የምርጫውን ውጤት አልተቀበለውም። ድርጅቱ ምርጫው አነስተኛ የሚባሉ መስፈርቶችን እንኳ ያላሟላ በማለት አጣጥሎታል። መድረክ
በአገሪቱ ውስጥ ያሉ ገለልተኛ የሚባሉ ሰዎች ተመርጠው መምርራ እንዲያካሂዱ ጠይቋል።
ሰማያዊ ፓርቲ ምርጫውን በተመለከተ ይህን ዜና እስካጠናከርንበት ጊዜ ድረስ ያለው ነገር የለም። መንግስት የሰማያዊ ፓርቲ ደጋፊዎችን እያዋከበ በማሰር ላይ መሆኑ፣ ፓርቲውን አጣብቂኝ ውስጥ ሳይከተው አልቀረም። ሰማያዊ የምርጫውን
ውጤት ይቀበለዋል ተብሎ አይጠበቅም።
የአሜሪካ መንግስትና የአውሮፓ ህብረት ምርጫውን በተመለከተ በርካታ እጸጾችን አውጥተው ቢገልጹም፣ ከኢህአዴግ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንደማያቋርጡ አስታውቀዋል። የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ባወጣው መግለጫ ዲፕሎማቶች
በምርጫ ታዛቢነት እንዳይሰታፉ መከልከላቸው፣ ምርጫው አሳታፊ አለመሆኑንና የተለያዩ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች መታሰራቸውን በመግለጫቸው አመልክተዋል።
በምርጫው ሂደት ያጋጠሙ በርካታ አስገራሚ ክስተቶች ለኢሳት እየደረሱ ነው። ግንቦት12 ቀን 2007 ዓም በአዲስ አበባ ልዩ ቦታው ላንቻ ወይም ጠመንጃ ያዥ ነዋሪ የሆነ አንድ የ12 ዓመት ህፃን የኢህአዴግን የምርጫ መልዕክት ያየዘ
ፖስተር ከተለጠፈበት ግድግዳ ላይ ቀደሃል በሚል 6 ወር ተፈርዶበታል።
በአዲስ አበባ ችሎት በሚባል ቦታ አርብ ግንቦት 14 ቀን 2007 ዓ.ም ሁለት ማየት የተሳናቸው ወጣቶች ተይዘው ታስረዋል። ወጣቶቹ የተያዙት አንደኛው ሙሉ ሰማያዊ ልብስ ለብሶ በመውጣቱ በተፈጠረው አተካራ ነው። የአካባቢው
ሴት ካድሬ አንደኛውን ማየት የተሳነው ወጣት “ለምን ሰማያዊ ልብስ ለበስክ የሰማያዊ ፓርቲ አባል ነሆይ?” በማለት ጥያቄ ስታቀርበለት፣ ጓደኛው “ምን አገባሽ ምንስ ብለብስ!” የሚል መልስ መስጠቱን ተከትሎ፣ ግለሰቧ በብስጪት
ለደህንነቶች ባስተላለፈችው ጥቆማ መሰረት ሁለቱም ወጣቶች በድንገት ታፍነው የተወሰዱ ሲሆን እስከዛሬ ድረስ ታስረው ይገኛሉ።
መነን መሰናዶና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም ፀሃይ ጮራ ት/ቤት ውስጥ የሚገኙ ቁጥራቸው 20 መምህራንና 30 ተማሪዎች የሰማያዊና የአንድነት ፓርቲ አባላት ናቸው በሚል ዝርዝራቸው ለጸጥታ አካላት ተልዕኮ በልዩ ሁኔታ ክትትል እንዲደረግባቸው ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከምርጫ በፊት ትዕዛዝ ተላልፎ እንደነበርም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

ግንቦት 20 የበላቸው ቀሽ ገብሩዎች (በወይንሸት ሞላ )

ኢህአዴግ ታግዬ አስገኘኋቸው ከሚላቸው መብቶች መካከል አንዱና ሁሌም የሚያወራለት የሴቶች መብት ነው፡፡ በተለያዩ ፎረሞች ያደራጃቸው አባላቱም ኢህአዴግ የሴቶች መብትን እንዳስከበረ ለማሳየት ተደራጅተው ዶሮ የሚያረቡትን፣ ድንጋይ የሚቀጠቅጡትን ሴቶች ‹‹ተጠቃሚነት›› በመጥቀስ የፓርቲያቸውን ስኬት ሲያወድሱ መዋላቸው የዕለት ተዕለት ተግባር ነው፡፡Wonishet Mola (Blue Party )

በእውነቱ በባህልም ሆነ ከእምነት ጋር በተያያዘ ሴቶችን እንደሚጨቁኑ የሚወቀሱት የአረብ መንግስታት እንኳ ስለ ሴቶች መብት መከበር በሚጥርበት ወቅት ሴቶች ድንጋይ ስለፈለጡና ሌሎች አድካሚ ስራዎችን ስለሰሩ የሴቶችን መብት አስከብሬያለሁ የሚለው ዝባዝንኬ ውሃ የሚቋጥር ሊሆን አይችልም፡፡ በ1960ዎቹ ትውልድ ሴቶች የማይናቅ ተስትፎ እንዳደረጉ እነ ማርታን በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል፡፡ ደርግ የሚያፍነው ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ቢሆንም የሴቶች መብት ተለይቶ የተነፈገበት ጊዜ አልታየም፡፡ ኢህአዴግ ግን ራሱን ከደርግ ጋር በማወዳደር የተሻለ መብት እንደሰጠ የሚገልጸም ምን እንደሆነ በግልጽ አጥጠቀስም፡፡

ሆኖም የሴቶችን መብት አስከብሬያለሁ ድስኩር በውቅሩ ያለውን ዘርፈ ብዙ ጭቆና ለመሸፈም ካልሆነ በእውነታው የምናየው አይደለም፡፡ በህወሓትኢህአዴግ ትግል ውስጥ በርካታ ሴቶች መሳሪያ አንግተው ስርዓቱን አዲስ አበባ ድረስ አድርሰውታል፡፡ እንደ አረጋሽ ያሉት በፖለቲካ ልዩነት ስርዓቱን ጥለው ሲወጡ ሌሎቹ ደግሞ የረባ ቦታ ሳይሰጣቸው በሌለ መስክ ሲሰማሩ ስልጣኑ በወንዶች ቁጥጥር ስር እንዲሆን ተደርጓል፡፡ ህወሓት ጋር ታግለው ስልጣን ላይ ከወጡት ይልቅ ጦር ሜዳ ላይ እያለች የተሰዋችው ቀሽ ገብሩ በርካታ ሰዎች ያውቋታል፡፡

መቼም በህወሓት/ኢህአዴግ የትጥቅ ትግል ከቀሽ ገብሩ ውጭ ሌላ ቆራጥ ታጋይ ጠፍቶ ሊሆን አይችልም፡፡ ይልቁን በህይወት ያሉትን ቀሽ ገብሩዎች ቦታ አልተሰጣቸውም፡፡ ቀሽ ገብሩም ብትሆን ስለሞተች እንጅ በህይወት ብትኖር ይህ ነው የሚባል ቦታ ልታገኝ እንደማትችል አሁን ኢህአዴህ ካለው ተሞክሮ ለመረዳት ቀላል ነው፡፡ በመሆኑም አብዛኛዎቹ ለግንቦት 20 ያደረሱትን ሴቶች እንኳ የሚገባቸውን ክብርና ስልጣን ያልሰጠው ገዥው ፓርቲ የሴቶችን መብት አስከብሬያለሁ ቢል ከተለመደው ፕሮፖጋንዳ ያለፈ አይሆንም፡፡

በተቃራኒ ጎራ የሚገኙት የፖለቲካ ቡድኖችና አጠቃላይ የኢትዮጵያ ሴቶችን ስናይ ደግሞ መሬት ላይ ያለው ተጨባጭ ሁኔታ የተለየ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ኢህአዴግ ስልጣን እንደያዘ ጀምሮ መልካም መልካም የሚባሉትን የዴሞክራሲና የነጻ ገበያ መርሆች አገራችን ህዝብ እንዳይደርሱ ሲከለክል የአገራችንን ባህል የሚጎዳውን ግን በሩን ከፍቶለታል፡፡ በደርግና በኃይለስላሴ ወቅት ሲወገዙና ሲከለከሉ የነበሩ የባህል ወረርሽኞች ኢትዮጵያውያንን እንዲያደነዝዙ በሩ ተከፍቶላቸዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ውስጥ የተስፋፋው ሴተኛ አዳሪነትና ሌሎች የባህል ወረርሽኞች ከግንቦት 20/1983 ዓ.ም በኋላ ኢትዮጵያን መዳረሻቸው ያደረጉ ናቸው፡፡

በፖለቲካው መስክ ያለውን ካየን ደግሞ ይበልጡን የባሰ መሆኑን እንረዳለን፡፡ ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘ በኋላ በርካታ የተቀናቃኝ (ታጣቂም ሆነ ሰላማዊ) የፖለቲካ ቡድኖችን ለማጥፋት ከፍተኛ ጥረት አድርጓል፡፡ ከ40 ሺህ በላይ የሚሆኑ ኦሮምኛ ተናጋሪዎች ‹‹ኦነግ›› ተብለው ታስረዋል፡፡ ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና የሌሎች ቡድኖች አባላት የሆኑ በርካታ ኢትዮጵያውያን እስር ቤት ውስጥ ታጉረዋል፡፡ ከእነዚህ መካከል ሴቶች የሚገኙበት ሲሆን ወንዶቹ ደግሞ ሴት ልጆች፣ ሚስቶችና እናቶችን የሚያስተዳድሩ፣ የሚረዱና የሚያግዙ ናቸው፡፡ በመሆኑም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ አብዛኛዎቹን ሴቶች የሚጎዱ አሉታዊ እርምጃዎችን ከመውሰድ አልተቆጠበም፡፡

በኢኮኖሚው መስክ ሴቶች ተጠቃሚ ናቸው ቢባልም ወደ ውጭ የሚሰደዱት እነሱው መሆናቸው ፕሮፖጋንዳው እርባና ቢስ መሆኑን በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡ ከ18 አመት በታች የሆኑትን ጨምሮ በርካታ ሴቶች ወደ አረብ፣ ደቡብ አፍሪካና ጎረቤት የአፍሪካ አገራት ይጎርፋሉ፡፡ እነዚህ አብዛኛዎቹ እህቶቻችን ህይወታቸውን ለአደጋ አጋልጠው የሚሰደዱት ግንቦት 20 አመጣው የሚባለው ልማት ለእነሱ ጠቃሚ ባለመሆኑ እንጅ አገራቸውን ጠልተው አይደለም፡፡ የሚገርመው ደግሞ ለሴቶች መብት ቆሜያለሁ የሚለው ኢህአዴግ በውጭ አገር ችግር ሲደርስባቸው ‹‹ህገ ወጥ›› አድርጎ የሚፈርጃቸውና ተገቢውን እርዳታ የማያደርግላቸው መሆኑ ነው፡፡

ለዚህ በምሳሌ ልጠቅሰው የምችለው ከሳውዲ አረቢያ ተባረው ወደ ኢትዮጵያ የመጡ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ መንግስት ‹‹ህገ ወጥ›› ተብለው መፈረጃቸውና ለእነሱም ድምጽ ለማሰማት ሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ የወጡ ኢትዬጵያውያን በኢትዬጵያ መንግስት የፌደራል ዱላ የተበተነ ሲሆን ይህ እንደሀገር መደፈራችንን ያየንበት እንደመንግስ ለህዝብ ተቆርቋሪነት ሞራል የጎደለው መሪ እንዳለን የሚያሳየን ነው፡፡ ታዲያ ከሳውዲዎች ጎን ቆሞ ኢትዮጵያውያንን ህገ ወጥ ብሎ የሚፈርጅ መንግስት እንዴት ለሴቶች መብት ቆሜያለሁ ሊለን ይችላል?

ምንም እንኳ ኢህአዴግ በተፈጥሮው ዶክመንተሪም ሆነ ሌላ ነገር አጋንኖ የሚያቀርብ ቢሆንም ቀሽ ገብሩ በዶክመንተሪው ላይ ስትናገር ከነበረው ለመረዳት የሚቻለው ወጣቷ ልክ ጥለውት እንደወጡት ሴቶች ትወጣ ካልሆነ ከኢህአዴግ ጋር አብራ መቆየት እንደማይቻል ነው፡፡ ደርግ ያችን ወጣት በርህራሄ ገድሏል፡፡ በርካቶችን አሰቃይቷቸዋል፡፡ ኢህአዴግ ደግሞ ያንን ስቃይ በዶክመንተሪ እያሳየን የዘመኑን ቀሽዎች ማሰቃየቱን ተያይዞታል፡፡ ለዚህም ባል፣ አባት፣ ልጅና ሌሎች ወንዶች ዘመድ አዝማዳቸው ታስረውባቸው ከሚሰቃዩት በተጨማሪ በዚህ ስርዓት የተሰቃዩት ጥሩ ምሳሌ ይሆኑናል፡፡ በጋዜጠኝነት ሙያ ተሰማርታ ህዝቧን ባገለገለች ወይዘሮ ሰልካለም ፋሲል ከባሏ ከታዋቂው ጋዜጠኛ እና የፖለቲካ ተንታኝ ጋር እስር ቤት ታጉራ እዛው እስር ቤት ውስጥ እንድትወልድ ተደርጋለች፡፡

የሴቶች ብቻ ሳይሆን ለወንዶችም የጥንካሬ ምሳሌ የነበረችው ብርቱካን ሚዴቅሳ ኢህአዴግ በክፉ አይን ከሚያያቸው ሌሎች የወቅቱ ፖለቲከኞችም በላይ በእስር እንድትማቅቅ ተደርጋለች፡፡

በተመሳሳይ በአሁኑ ወቅት እስር ቤት ውስጥ የምትገኘው ርዕዮት አለሙ ግንቦት 20 1983 ዓ.ም ላይ ስልጣን የተቆናጠጠው ኢህአዴግ በሴቶች ላይ እየፈጸመው ለሚገኘው በደልና ግፍ ማሳያ ነው፡፡ ርዕዮት አለሙ ከእጮኛዋ ጨምሮ ከዘመድ አዝማድ እንዳትገናኝ ተከልክላለች፡፡ ጡቷ እየደማ ለብዙ ጊዜ ህክምና መከልከሏ ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ትውልድም ከቀሽ ገብሩ የማይተናነሱ በርካታ ቆራጥ ሴቶች ለአገራቸው ዴሞክራሲ ራሳቸውን መስዋዕት እያደረጉ ነው፡፡ ደርግ ቀሽ ገብሩን አሰቃይቶ ገድሏታል፡፡ ኢህአዴግ ስልጣን ከወጣ በኋላ በርካታ ከቀሽ ገብሩዎች የሚገባቸውን ቦታ ሳያገኙ ወንዶቹ ስልጣኑን ተቆጣጥረውታል፡፡ እነዚህ
የድሮዎቹ ቀሽ ገብሩዎች እንደ ሌላው የኢትዮጵያ ሴቶች አበሳቸውን እየበሉ ነው፡፡

በተቃራኒው ጦር ሜዳ ላይ ያልነበሩት በዝምድና፣ በውሽምነት፣ በሚስትነት…..የማይገባቸውን ጥቅም አግኝተው ከስርዓቱ ቁንጮ ወንዶች ጋር ሌሎች ሴቶችን በማስበደል ላይ ናቸው፡፡ አዜብ መስፍንን በምሳሌነት ባነሳ የምሳሳት አይመስለኝም፡፡ የወቅቱ ቀሽ ገብሩዎች ላይ የሚደርሰው ደግሞ ከሁሉም የባሰና መሪር ነው፡፡ በእነ ርዕዮት ላይ የሚፈጸመው አሁን በእነ በዞን ዘጠኝ ጦማሪ ሴቶችና በጋዜጠኞቹ ላይ ተከትሏል፣ ከ1960ዎቹ ትውልድ ቀጥሎ ትልቅ የሴቶች የፖለቲካ ተሳትፎን ያየንበት የሴቶች ቀን (march 8) በ ሴቶች ታላቁ ሩጫ ላይ አጋጣሚውን ተጠቅመው ድምፃቸውን ከፍ አድርገው በስርአቱ የመጀመርያ ተጠቂዎች ሴቶች እንደሆኑ ፣ነፃነትን እንደሚሹ ፣ ፍትህ የሰፈነባት ኢትየጵያን እንሻለን፣የአባቶቻችን ልጆች ነን፣የጣይቱ ልጆች ነን፣የአባ ጅፋር ልጆች ነን አታስደፍሩን በማለት የቀዘቀዘውን የሴቶች የትግል ተሳትፎ በአንድ እርምጃ ለመቀጠል ባደረጉት እንቅስቃሴ የመንግስት አፀፋ የጣይቱ ልጆች ነን፣ የሚኒልክ ልጆች ነን አሉ በሚል ክስ ለ 11 ቀናት አስሮ እንደፈታቸው የሚታወስ ነው፡፡

በጣም የሚገርመው ግን እነሱ የማን ልጆች እንደሆኑ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያሳዩበት ትይንት ነው፡፡ ይህን ሁሉ የሚያሳየን ግንቦት 20 ለሴቶች ተጠቃሚነትን ሊያመጣ ቀርቶ ለአገራቸው ማበርከት የሚችሉትንም እንዳጠፋቸው የሚያስረዳ ነው፡፡

ኢትዮጵያ በክብር ለዘለአለም ትኑር!!!

(ይህ ፅሁፍ የዛሬ ዓመት በነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ላይ ታትሞ የወጣ ፅሁፍ ነው)

ግንቦትና ግንቦታውያን

– ከጌታቸው ሽፈራው
ግንቦት በሞቃታማው በጋ እና በክረምቱ መካከል የሚገኝ የሙቀትና የወበቅ ወር ነው፡፡ ይህ ወር አየር ንብረቱ በቅጡ የማይታወቅ፣ ሙቀትና ቅዝቃዜ የሚፈራረቅበት እንደመሆኑ ለሰዎች ጤና ተስማሚ አይደለም፡፡ ሙቀትና ቅዝቀዜው ድብልቅልቅ ባለበት በዚህ ወር አብዛኛው አርሶ አደር በበሽታ ይጠቃል፡፡ በዝናብ እጥረትና በረዥሙ በጋ ምክንያት ከብቶቻቸው ያልቃሉ፡፡ በአጠቃላይ ግንቦት ለአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የመከራና የስቃይ ወር ነው፡፡
mengistu hailemariam
ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ወሩን መልካም ነገር ይዞ እንዲመጣ አምላካቸውን ይማጸናሉ፡፡ ለአብነት ያህል ክርስቲያኖችና የሌሎች እምነት ተከታዮችም የግንቦት ልደታ ዕለት (አብዛኛዎቹ ከእምነት ይልቅ አምልኮ አዊ ያደርጉታል) ንፍሮ አንፍረው፣ ቡና አፍልተው የግንቦት ወር ጦስ በጭስና በንፍሮ ውሃ ለመሸኘት ይጥራሉ፡፡ ሆኖም ግን ለኢትዮጵያውያን ግንቦት የመከራ ዘመን፣ የደም ወር ከመሆን አላለፈም፡፡ ከዚህ ወር ጦሶች መካከል ለአሁኑ ዘመን መከራ ምንጭ የሆኑትን ግንቦታዊ ክስተቶች ብቻ እጠቅሳለሁ፡፡

26 አመታትን ወደኋላ ስንመለስ ኢትዮጵያ ለአሁኑ ፖለቲካዊ፣ ጂኦ ፖለቲካዊና ሌሎች አሉታዊ ገጽታዎች የዳረጋትን ውጥንቅጥ እናገኛለን፡፡ ግንቦት 8/1981 ዓ.ም፡፡ ይህ ወቅት የኢትዮጵያ ወታደሮችና አመራሮቻቸው በጦርነት የተማረሩበት ወቅት ነበር፡፡ ከጀኔራሎቹም በላይ በእነ መንግስቱ ኃይለማርያም ይሁንታን ያገኘ ካድሬ ስለ ወታደራዊ ስትራቴጅ ለመተንተን የሚቃጣበትና ጀኔራሎቹን ያማረረበት ወቅት እንደነበር በርካቶች እማኝነ ታቸውን ይሰጣሉ፡፡ በገፈፋና በግድ ጦር ሜዳ ይቀላቀሉ የነበሩ ወታደሮች በቁርጠኝነት ይዋጋ የነበረውን ሰራዊት መንፈስ ቀይረውታል፡፡ ይህ ሁሉ ውጥንቅጥ ያሳሰባቸው የጦሩ መሪዎች ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም ከስልጣን ካልተወገዱ ኢትዮጵያ የገባችበት ችግር ሊፈታ እንደማይችል አመኑ፡፡ ‹‹በጓድ መንግስቱ ኃይለማርያም›› ላይ ይሞከራል ተብሎ የማይታሰበውን መፈንቅለ መንግስትም ወጠኑ፡፡ አዲስ አበባና አስመራም የመፈንቅለ መንግስት መሪዎቹ ማዕከል ሆኑ፡፡ ሆኖም የአዲስ አበባው ማታ ላይ እንዲሁም አስመራው ደግሞ ከአንድ ቀን በኋላ ግንቦት 8/1981 ዓ.ም ከሸፈ፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ ሙከራውን ያደረጉት ጀኔራሎች ራሳቸውን ገደሉ፣ ተገደሉ፣ ታሰሩ፡፡ አስመራ ላይ ደግሞ ግንቦት 9 የ102ኛ አየር ወለድ ክ/ጦር በምስራቅና በሰሜን የገጠማትን ጦርነት ሲመሩ የኖሩትን ጀኔራሎች ዓይናቸ ውን ጎልጉሎ፤ በየጎዳናው እየጎተተ፣ አንገታቸውን ቆርጦ ብቻ ወታደር በመሪዎቹ ላይ ብቻ ሳይሆን ጠላት በማረካቸው ላይ ሊያደርገው በማይታሰበው አረመኔያዊ ድርጊት አስመራን የደም አላባ አደረጋት፡፡ በመፈንቅለ መንግስት በአጠቃላይ ከ137 በላይ የጦሩ አመራሮች ታሰሩ፡፡ ከእነዚህ መካከልም 28 ጀኔራሎች፣ 20 በላይ ኮሎኔሎች፣ 20 በላይ ሻለቃዎች፣ 20 በላይ ሻምበሎች ይገኙበታል፡፡ ገንጣይ አስገንጣይ የሚባሉት ሳይቀሩ አንዳንዶቹ ‹‹የኢትዮጵያ መንግስት ቀኝ እጁን በግራ እጁ ቆረጠ!›› ሲሉ ሌሎቹ ደግሞ ‹‹ኢትዮጵያ የጦር መሃንዲሶቿን ገደለች፣ በላች›› ብለው ጽፈውታል፡፡ በዚህ ምክንያት 270 ሺህ ያህል ኤርትራ ውስጥ የነበረው ሰራዊት አመራር አልባ ሆነ፡፡

መፈንቅለ መንግስቱ በከሸፈ በሁለተኛው ቀን ግንቦት 10 በርካታ የኢትዮጵያ ሰራዊት አመራሮች ሲገደሉ፣ ሲታሰሩና ከጦሩ ሲርቁ እንዲሁም ሰራዊቱም ሆነ አመራሩ ሞራሉ ሲላሽቅ ሻዕቢያና ህወሓት የኢትዮጵያን ሰራዊት ይዞት የነበረውን ሰፊ መሬት ማስለቀቅ ጀመሩ፡፡ ይህ ወቅት የኢትዮጵያ ሰራዊት እንደ ውጭ ወራሪ ያለ ርህራሄ የተጨፈጨፈበት ጊዜ ነው፡፡ ህወሓትና ሻዕቢያ የተማረከውን ሰራዊት ሳይቀር መሬት ላይ አስተኝተው በመድፍ ጨፍልቀውታል፡፡ ቁስለኛውን በጅምላ ሲፈልጉ ወደ ገደል፣ ሲፈልጉ ወደባህሩ አሊያም በጅምላ የጨፈጨፉበት ወቅትም ነው፡፡ ይህ ወር ኤርትራና ትግራይ በኢትዮጵያ ሰራዊት ደም የጨቀየበት ክፉ ቀን ነው፡፡
ይህ ግንቦት ያመጣው ጦስ የኢትዮጵያውያን እጣ ፈንታ በገንጣዮቹ እጅ እንዲወድቅ አደረገ፡፡ መንግስቱ ኃይለ ማርያም ለኢትዮጵያ አንድነት ‹‹አንድ ጥይትና አንድ ሰው›› እስኪቀር እንደሚዋጉ ቃል ገብተው እንደነበር ይነገራል፡፡ በእርግጥ እርሳቸው ብቻ ሳይሆን ሌሎችም መንግስቱ ኃይለማርያም ኢትዮጵያን ጦርነት ውስጥ ዘፍቀው መሸሸት እንደሌለባቸው በአደባባይ ነግረዋቸዋል፡፡ ለአብነት ያህል በመጨረሻው ሸንጎ አንድ የሀይማኖት መሪ መንግስቱ ኃይለማርያም አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱትን ሀገርና ህዝብ ጥለው መሄድ እንደሌለባቸው በግልጽ እንዲህ ብለዋቸው ነበር፡፡ ‹‹….50 ሚሊዮን ህዝብ በጦርነት ባህር ማግደው፣ ቆስቁሰው፣ በእርስዎ ኃላፊነት 18 ዓመት ሙሉ መርተው ሳያደራድሩ፣ ሳያረጋጉ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ለእሳት ዳርገው፣ በአሁኑ ሰዓት ከመሞት በስተቀር፣ የቴዎድሮስን ጽዋ ከመጠጣት በስተቀር፣ ሌላ እድል የለዎትም፡፡ እንደሌሎች መሪዎች ኢሮፕ ይፈረጥ ጣሉ ብዬ እምነት የለኝም፡፡ እግዚያብሄር ምስክሬ ነው፡፡ ይህን ህዝብ አጋልጠው ይሄዳሉ አልልም፡፡ መንጌ፤ ከሷ ወንበር ላይ እንደቋንጣ ደርቀው እንደሚቀሩ አምንብዎ ታለሁ፡፡ ይህንን ባያደርጉ ግን ታሪክ ይፋረድዎታል፡፡››
በዚያ የሀይማኖት መሪዎች ስለ እውነት ይናገሩ በነበረው ወቅት ከንግግራቸው ሁለት የግንቦት ጦሶችን በግልጽ እንረዳለን፡፡ አንደኛውና ዋነኛው ፕሬዝደንት መንግስቱ የፈጠሩትን ቀውስ ‹‹….50 ሚሊዮን ህዝብ በጦርነት ባህር ማግደው፣ ቆስቁሰው፣ በእርስዎ ኃላፊነት 18 ዓመት ሙሉ መርተው ሳያደራድሩ፣ ሳያረጋጉ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ለእሳት ዳርገው፣›› ሲሉ ስለ ቀውሱ በግልጽ ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ‹‹ይህን ህዝብ አጋልጠው ይሄዳሉ አልልም፡፡›› ሲሉ ህወሓትና ሻዕቢያ ለኢትዮጵያ ህዝብ ምን ያህል ጠላት እንደሆኑ በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡
meles zenawi
ግንቦት 13/1983 ከቀኑ 6 ሰዓት ላይ ‹‹ጓድ ሊቀመንበር››ን አሞካሽቶ የማይጠግበው ሚዲያ ‹‹ጦርነቱ ያስከተለውን ሁኔታ እንዲለወጥ በልዩ ልዩ ወገኖች በልዩ ልዩ መልክ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፡፡ ሆኖም ችግሩ አልተቃለለም፡፡ ስለዚህ ደም መፋሰስ እንዲቆም፣ ስምምነት እንዲሰፍን በልዩ ልዩ ወገኖች የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃ/ማርያም ከስልጣን መውረዳቸው እንደሚበጅ የታመነበት ስለሆነ ይህንኑ በማመዛዘን ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃ/ማርያም በዛሬው ዕለት ከስልጣን ወርደው ከኢትዮጵያ ውጭ ሄደዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ ከስልጣን በመውረድ ሀገር ለቀው በመሄዳቸው የሪፐብሊኩ ም/ፕሬዘዳንት ሌፍትናንት ጀኔራል ተስፋዬ ወ/ኪዳን ተክተው ይሰራሉ፡፡›› ተባለ፡፡
‹‹ከመንግስቱ ኃይለማርያም አመራር ጋር ወደፊት!›› ይል የነበር ካድሬ ደግሞ ጆሮው ሊቀበለው የማይችለውን ነገር ሰማ፡፡ ለመንግስቱ ኃይለማርያም ቆሞ አመራሮቹን በጭካኔ ያረደው፣ በጭካኔ ዓይና ቸውን ያወጣውንና አስከሬናቸውን በአስመራ ጎዳና የጎተተው የ102ኛ ሰራዊት የመጨረሻው ተስፋውን ቆረጠ፡፡ ‹‹መንጌ!›› ሲል የነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ እጣ ፈንታው ‹‹ገንጣይ አስገንጣይ›› ሲባሉና ኢትዮጵያን ሊገነጥሉ ሲታገሉ በኖሩት ሻዕቢያና ህወሓት ስር ሆነ፡፡ ሻዕቢያና ህወሓት በሚጠሏት ኢትዮጵያ ላይ የሚፈነጩበት መንገድ ወለል ብሎ ተከፈተ፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ ጦሰኛ ግንቦት ወር አደጋ ውስጥ ገባች፡፡ ይባስ ብሎ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያምን የተኩት ተስፋዬ ወልደኪዳን መንግስቱ ጥሎ ከወጣበት ከሁለት ቀን በኋላ የኢትዮጵያ ጦር መሳሪያውን ለ‹‹ወንበዴ›› አስረክቦ ወደ ፈለገበት ቦታ እንዲሄድ አዋጅ አስነገሩ፡፡ ለአንድነት ሲዋጋ የኖረው ሰራዊትም መሳሪያውን እየጣለ ወደየትውልድ ቦታውና ወደ ከተማው ሲያቀና ለህወሓትና ሻዕቢያ እንዲሁም በደርግ ለተማረረው አርሶ አደር ጥይት ሰለባ ሆነ፡፡ እንደ ምንም ብሎ ህይወቱን ያተረፈው ደግሞ በዚህ ደሙን ባፈሰሰላት አገር ጎዳና ላይ ወደቀ፡፡

ሰራዊቱ ትጥቁን እንዲፈታ በጊዜያዊ ፕሬዝደንቱ መጠየቁን ተከትሎ ሻዕቢያ በወቅቱ ሁለተኛዋ የኢትዮጵያ ከተማ የነበረችውን አስመራን ተቆጣጠረ፡፡ አረመኔዎቹ የሻዕቢያ ታጋዮች ኢትዮጵያውያንን እንደ ወራሪ ጠላት መዓት አወረዱባቸው፡፡ ህወሓት ኢህአዴግ ከአራት ቀን በኋላ ግንቦት 20 አዲስ አበባን ተቆጣጠረ፡፡ ደርግ መሸነፉን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ይህ ወር መልካም ነገር ይዞ ይመጣል ብለው ቢጠብቁም ያመጣው ግን ተቃራኒውን ሆነ፡

ግንቦት 20… ጥቁሩ ቀን

በግንቦት ወር የመጀመሪያ ቀናት ሻዕቢያና ህወሓት አሜ ሪካን ጨምሮ ከምዕራባውያን መንግስታት ጋር ሎንደን ውይይት አድርገው ነበር፡፡ ከዚህ ውይይት ዋና ጭብጥ መካከል አንዱ ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል በሚል ከምዕራባዊያኑ በተለይም ከአሜሪካ የተነሳው ሀሳብ ነበር፡፡ ይሁንና መለስ ዜናዊ ኢትዮጵያ የባህር በር እንደማያስፈልጋት ሽንጡን ገትሮ በመከራከር ምን አል ባትም ‹‹ለማስተዳደር›› በሚፈልጋት አገር ሉዓላዊነትን አሳልፎ የሰጠ የመጀመሪያው መሪ የሚያደርገውን ከሃዲነት ፈጸመ፡፡ ግንቦት 21 ቀን ኤርትራ በሻዕቢያ ስር መተዳ ደር ጀመረች፡፡ ያ የተደከመበት፣ በርካታ የሰው ነፍስ የጠፋበት ሉዓላዊነት ግብጽ ጀምራው እነ ሶማሊያ፣ ሱዳንና ሌሎች የአረብ አገራት ትኩስ ስንቅ እየቋጠሩላቸውና የደርግም ስህተት ተጨምሮበት በአገር አንድነት ላይ በተ ነሱት ‹‹ወንበዴዎች›› የበላይነት ተጠናቀቀ፡፡ ሉዓላዊነቷ ተደፈረ፡፡

ህወሓትና ሻዕቢያ ስልጣን ከመያዛቸው በፊትም ጀምረው ተሻርከው እንጨት፣ ብረት፣ ቡና፣ ወርቅ፣ ብር፣ ሳይሉ ያገኙትን የኢትዮጵያን ሀብትና ንብረት መዘበሩ፡፡ ከደርግ ጋርም ሆነ ካለፉት ስርዓት ጋር ግን ኙነት አለው ያሉትን ህዝብ ላይ እስራት፣ ግድያና ሌሎች አሰቃቂ እርምጃዎችን ወሰዱ፡፡ እርግጥ ነው ይህ ተባብሮ ኢትዮጵያን የመመዝበር ተግባር በስምምነት አልዘለ ቀም፡፡ ሁለቱ የኢትዮጵያን ምጣኔ ሃብት ለማጋበስ በመ ነበራቸው አለመግባባት እርስ በእርስ መነካከስ ጀመሩ፡ ፡ በዚህ የሁለት ጅቦች ጠብ ምክንያትም ህወሓት የሚ ገዛት ኢትዮጵያ ግንቦት 4/1990 ዓ.ም በሻዕቢያ ተወረ ረች፡፡ በሁለቱ ግለሰቦች፣ ፓርቲዎች ኢኮኖሚያዊና ድሮ ኢትዮጵያን ለመገነጣጠል በርሃ በነበሩበት ወቅት በተፈ ጠረ ቁርሾ 70 ሺ ያህል ህዝብ በዚህ ወርሃ ግንቦት በተፈ ጠረ ግጭት ሰበብ ውድ ህይወቱን አጣ፡፡ በዚህ ግጭት ምክንያት በርካታ ኢትዮጵያውያን ጥርሳቸው ሳይቀር እየ ተነቀለ ከአስመራ ተባረሩ፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግም ቢሆን ያ አብዛኛውን ተግባሩን ካስተማረው ሻዕቢያ በቀሰመው ተሞክሮ መሰረት ምላሹን ሰጠ፡፡
ህወሓት/ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘ በኋላ እርዳታ ለመ ለመን እከተለዋለሁ ካለው የይስሙላ ዴሞክራሲ ስም አፋኝነቱን ያሰፈነ ድርጅት ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ጥቅም ይልቅ የራሱንና የሻዕቢያ ጥቅም አስቀድሟል፡፡ ኢትዮጵ ያውያንን በዘውግ ከፋፍሎ መግዛትን እንደዋነኛ ስልት ወስዶታል፡፡ የይስሙላህ ዴሞክራሲና ምርጫ አሰፈንኩ ቢልም ከመግዢያነት ያለፈ ግን አልነበረም፡፡ ለዚህም ህወሓት/ኢህአዴግ ስቃይ እያደረሰበት የሚገኘውን ህዝብ ጥላ ለመሆን በህገ መንግስቱ መሰረት የተቋቋሙት ፓርቲዎችና ፖለቲከኞቻቸው የደረሰባቸውን መከራ ማንሳት በቂ ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል በየክልሉ ኦነግና ህወሓት/ኢህአዴግ ሲጨፈጭፉት የነበረውን ኢትዮጵያ ዊና የኢትዮጵያ አንድነት ለመታደግ የተነሳው መዐሕድ የመጀመሪያው ተጠቂ ነበር፡፡ የዚህ ፓርቲ መስራችና
እውቁ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ደግሞ የዚህ የግንቦት ዘራሽ አምባገነን ስርዓት ዋነኛ ተጠቂ ናቸው፡፡ ፕሮፌሰሩ እስር ቤት ሲማቅቁ ቆይተው ግንቦት 1/1991 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ የሚገርመው መንግስቱ ኃይለማርያም እና ውጫዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች በከፈቱላ ቸው ቀዳዳ በግንቦት ነፋስ ወደ ስልጣን ብቅ ያሉትና የአሁኑ ስርዓት ‹‹መሃንዲስ›› መለስ ዜናዊም በዚሁ የደም ወር እውቁ ፕሮፌሰር ተሰቃይተው በሞቱበት ቀን የተወ ለዱ መሆናቸው ነው፡፡ ፕሮፈሰሩ ከሞቱ በኋላ የመዐሕድ አካል የነበሩም ሆነ ሌሎች የፖለቲካ ኃይሎች በ1997 ተጠናክረው በአዲስ ምዕራፍ ለትግል የመጡበት ዘመን ነበር፡፡ በተለይ የግ ንቦት 1997 ምርጫ ኢትዮጵያውያን ካሉበት አምባገነ ናዊ አገዛዝ ነጻ እንዲሚያወጣ በኢትዮጵያውያኑ ብቻ ሳይሆን ህወሓት/ኢህአዴግ ለኢትዮጵያ፣ ለቀጠናውና ለዓለምም እንደማይመጥንና እንደማይበጅ በተረዳው ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ዘንድ ተስፋ ተጥሎበት ነበር፡፡ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ ነጻ ለመውጣት በሙሉ ልብ ወደ ምርጫ ጣቢያ የጎረፉ ትም በዚህ ቀን ነው፡፡ የሚያዝያው ሰልፍና ሌሎች መነ ቃቂያዎች ግንቦት 7 ኢትዮጵያውያንን ነጻ የምታወጣ ቀን አስመስሏታል፡፡ እነዚያ ንፍሮ ቀቅለው፣ ቡና አፍል ተው ግንቦት ክፉውን ይዞ እንዳይመጣ ተስፋ ሳይቆረጡ ሲልምኑ የኖሩት ኢትዮጵያውያን አሁን አዲስ ተስፋ ሰንቀዋል፡፡ ተስፋው ከአንድ ቀን በላይ አልዘለለም እንጂ፡፡

ተቃዋሚ አጣን ሲሉ የነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ማታ ላይ ብቅ ብለው ይህን የግንቦት 7 ተስፋ አቧራ ነሰነሱበት፡፡ ማታ በኢቲቪ ብቅ ብለው አሁንም ድረስ ኢትዮጵያውያንን ለቀየደው የጸረ ሽብር፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የሚዲያ…..ሌሎች ቀያጅ አዋጆች መሰረት የሆነውን ጊዜያዊ አዋጅ አወጁ፡፡ በነጋታው ግንቦት 8/1997 ህዝብ ከቤት ውጭ ምንም አይነት ስብሰባም ሆነ እንቅስቃሴ እንዳያደርግ ተከለከለ፡፡ በዚሁ ቀን ‹‹አብዮታዊ›› ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ምንም ባላሳወቀበት ግንቦት 8 ከአዲስ አበባ ውጭ በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ማሻነፉን በተቆጣጠረው ሚዲያ አሳወቀ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የሰላማዊ ትግልን የቀፈደዱ በርካታ እርምጃዎች በዚሁና በቀጣዩ ግንቦቶች ተወስደዋል፡፡ ግንቦት 2002 ዓ.ም ምርጫ ደግሞ አፋኝነቱን ያጠናከረው ኢህአዴግ አስፈራርቶም፣ አጭበርብሮም 99.6 በመቶ አሸንፎ ‹‹አውራ ነኝ›› ያለበትን ኢትዮጵያውያንን በገዥነት እንደሚቀጥል ያቀደበት ወቅት ሆነ፡፡ ባለፉት 5 አመታት ፖለቲከኞችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ፖለቲካውን ያነቃቃሉ ብሎ የፈራቸውን ብሎገሮች አስሮ፣ ህዝቡን 1ለ5 ጠርንፎ፣ እና አጭበርብሮ የዘንድሮውን ምርጫ 100 በ100 እንዳሸነፈ እየተነገረ ነው፡፡ በእርግጥ በተለይ ከ1997 በኋላ አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን ኢህአዴግ የሚወዳደሩት ሳይሆን የሚታገሉት እንደሆነ በማመናቸው ምርጫውን 90፣99.6፣ 100 አሸነፍኩ ቢል የሚገርማቸው አይደለም፡፡ ያም ሆኖ ግን ግንቦት ለኢትዮጵያውያን የመከራ ወር እንደሆነ ቀጥሏል፡፡

በአጠቃላይ ግንቦት 20 ህወሓት/ኢህአዴግ ሳይገባው፣ ለኢትዮጵያውያን ሳያስብና ኢትዮጵያዊ ሳይሆን ኢት ዮጵያን የተቆጣጠረበት፣ በኢትዮጵያውያን ላይ ፕ/ር መስፍን እንደሚሉት ‹‹ህገ አራዊት›› መተግበር የጀመረበት፣ ዓለም አንድ በሆነችበት ወቅት መገንጠልን በወርቃማ መብትነት ያጸደቀበት፣ ኢትዮጵያውያን አገራ ቸው ውስጥ እንዳይዘዋወሩ የማንነት ግንብ የገነባበት ጥቁር ቀን ነው፡፡ በተለይ ከኢትዮጵያዊ አላማ ያፈነገጠ መሆኑ፣ ኢትዮጵያው ያንን በስስ ማንነት መከፋፈሉ፣ ለራሱ ቡድናዊ ጥቅም መሯሯጡ ህወሓት/ ኢህአዴግ አዲስ አበባን የተቆጣጠረበትን ቀን ለኢትዮጵያውያን ጨለማ፣ አዲስ የጭቆና ዘመን ነው፡፡ ይህን ቀን ምናልባትም የጀርመኑ ሂትለር ለቤልጀም ሳይሆን ለራሱ የስልጣንና ልሂቃን ጥቅም፣ በበላይነት ተወጥሮ ቤልጀምን ከወረረበት የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ግንቦት 1940 ተመሳሳይ ወቅት (ግንቦት 20) ጋር ማመሳሰል ይቻላል፡፡ እንዲያውም ናዚዎቹ የጀርመንን ጥቅም ለማስጠበቅ፣ ቤልጀምን ሰጥ ለጥ አድርገው ለመግዛት ግልጽ አላማ ይዘው ነው የገቡት፡፡ ህወሓት ግን እስካሁንም ድረስ፣ ለባለፉት 23 አመታት የሚጠላትን አገር የገንጣይ ስምና አላማውን እንዳነገበ እየገዛት ይገኛል፡፡ አሁንም ድረስ ኢትዮጵያውያን ንፍሮ አንፍረው፣ ቡና አፍልተው ‹መከረኛውን› አምላካ ቸውን መለመናቸው ቀጥለዋል፡፡ ግንቦት የሰጠው ‹‹አብ ዮታዊ›› ፓርቲ ግን በከፍፍለህ ግዛ፣ በስራትና ግርፋት፣ በኑሮ ውድነት፣ በመሰረታዊ አገልግሎት እጥረት፣ በሙስና ኢትዮጵያን የመከራ ምድር አድርጓታል፡፡ ግንቦት ደግሞ በአየር ንብረት ብቻ ሳይሆን በፖለቲካ ውም ውጥንቅጡ የወጣ ክፉ ወር ሆኖ ቀጥሏል፡፡ ይህም ነው ግንቦት አሁንም የህወሓት/ኢህአዴግ እንጂ የኢት ዮጵያውያን ወር አይደለም ለማለት የሚያስደፍረው፡፡

(ይህ ጽሁፍ ከመጠነኛ ማስተካከያ ውጭ ግንቦት 15/2006 ዓ.ም ነገረ ኢትዮጵያ ላይ የወጣ ነው)

– See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41779#sthash.9BNwT974.dpuf

የዛሬ 24 ዓመት ኢህአዴግ አዲስ አበባን ባይቆጣጠር ኖሮ ዛሬ የኢትዮያ እድገት ከብራዚል ጋር ይስተካከል ነበር

(የጉዳያችን ማስታወሻ)

ደርግ 17 ዓመታት ሙሉ በህወሓት እና ሻብያ የተከፈተውን ጦርነት ሲዋጋ እንደነበር እና ጦርነቱ በቀን ብቻ በሚልዮን የሚቆጠር ብር ያስወጣ ነበር።በመቶሺዎች የሚቆጠር ሰራዊት መግቦ፣ታንክ እና ብረት ለበስ ተሽከርካሪ ነዳጅ
እና ግዥ ፈፅሞ ማደር በራሱ ከፍተኛ ወጪ ነበር።ይህ ገንዘብ እንዳሁኑ የእርዳታ እና የብድር ገንዘብ ሳይሆን ህዝቡ ለእናት ሀገር እያለ ከሚያዋጣው እንደነበር ይታወቃል።በእርግጥ የሩስያ እርዳታ እና ብድር እንዳለ ሆኖ።
addis-ababa-realethiopia-141
በአንድ ወቅት ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማርይም የሰሜኑ ጦርነት ባይኖር በጥቂት አመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምዕራብ እስከ ምስራቅ በባቡር ማገናኘት በተቻለ ነበር።ሲሉ መደመጣቸው ይታወሳል።በተለይ ህወሓት በዋነኛነት ድልድዮች እና መንገዶችን ማፍረስ ስራዬ ብሎ ይዞ ስለነበር እነርሱን ተከታትሎ መጠገን ሌላው ሥራ ነበር።የመከላከያ ኮንስትራክሽን ድርጅት (መኮድ) የተሰኘው ድርጅት አንዱ ስራው ህወሓት ያፈረሰውን
ድልድይ እና መንገድ መልሶ መጠገን ነበር።

በደርግ የመጨረሻ አመታት ታድያ ኮ/ል መንግስቱ የመንግስታቸውን ቅርፅ ለመቀየር ወስነው ነበር።ቅይጥ ኢኮኖሚ ታወጀ።ሚኒስትሮች በአዲስ መልክ ተሾሙ።ብዙዎቹ በምዕራብ ዓለም የተማሩ ነበሩ።ኢኮኖሚውም ሆነ ፖለቲካው ለቀቅ ያለ መስሎ ነበር።በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው የመመለስ ዕድል እንዳላቸው ምህረት እንደሚደረገም ተወራ።ፕሮፌሠር መስፍን ወ/ማርያምን ጨምሮ ሌሎች ምሁራን ከአመታት በኃላ እንደገና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን የማናገር፣በሀገሪቱ መፃኢ ዕድል ላይ የመነጋገር ዕድል አገኙ።

በወቅቱ በተያዘው መልክ የሀገሪቱ ሰላም ቢረጋጋ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ የህወሃትን የጎሳ ፖለቲካ እና የሻብያ ኤርትራን የመገንጠል አጀንዳ እንደመጥላቱ በነበረው ሕብረት ቢቀጥል ኖሮ፣በውጭ ይኖር የነበረው ሕብረተሰብ ወደሀገር ቤት ገብቶ የመስራት፣በሀገር ውስጥ ያለው ካለ ምንም የጎሳ ክፍፍል የመስራት እና ትላልቅ ኩባንያዎችን የመመስረት እድሉ ሰፊ ነበር። ዛሬ ኤፈርት እና ጥቂት ባለ ሀብቶች የሃገሩትን ሀብት ሁሉ እንዲህ ጠቅልለው ሚልዮን ኢትዮጵያውያን በድህነት ውስጥ አይዳክሩም ነበር።

አሁንም በተጀመሩ የሽግግር ሂደት ደርግ ስልጣኑን ቢለቅ እና የሽግግር መንግስት ተመስርቶ ቀጥሎም ወደ እውነተኛ ምርጫ ኢትዮጵያ ሄዳ የእራሷ የሆነ መንግስት ቢኖራት ኖሮ ዛሬ ከ 24 ዓመታት በኃላ ኢትዮጵያ ካለምንም ጥርጥር ብራዚል ከደረሰችበት የእድገት ደረጃ የመድረስ ዕድል ነበራት።እዚህ ላይ ብራዚል ቀደም ብላ በውጭ ኃይሎች የመገዛቷ እና በርካታ የባህል ተቃርኖ ቢኖርም እኛ ካለን የባህል ሀብት ጋር በምጣኔ ሀብት ደረጃ እና በፈጠራ እንዲሁም በአዲስ ቴክኖሎጂ ክህሎት ሁሉ በእጅጉ የምንራመድበት የመነቃቃት አመታት ነበሩ።በእነኝህ 24 አመታት ውስጥ ከተባለው ደረጃ ለመድረስ እንችል እንደነበር እንደማሳያ የምረዳኝን ኢትዮጵያ ሊኖሯት እና ላይኖሯት የሚችሉት ነገሮች ሁለት ክፍል ከፍዬ ለማሳየት እና እነኝህ ጉዳዮች ማለትም ኢትዮጵያ ሊኖሯት የሚችሉት ነገሮች ምን ያህል ወደፊት እንደሚያራምዱን እና ላይኖሩ የሚችሉት ደግሞ ምን ያህል ወደኃላ እንደወሰዱን ለመመልከት ይረዳናል።እነኝህን ነጥቦች ለመንደርደርያ አነሳሁ እንጂ ጠለቅ ያለ ጥናት ቢደረግ ብዙ ጉዳዮችን ሊያሳየን እንደሚችል መረዳት ይቻላል።
ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ዓመታት ውስጥ ሊኖሯት የሚችሉት
eth Bank
1/ የባንክ ኢንዱስትሪያችን ቢያንስ በ 5 የአፍሪካ ሁለት የመካከለኛው ምስራቅ እና አንድ አውሮፓ እንዲሁም 3 በአሜሪካ ቅርንጫፍ ከፍተው ግዙፍ የፋይናንስ ተቋም በሆኑ ነበር፣

2/ እነ ጣና በለስ የመስኖ ልማት በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ ሞደል የተባለ ምርቶቹ ከኢትዮጵያ አልፈው ለመላው ዓለም የሚልክ በአውሮፓ የስቶክ ኤክስቸንጅ ገበያ የሚገባ ኩባንያ ይሆን ነበር፣

3/ ኢትዮጵያ ከሻብያ ጋር በኤርትራ ጉዳይ ባትግባባ ቢያንስ በአሰብ ጉዳይ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተደራድራ ወደቧን ታስከብር ነበር።በሌላ በኩል እንደ ህወሓት በመሃል ሀገር የሚኖሩ ትውልደ ኤርትራውያንን ከሀገር ስለማታስወጣ በሂደት እነኝሁ ትውልደ ኤርትራውያን የኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር አብሮ መኖር ሽንጣቸውን ገትረው የሚከራከሩ በሆኑ ነበር።እዚህ ላይ በደርግ ዘመን ከፍተኛ ተደማጭ የነበሩ የኤርትራ ቆላው ተወካዮች የነበራቸውን ተሰሚነት ማሰብ ይገባል።እነኝህ ሁሉ በህወሓት ስሳደዱ እና ሲገፉ 24 ዓመታት ተቆጠሩ።

4/ ኢትዮጵያ የመከላከያ ኃይሏ ጠንካራ ስለነበር በደቡብ ሱዳን ጉዳይም ሆነ የሱማልያ አልሸባብ ፈፅሞ ስጋት ሊሆኑ አይችሉም ይልቁንም በአካባቢው ሃያል ሀገርነቷ እስከ ግብፅ እና መካከለኛው ምስራቅ ድረስ ይናኝ ነበር።የአይኤስ ኤስ ጥቃት መፈፀሙ በተሰማ በ24 ሰዓታት ውስጥ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከደብረ ዘይት ተነስተው የሱዳንን የአየር ክልል ጥሰው በርካታ የአሸባሪው ይዞታዎችን ሊብያ ውስጥ ያጠቁ ነበር።በእዚህም ሌሎች ተቀናቃኝ ሀገሮችን ሊያስደምም ይችል ነበር።

5/ በጦርነት ውስጥ የነበረ ኢኮኖሚ ያንን ያህል የስራ ዕድል ለወጣቱ መፍጠር ከቻለ ከጦርነት በኃላ ላለፉት 24 ዓመታት ውስጥ ቢያንስ ከ አስር ያላነሱ ከባድ የብረት ኢንዱስትሪዎች፣የነዳጅ ማውጣት ሥራ (ሱዳን ባቅሟ ነዳጅ ስታወጣ ኢትዮጵያ በሙስና ያልባለገ መንግስት ቢኖራት ኖሮ እስካሁን የነዳጅ ምርት በጀመረን ነበር)፣

6/ በኢትዮጵያ ተጀምረው የነበሩት የመካናይዝድ እርሻ ልማቶች በሰፊ ይስፋፉ ነበር።ኢትዮጵያ ጤፍ በብዛት በማምረት ለዓለም ብቸኛ አምራች እና ላኪ ሀገር ትሆን ነበር።

7/ የበርካታ ሃገራት ትላልቅ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መዋለ ንዋይ ለማፍሰስ ይጎርፉ ነበር።በተለይ ደርግ የወደቀበት ወቅት የምስራቅ አውሮፓ ሃገራት ገና ከሩስያ ተፅኖ እየወጡ፣በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም እየተነቃቁ ስለነበር ከወቅቱ ጋር የሚሄድ የድርጊት መርሃ ግብር እና ከሙስና በተቻለ መጠን የፀዳ መንግስት ስለሚኖር ኩባንያዎቹ ከማንም የአፍሪካ ሃገራት ኢትዮጵያን እንደሚመርጡ ሳይታለም የተፈታ ነበር።ይህም ባለፉት 24 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ ከብራዚል እኩል የምትጠራ ሀገር ትሆን ነበር።

8/ ናዝሬት የተጀመረው የትራክተር መገጣጠምያ ፋብሪካ ምርቱን አሻሽሎ በሌሎች ቦታዎች ማምረት እና የኢትዮጵያን ገበሬ በከፊልም ቢሆን ከበሬ አስተራረስ ዘዴ እንወጣ ነበር።

9/ ወላጆቻቸው የሞቱባቸው ማሳደጊያ እና መንከባከቢያ ማዕከል ”ሕፃናት አምባ” በሁሉም ክፍለ ሀገሮች ተመስርቶ እናት አባት የሞቱባቸውን በተለይ ባለፉት 24 ዓመታት ቁጥራቸው በመቶ ሺዎች የሆኑትን ሕፃናት ወደ ማዕከሉ አስገብቶ ኃላፊነት የሚሰማቸው ትውልድ ማፍራት ይቻል ነበር።የማዕከሉም አስተዳደር በባለሥልጣን ደረጃ ተዋቅሮ ኢትዮጵያውያን በወር ከደሞዛቸው እያዋጡ በርካታ እናት አባት ያጡ ሕፃናትን ሕይወት መታደግ ይቻል ነበር።ኢህአዴግ ማዕከሉ የነበሩ ሕፃናትን የደርግ ልጆች ብሎ በምሽት እንዳባረራቸው እና ማዕከሉን አንዴ የካድሬ ማሰልጠኛ ሌላ ጊዜ የግብርና ማሰልጠኛ እያደረገው መሆኑ ይታወቃል።

ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ዓመታት ውስጥ ላይኖሯት (ላይሆንባት) የሚችሉት

1/ ሀገሪቱ በጫት እንዲህ አትበከልም ነበር።ወጣቶቿ በስፖርት እና በልዩ ልዩ ሙያ ላይ እንጂ የጫት ተገዢ አይሆኑም ነበር፣

2/ ከሶስት መቶ ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችን ወደ መካከለኛው ምስራቅ ለግዳጅ ሥራ አይጋዙም ነበር፣

3/ የጣና በለስ ፕሮጀክት አይፈርስም ነበር፣

4/ ኢትዮጵያ የባህር በር የሌላት ሀገር አትሆንም ነበር፣

5/ ኢትዮጵያ በጎሳ የተደራጀ ፓርቲ አይኖራትም ነበር።ሀገሩም በጎሳ የተከፋፈለ አስተዳደር አይኖራትም ነበር።
6/ ኢትዮጵያውያን ጎሳቸው ሳይሆን ኢትዮጵያዊነታቸው ብቻ በፈለጉት ቦታ ሄደው የመስራት መብት ይኖራቸው ነበር፣

7/ ኢትዮጵያውያን በመላው ዓለም ክብራችን ዝቅ ተደርጎ እንዲታይ አይደረገም ነበር። አንድ ችግር ሲገጥመን ወደ ኤምባሲያችን ሄደን ችግራችንን እንፈታ ነበር፣

8/ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለሁለት የተከፈሉ አባቶች አስተዳደር አይኖራትም ነበር፣

9/ ከ11 ቢልዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ከሀገር በሕገ ወጥ መንገድ አይወጣም ነበር፣

10/ የብሔራዊ ባንክ በቀትር ፀሐይ ወርቁን ለሌቦች አስረክቦ አርተፍሻል ወርቅ አይቀበልም ነበር፣

11/ የተማረ የሚከበርባት እና ሥራ የምያገኝባት እንጂ ኮብል ስቶን ተራቢ እንዲሆን አይደረገም ነበር፣

12/ የሕፃናት አምባ ወላጆቻቸው የሞቱባቸው ሕፃናት በምሽት በኢህአዴግ ወታደር አያባረሩም እና ሴቶች ለሴተኛ አዳሪነት ወንዶቹ ለጎዳና ተዳዳሪነት አይዳረጉም ነበር።
national bank of ethiopia
13/ ኢትዮጵያ ሕፃናቶቿን በጉዲ ፈቻነት በመሸጥ በአፍሪካ ቀዳሚ አትሆንም ነበር።

ባጠቃለይ ኢትዮጵያ በህወሓት አገዛዝ ስር እሩብ ክ/ዘመን (25 ዓመታት) ሊሞላት አንድ ዓመት ብቻ ቀራት።ሃያ አምስት አመታት በርካታ ሃገራት ወደ መካከለኛ ገብ ደረጃ የደረሱበት ነው።የዛሬ 24 ዓመት አንጎላ ጦርነት ላይ ነበረች።ዛሬ አንጎላ በከፍተኛ እድገት ላይ የምትገኝ ሀገር ነች። የዛሬ 24 ዓመት ቦትስዋና ብዙም የምትደነቅ ሀገር አልነበረችም ዛሬ ቦትስዋና የአልማዝ አምራች ሀገር ነች።የዛሬ 24 ዓመት ጋና ስሟ እምብዛም አይነሳም። ዛሬ ጋና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ መንግስት የምትቀይር እና የነዳጅ ሀብት ባለቤት የሆነች ሀገር ነች።ሃያ አራት ዓመት እንደ ኢትዮጵያ ላለ ጠንካራ ሰራተኛ ሕዝብ፣በብዙ ውጣ ውረድ ላለፈ ሕዝብ እና በርካታ እድሎች ከፊቱ ላሉት ሕዝብ ዛሬ ብራዚል ለደረሰችበት ደረጃ የመድረስ አቅም ነበረው።ነገር ግን በጎሰኛ መንግስት ተጠልፎ የጥቂቶችን የተንደላቀቀ ሕይወት እየተመለከተ እንዲኖር ተፈርዶበታል።አሁንም ከነገ ዛሬ ይቀድማል እና ለኢትዮጵያ ነፃነት አንድነታችንን እናጠናክር።ከጎሰኞች ማዶ ለምትመሰረተው የሁላችንም ኢትዮጵያ የበኩላችንን እናድርግ።

ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ግንቦት 20/2005 ዓም (ሜይ 28/2015)

– See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41799#sthash.ryD3xo6F.dpuf