ሱዳን ከአማራ ክልል ጋር በምትዋሰንበት በኩል የሚገኘውንና ሶስት ወንዞች የሚያቋርጡትን የ250ካሬ ኪ.ሜ የቆዳስፋት መሬት እንደገና ይካለል ዘንድ ለኢትዮጵያ መንግስት ጥሪ አደረገች (አዋዜ)

Ethiopia-Sudan-Border-Protest1

የሱዳን ገዳሪፍ ግዛት ሀገረ ገዢ ሜርጋኔ ሳሌህ በኢትዮጵያና በሰዳን መካከል አለ ብለው የሚያምኑት የረጅም ግዜ የድንበር ውዝግብ ይፈታ ዘንድ ድንበሩ እንዲካለል መጠየቃቸው ተሰማ፡፡ ሄራል ትርቢውን የተሰኘው ጋዜጣ ትላንት እንደዘገበው ሱዳን በምስራቃዊ ግዛቴ ገዳሪፍ ደቡብ ምስራቅ አል-ፍልሻጋ በተባለው አከባቢ ይገኛል የምትለውና የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች መሬታችው መሆኑን ሚናገሩለትን ይህን ምሬት ጉዳይ ከቀ/ጠ/ሚ/ አቶ/መለሰ ዜናዊ ግዜ ተጀምሮ እሳቸው ድንገት በመሞታቸው መቋረጡን ያስታውሳል ጋዜጣው፡፡ እናም አሁን ‹‹የኢትዮጵያና ሱዳን መንግስታት ድንበሩን እንደገና ለማካለል በተስማሙት መሰረት ይፈጸምና ድንበር ውዝግቡ ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ይፈታ››› ብለዋል ገዳሪፍ ሀገረ ገዢ፡፡

የሱዳኑ ሄራልድ ትርቢውን የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ‹‹ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ የኢትዮጵያን ምድር ለሱዳን አሳልፎ ትቶለታል በማላት ይከሳሉ›› ሲል ጋዜጣው ጽፏል፡፡ በባለፈው የፈረንጆች አመት ህዳር ወር የሱዳኑ አል-በሽርና የኢትዮጵያው ጠ/ሚ ሀይለማሪያም ደሳለኝ በቀ/ጠ/ሚ/ አቶ/መለሰ ዜናዊ ሞት የተነሳ የተቋረጠውን ድንበሩን እንደገና የማካለል ስራ የሚጀመርበትን አዲስ ቀን እንዲወስኑ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሮቻቸው መመሪያ ማስተላለፍቸውን ጋዜጣው ጠቅሷል፡፡

አዲስ ይደረጋል በተባለው ማካለል ጉዳይ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው መሬት 250 የ250 ካሬ ኪ.ሜ ነው ምናልባት የአዲስ አበባን ጠቅላላ ስፋት ከግማሽ በላይ የሚሆን መሬት ማለት ነው፡፡ በውስጡ ደግሞ ለእርሻ እጅግ ተስማሚ መሬት የሆነ 6 መቶ ሺ ሄክታር 6 መቶ ሺ የእግር ኳስ ሜዳ የሚያክል ለም መሬት አለው፡፡

የሱዳኑ ሄራልድ ትርቢውን እንደተነተነው ይህን ለም መሬት ደግሞ አጥባር ሲቲት ባዝላን የሰተሠኙ ወንዞች አቋርጠውት የሚያልፉ በመስኖ ሊለማና በአመት ሁለት ግዜ ሊመግብ የሚችል በጠራ ቋንቋ ጮማ መሬት ነው የሱዳን ገዳሪፍና ብሉ ናይል ግዛቶች ከአማራ ክልል ጋር የሚዋሰኑ ናቸው፡፡

ምንጭ ፤- አዋዜ

– See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/10034#sthash.CwU6WdaE.dpuf

ከዊሃ እስከ ኦምሃጀር – አንድ ሰሞን ከአርበኞች ጋር (ኤፍሬም ማዴቦ)

በኤፍሬም ማዴቦ

ቃል የዕምነት ዕዳ ነዉ። አዎ! ማተቡን ላጠበቀና በአምላኩ ለሚታመን በእርግጥ ቃል የዕምነት ዕዳ ነዉ። ሰዉ ነኝና እንደ ፈጣሪ ቃሌ ሁሉ እዉነት ነዉ ብዬ አለተፈጥሮዬ አላብጥም። ግን ሰዉ ብሆንም ፈጣሪዬን የምፈራ ሰዉ ነኝና ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ስል ልቦናዬ እያወቀዉ እንደነ ጋሼ እንደልቡ ዉሸት ደርድሬ ለአንባቢ የማቀርብበት ምንም ምክንያት የለም። ከዚህ ቀጥሎ የማስነብባችሁ እያንዳንዱ ቃል እንደ ዳያስፖራ ተረተኞች የምተርተዉ ‘ሰዉ ሰዉ’ የማይሸተት ተረት ሳይሆን ኢትዮጵያ ድንበር ላይ በየግንባሩ የተሰለፉትንና በስልጠና ላይ የሚገኙትን የኢትዮጵያ አርበኞች ስጎበኝ በአይኔ ያየሁትንና በጆሮዬ የሰማሁትን ቃል ነዉ።Ephrem Madebo with Patriotic Ginbot 7 fighters

ቨርጂኒያ ወደሚገኘዉ “Dulles” አዉሮፕላን ማረፊያ የሄድኩት ከልጄ ጋር ነበር። ከቤቴ Dulles የግማሽ ሰዐት መንገድ ነዉ። ያቺን ግማሽ ሰዐትና አዉሮፕላን ማረፊያ ደርሼ ሻንጣዬን እስካስጭን ድረስ አይኔ እያንዳንዷን ደቂቃ ከልጄ ከቢኒያም አልተለየም። መለየቱን ስላልወደደዉ ልቤ ደንግጧል። ከወያኔ ጋር ለመፋለም በረሃ የሚጓዘዉ ኤፍሬም ከአንድ ልጁ መለየት አቃተዉ። ምነዉ ብዬ እራሴን ጠየኩት- እኔዉ መልሼ ምንም አልኩ። ልጄን አቀፍኩት፤ አሁንም ደግሜ ደጋግሜ አቀፍኩት። እምባ ፊቴን ሞላዉ። ቀና ብሎ ተመለከተኝና ሲከፋዉ ታየኝ። ሁለተኛ ዙር እምባ ፊቴን ሞላዉ። “Son I don’t want to do this, but I have to do it” አልኩ በሁለት እጄ አቅፌ እንደያዝኩት። ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ አባት ሆይ ፈቃድህ ከሆነች ይቺ ጽዋ ከኔ ትለፍ ብሎ የጸለየዉ ፀሎት ትዝ አለኝ። እኛ ሰዎች የዳንነዉ ይህ ፀሎት ባለመመለሱ መሆኑ ትዉስ ሲለኝ ልቤ በሀሳቡ ጸና። አባባ Come on . . . be strong. I promise I will be the son that you raised- you will be proud of me” አለኝ ቢኒያም በዚያ 17 አመት ሙሉ በማዉቀዉ ቆንጆ ድምጹ። የተናገራቸዉ ቃላት ዉስጤ ገብተዉ ኃይል ሲሆኑኝ ተሰማኝ። ጠነከርኩ። ተሰናብቼዉ ወደኋላ እያየሁት ወደ ዉስጥ ገባሁ። ወደ ፍተሻዉ ቦታ ስሄድ ልቤን ከፍተኛ የመለየት ኃዘን እንደ ግግር በረዶ ሲጫነዉ ተሰማኝ፤ መሸከም አቃተኝና እንደ ህፃን ልጅ እያነባሁ ፍተሻዉ መስመር ላይ ገብቼ ወረፋ ያዝኩ።

እንደፈረንጆቹ ዘመን አቆጣጠር ረቡዕ ኦጎስት 5 ቀን ከሌሊቱ 9 ሰዐት የተሳፈርኩበት አዉሮፕላን አስመራ አለም አቀፍ አዉሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ አይኔ ላይ ዉል ዉል እያለ ልቤን የሰቀለዉ የሚጠብቀኝ የትግል ዉጣ ዉረድ ሳይሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተመርቄ በ22 አመቴ ስራ የጀመርኩባት ዉቧ የአስመራ ከተማ ምን ትመስል ይሆን የሚል የሀሳብ ዉጣ ዉረድ ነበር። ሆኖም አካልም መንፈስም እየከዳ ምንም ነገር ማሰብ አይቻልምና ወደ ግዜያዊ ማረፊያ ቦታዬ እንደወሰዱኝ ለሁለት ቀን ከግማሽ የተጠራቀመ እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ አለ።

ረቡዕ ከቀኑ አንድ ሰዐት አካባቢ “እባክህ ተነሳና ምሳ እንብላ” የሚል የሁለት ሰዎች ድምጽ ተራ በተራ ጆሮዬ ዉስጥ ገባና እንቅልፌን ሰለበዉ. . . መነሳት ባልፈልግም በልቤ ትግሉ ተጀመረ አልኩና ከተጋደምኩበት ቀና አልኩ። ፊት ለፊቴ ቆመዉ ተነስ እያሉ የሚጨቀጭቁኝ የትግል ጓደኞቼ ነአምን ዘለቀና ብርሀኑ ነጋ ነበሩ። ምሳ ላይ ተቀምጠን እነሱ የሚያወሩት ወደ ኤርትራ በረሃዎች ሰለሚደረገዉ ጉዞ ሲሆን እኔ ደግሞ በወጣትነቴ ስለማዉቃት የአስመራ ከተማ ነበር። አስመራን ትቼ ከነሱ ጋር እንደነሱ ማሰብ ሞከርኩ . . . አሁንም አሁንም ሞከርኩና ሲያቅተኝ ተዉኩት። በተለይ ምሳ የበላንበት ካራቨል ሬስቶራንት ዉስጥ በወጣትነቴ ብዙ ትዝታዎች ነበሩኝና ጭራሽ ምግቡን ትቼ በምናብ ወደ ወጣትነቴ ሽምጥ ጋለብኩ። ባር ኡጎ፤ ባር ቱኔል፤ ባር ፀአዳ ፈርስ፤ ባር እምባባና የባቢሎን ጋጋታ እንዳለ ፊቴ ላይ እየመጡ ተደቀኑ። ቀና ስል ነአምንና ብርሀኑ . . . አትበላም እንዴ አሉኝ። ወደ ኋላ ሽምጥ ያስጋለበኝን ፈረሴን ልጓም ያዝ አደረኩና ካሁን በኋላ ወደፊት ብቻ ብዬ ከሁለቱ ጓደኞቼ ጋር በአካልም በመንፈስም ተቀላቀልኩ።

የአስመራ ከረን መንገድ ከተነጠፈ አስፋልት ዉጭ ሌላ ምንም አይቶ ለማያዉቅ ለእንደኔ አይነቱ የዳያስፖራ ‘በለስ’ ቀርቶ ደጋግሞ የተጓዘበትንም ሰዉ ልብ ይሰልባል። አስመራን ይዞ፤ አዲአቤቶንና እምባደርሆን ይዞ በአዲተከለዛን፤ በኢላበርዕድ፤ በከረንና በሀጋዝ አድርጎ አቆርደት ድረስ የሚዘልቀዉ መንገድ የአለም ተራራዎች ስብሰባ ተጠራርተዉ ወደየመጡበት ላለመመለስ ተማምለዉ የመሸጉበት ቦታ ይመስላል። አንዱን ተራራ ሽቅብ ወጥተንና ቁልቁል ወርደን እፎይ ብለን ሳንጨርስ ሌላዉ ከተፍ ይላል። በስተቀኛችን ያለዉን ተራራ አይተን ወይ ጉድ ስንል በግራችን ያለዉ ድንቄም ጉድ እያለ ያሾፍብናል። እልፍ ስንል ተራራ፤ ከዚያም ተራራ፤ተራራ፤ ተራራ ብቻ ነዉ። ፊት ለፊቴ የማያቸዉ ተራራዎች ተፈጥሮ የቆለለዉ የዲንጋይ ክምር ሳይሆን አዋቂ በዉኃ ልክ እየጠረበ የደረደረዉ ሾጣጣ ኃዉልት ይመስላሉ። አንኳን ለሰዉ ልጅ ለገደሉ ንጉስ ለዝንጀሮም አይመቹም። ባጠቃላይ የአስመራ አቆርደትን መንገድ ሲመለከቱት እንደ አጥር ከተሰለፉት ተራራዎች ባሻገር አገር ያለ አይመስልም። አላማና ጽናት ላለዉ ሰዉ ግን ከተራራዉ ወዲያ አገር ከአገርም ወዲያ ሌላ. . . ሌላ ወያኔ የቀማን አገር አለ።

አላማ የሌለዉ፤ ሆዱ ያልቆረጠ፤ ፈሪ፤ ወኔ የከዳዉና አይኑን ተራራዎቹ ላይ ብቻ ያሳረፈ ሰዉ ከአስመራ ተነስቶ በከረን በኩል አቆርደትን አቋርጦ የጀግኖቹ መንደር ሀሬና የሚደርስ አይመስለዉም። ለዚህ ነዉ ሁሉን የሚችል እግዚአብሄር አይዞህ ብሎ የላከዉ የብሉይ ኪዳኑ ነቢዩ ኤልያስ ኤልዛቤልን ፈርቶ እንደሸሸ ሁሉ የኛም ዘመን ጋዜጠኛ ነን ባዮች፤ ዘፋኞችና አርበኛ ነን ባይ የሀሰት ነቢያት ገና ከረን ሳይደርሱ ተራራዉን እየፈሩ በኤርትራ በኩል ምንም ነገር መስራት አይቻልም እያሉ እንደ ግመል ሽንት የኋሊት የሚጓዙት። ድንቄም ጋዜጠኛ! ጋዜጠኛ ታሪክ ሸራርፎ በሰጠዉ ግዜ እየኖረ ያየዉንና የሰማዉን ለትዉልድ እያስተላለፈ ለራሱ የማይኖር ልዩ ፍጡር ነዉ። የኛዎቹ “ጋዜጠኛ” ነን ባዮች ግን እራሳቸዉ ለራሳቸዉ በሰጡት ግዜ እየኖሩ የራሳቸዉን ግሳንግስ የፈጠራ ታሪክ የሚነግሩን ከህያዉ በታችና ከሙታን በላይ ባለዉ ባዶ ቦታ የሚኖሩ ባዶዎች ናቸዉ። አምላክ በምህረቱ ወደ ላይ ይሳባቸዉና ከህያዋን ጋር ይቀላቅላቸዉ።

ምድረ የወሬ ቋቶች ይግባችሁ! የኢትዮጵያ ህዝብ ዉኃ ዉኃ የሚያሰኝ የእሳት ጉድጓድ ዉስጥ ነዉ ያለዉ፤እሱ ከጉድጓዱ ባስቸኳይ መዉጣት እንጂ እንደናንተ በኤርትራ በኩል ከሆነ ይቅርብኝ ብሎ የሚጃጃልበት ግዜዉም ትዕግስቱም የለዉም። ለነገሩ እነዚህ የወሬ አርበኞች ተራራ ወጥተዉ፤ በረሃ አቋርጠዉና ወንዝ ተሻግረዉ ከወያኔ ጋር ሳንጃ ሊማዘዙ ቀርቶ የገዛ ልጆቻቸውን የልደት ኬክ ደፍረዉ በቢላዋ የማይቆርጡ የ”ዳዉን ታዉን” ቅምጦልች ናቸዉና ከነወሬያቸዉ እዚያዉ “ዳዉን ታወን” ብንተዋቸዉ የሚበጅ ይመስለኛል። አይደል?

ወሬና ስራ ለየቅል ናቸዉ፤ ለወሬ የሚያስፈልገዉ ሹል አፍ ብቻ ነዉ። ለስራ ግን አፍ፤ እጅ፤ አግር፤ አይን፤ ጆሮና የሚያስብ አዕምሮ ያስፈልጋል። ወረኛና ለስራ ያልተፈጠረ ሰዉ የተራራዉ ከፍታ እየታየዉ “በዚህ በኩል እንዴት ተደርጎ” እያለ የወሬ ቱማታዉን መደርደር ይጀምራል። የሚሰራ ሰዉ ግን ግቡ ከተራራዉ ባሻገር ከተከዜ ማዶ ነዉና ተራራዉን ሽቅብ ወጥቶና ከጠመዝማዛዉ መንገድ ጋር እኩል ተጠማዝዞ ወዳለመዉ ግብ ይጓዛል። አንባቢ ሆይ! ሠራተኛ በለኝ አትበለኝ እሱ ያንተ ጉዳይ ነዉ፤ መዳረሻዬ ከተከዜና ከመረብ ወንዞች ባሻገር መሆኑንና አላማዬም ፍትህና ነጻነት መሆኑን ግን እኔዉ እራሴ አብጠርጥሬ ልነግርህ እችላለሁ። የምወደዉን አንድ ልጄንና ጥሩ ስራዬን ደህና ሁኑ ብዬ በረሃ የገባሁት እናት አገሬ ዉስጥ ፍትህ፤ ነጻነት፤ እኩልነትና ዲሞክራሲ አብበዉ ለማየት ነዉ እንጂ የኤርትራ በረሃና ተራራ ናፍቆኝ አይደለም። የናፈቀኝ ተራራና በረሃ ቢሆን ኖሮ አሪዞናና ኮሎራዶ ይቀርቡኝ ነበር።

ዉቧን የአቆርደት ከተማና ቀዳማዊ ኃ/ሥላሤ ያሰሩትን ግዙፍ መስጊድ በስተቀኝ እያየን ወደ ባሬንቱ ስናመራ ያ ከአስመራ ጀምሮ የተከተለን የተራራ መንጋ ፀሐይ እንደገላመጠዉ በረዶ እየሟሸሸ ሄዶ ገና ሀይኮታ ሳንደርስ ሜዳ ሆኖ አረፈዉ። የበረሃዉ ሙቀት እንዳለ ቢሆንም ባሬንቱ ስንደረስ የሚነፍሰዉ ቀዝቃዛ አየር ሙቀቱን አለዝቦታል። ባሬንቱን ለቅቀን ወደ ተሰነይ ስናመራ መሬቱ ሜዳ፤ ሰማዩ ደመናማ፤ አየሩ ነፋሻማ እየሆነ ይመጣል። ትናንሽ ልጆች እዚህም እዚያም ይዘልላሉ፤ ትራክተሩ ያርሳል፤ ግረደሩ ይዳምጣል፤ እንደኔ አይነቱ ጠመዝማዛዉ መንገድ ቀልቡን የሰለበዉና ፀሐዩ ያቀለጠዉ ምስኪን ደግሞ ወላዲት አምላክ ምን በደልኩሽ እያለ ያምጣል። ባሬንቱ ያኔ እኔ ሳዉቃት የጋሽና ሰቲት አዉራጃ ዋና ከተማ ነበረች፤ ዛሬ ከሃያ ስምንት አመት በኋላ ያየኋት ባሬንቱ ግን ከፍተኛ የንግድና የእርሻ እንቅስቃሴ ይታይባታል፤ ዉብትም ስፋቷም በእጥፍ ጨምሯል ፤ደግሞም የዛሬዋ ባሬንቱ የጋሽ ባርካ ዞን ዋና ከተማ ናት።

ከባሬንቱ ወደ ተሰነይ ሲወጣ ግራና ቀኝ አዉራጎዳናዉን ይዞ ኢትዮጵያና ሱዳን ጠረፍ ድረስ የተንጣለለዉ መሬት የኤርትራ የእህል መቀነት ነዉ። አካባቢዉ ከፍተኛ የልማት እንቅስቃሴ ይታይበታል። የኤርትራን ልማትና የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ ማየት የፈለገ ሰዉ ከአስመራና ከሌሎች ትላልቅ ከተማዎች ወጥቶ ገጠር መግባት አለበት። ግድቡ፤ እርሻዉ፤ የጤና ተቋሙና ሌላም ሌላ የመሠረተ ልማት ምልክቶች በጉልህ የሚታዩት ገጠሪቱ ኤርትራ ዉስጥ ነዉ።

ከተሰነይ ወጥተን ጥቂት እንደተጓዝን መኪናችን አስፋልቱን ለቅቃ ኮረኮንቹ መንገድ ዉስጥ ገብታ ስትንገጫገጭ ከእንቅልፌ ነቃሁና እንደመንጠራራት ብዬ . . . ደረስን እንዴ አልኩ … የመኪናችንን ሾፌር። ገና ነዉ ትንሽ ይቀራል አሉ ወደኋላ ዞር ብለዉ። እንዳዉ ለነገሩ ነዉ እንጂ ሰዉዬዉ ዬት እንሄዳለን፤ መቼ አንሄዳለን ወይም መቼ እንመለሳለን ለሚሉ ጥያቄዎች በፍጹም መልስ አይሰጡም። ወያኔ የማይሰማን ሁሉንም ነገር ሆዳችን ዉስጥ ከያዝነዉ ብቻ ነዉ የሚል ፈሊጥ አላቸዉ። ዋናዉን መንገድ ለቅቀን ኮረኮንቹን ከተያያዝነዉ በግምት ከ20 ደቂቃ በኋላ አርበኞች መንደር ቁጥር አንድ ደርስን። ዘፈኑ፤ ጭፈራዉ፤ ሆታዉና ዕልልታዉ ቀለጠ። አርበኛዉ ጠመንጃዉን እንደታቀፈ እየዘለለና እየፎከረ እንኳን ደህና መጣህልን እያለ መሪዉ ላይ ተጠቀለለ። “የወያኔ ዘረኞችና አንዳንድ ተላላዎች አንተንና ጓዶችህን ትኩስ ሀምበርገር እየበላችሁ ወጣቱን በረሃ ዉስጥ ታስጨርሳላችሁ” እያሉ አርበኛዉንና መሪዉን ለመለያየት ብዙ ጥረዋል። እናንተ ግን የሞቀ ኑሯችሁን ትታችሁ ታግላችሁ ልታታግሉን በረሃዉ ድረስ መጥታችሁ ተቀላቅላችሁናል . . . እሴይ የኢትዮጵያ አምላክ! . . . ወያኔ የተሸነፈዉ ዛሬ ነዉ እየለ አርበኛዉ በሆታና በዕልልታ ከዉስጥ የመነጨ ደስታዉን ገልጸ። ብቻ ምን አለፋችሁ ጀግኖቹን ያሉበት ቦታ ድረስ ልናይ ሄደን የጀግና አቀባበል ተደረገልን። እንደ አንድ ታጋይ ድል አፋፍ ላይ ልድረስ አልድረስ አላዉቅም፤ ማሸነፋችንን ግን አረጋገጥኩ።

የነፍስ ወከፍ ጠመንጃዉን እንዳቀፈ ሰላም ሊለኝ ሲመጣ ትኩር ብዬ አየሁት። ወጣት ነዉ፤ ጽናቱና ቁርጠኝነቱ ፊቱ ላይ ይነበባል። በፈገግታ የታጀበዉ የዋህ ፊቱ ልጅነቱን በአዋጅ ይናገራል። ዕድሜዉ ከሃያ አይበልጥም። ተቃቅፈን ሰላም ስንባባል እጅብ እጅብ ብሎ የተጎነጎነ ፀጉሩን በእጄ እያሻሸሁ “እቺን ነገር ታበድረኛለህ” አልኩት ፀጉር እየከዳዉ ያስቸገረኝን እራሴን እያሳየሁት። ችግር የለም አለኝ። “ችግር የለም” በአርበኞቹ ሠፈር የተለመደ አባባል ነዉ። የበረሃዉ ንዳድ፤ የዉኃዉ ጥማት፤ የምግብ ችግር፤ ክብደት ተሸክሞ ተራራዉን ሽቅብ መዉጣትና ባጠቃላይ ወያኔንና ዘረኛ ስርዐቱን ማስወገድ ለአርበኛዉ ችግር አይደለም። አርበኛዉ ለእንደነዚሀ አይነት ችግሮች ተዘጋጅቶ ስለመጣ እንደችግር አይመለከታቸዉም።

ድንኳን ዉስጥ ገብተን ቁጭ እንዳልን . . . . እዚህ አካባቢ ችግራቸሁ ምንድነዉ አልኩት። ይምጡ አለኝና ከድንኳኑ ይዞኝ ወጥቶ ገዢ መሬት ይዘዉ የመሸጉትን የተለያዩ ካምፖች አሳየኝና የእያንዳንዳቸዉን ስም ነገረኝ። ሁላችንም የመጣነዉ ከኢትዮጵያ ነዉ፤ ሁላችንም የምንታገለዉ ወያኔን ነዉ፤ ደግሞም የሁላችንም ጥያቄ ፍትህ፤ ነጻነትት፤ እኩልነትና ዲሞክራሲ ነዉ. . . .. ግን አንድ ላይ አንታገልም። እስከመቼ ነዉ የአንድ አገር አርበኞች ከአገራችን ወጥተን፤ የተለያየ ድንኳን ተክለን፤ በተናጠል የጋራ ጠላታችንን የምንዋጋዉ? እባካችሁ ገላግሉን ብሎኝ ቀና ሲል አይኑ ካይኔ ገጠመ። በአፉ ከነገረኝ በአይኑ የነገረኝ በለጠብኝ። እንዲህ አይነቱን ብስለት የተሞላዉ ንግግር የሰማሁት ከልጄ ብዙም ከማይበልጥ ኢትዮጵያዊ ወጣት መሆኑ ሲሰማኝ እራሴን ታዘብኩት፤ ኢትዮጵያዊነቴን ግን ከወደድኩት በላይ ወደድኩት። አዎ አሁንም አሁንም አትዮጵያዊነቴን ከነችግሩ ወደድኩት። ደግሞስ ዬኔ ስራ ችግር መፍታት ነዉ እንጂ የአገሬ ችግር ፊቴ ላይ በተደቀነ ቁጥር ኢትዮጵያዊነቴን ጥያቄ ዉስጥ ማስገባት አይደለም።በነገራችን ላይ በተናጠል የሚደረገዉ ትግል አያዋጣምና “እባካችሁ አንድ አድርጉን” የሚለዉ ጥያቄ የአንድ አርበኛ ጥያቄ ሳይሆን በየሄድኩበት ካምፕ፤ ግምባርና ምሽግ ዉስጥ ከአብዛኛዉ አርበኛ አፍ የሚወጣ ጥያቄ ነዉ።

ቀኝ እጄን ወጣቱ አርበኛ ግራ ትከሻ ላይ አሳረፍኩና በሌባ ጣቴ በርቀት የሚታዩትን ካምፖች እያሳየሁት… አንዱጋ መሄድ እንችላለን አልኩት። አይ ጋሼ አሁን መሽቷል አለኝ። ሰዐቱ ገና ከቀኑ 9 ሰዐት ቢሆንም ሰፈሩ የአርበኞች ስለሆነ በነሱ ህግ መተዳደር አለብኝ ብዬ እሺ አልኩት። አይዞት እናንተ አስተባብራችሁ አንድ አድርጉን እንጂ ሌላ ሌላዉ ችግር የለዉም አለኝ። እኔም እንደ ወጣቱ አርበኛ በድፍረት “ችግር የለም” ለማለት ባልደፍርም . . . አይዞህ ትብብርን በተመለከተ በቅርብ ግዜ ሁላችንንም የሚያስደስት ዜና አብረን እንሰማለን አልኩት። ፈገግ አለና እሱን ከጨረሳችሁልን ሌላዉን ለኛ ተዉት አለኝና ይዞኝ ወደ ድንኳኑ ገባ።

ሐሙስ ነኃሴ 13 ቀን ጎህ ሳይቀድ ከእንቅልፌ ተነሳሁና ትንሽ ዞር ዞር ብዬ አልጋዬ ላይ ተመልሼ መጽሐፌን ማንበብ ጀመርኩ። ሁለት ምዕራፍ ጨርሼ ሦስተኛዉን ልጀምር ስል ከሩቁ ቡና ቡና ሸተተኝ። ቀና ብዬ ስመለከት ፍረወይኒ የቆላችዉን ቡና እስከነማንከሽከሻዉ ተሸክማ ልታስሸትተኝ ስትመጣ አየኋት፤ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ቁርስ ደረሰ እንዴ ብዬ ማንከሽከሺያዉ ላይ የሚንቦገቦገዉን ጭስ በእጄ ደጋግሜ ወደ አፍንጫዬ ሳብኩት። ‘ኡወ ቁርሲ ደሪሱ’ ብላ ፍረወይኒ የተቆላዉን ቡና ይዛ ወደ መጣችበት ተመለሰች።

ከጧቱ አንድ ሰዐት ከመሆኑ በፊት ቁርስ ተበልቶ አለቀና ሁላችንም ወደየተመደብንበት መኪና እንድንገባ ተነገረን። የሚጸዳዳዉ ተጸዳድቶ ሲጋራ የሚያጤሰዉም ሲጋራዉን ለምጦ ጉዞ ተጀመረ። ዬት እንደምንሄድ ወይም ለምን እንደምንሄድ የጠየቀም የተናገረም አልነበረም። . . . ዋ! ትንፍንሽ ብትሉ የተባለ ይመስል ሁሉም አፉን ዘግቶ ወደማያዉቀዉ ቦታ ጉዞዉን ቀጠለ። አንድ ሰዐት ያክል እንደተጓዝን . . . “እነዚያ ቤቶች ይታዩሃል” የሚል ድምጽ መኪናዉ ዉስጥ የሰፈነዉን የዝምታ ጽላሎት ሰበረዉ።አዎ ይታየኛል . . . ምን የምትባል ከተማ ናት ብዬ ቀና ስል ትልቅ ወንዝ አየሁ፤ ግን ወንዙንም ከተማዉንም ስለማላዉቃቸዉ ምንም አልተሰማኝም። እንድያዉም ፀሐይ ያጋለዉን ሰዉነቴን ለማቀዝቀዝ ወደ ወንዙ እንሂድ አልኳቸዉ። “ይቅርብህ እንደቀዘቀዝክ ትቀራለህ” አለኝ ከአጃቢያችን አንዱ።

ከተማዉ ኦምሀጀር፤ ወንዙ ተከዜ፤ ከወንዙ ባሻገር የሚታየዉ ከተማ ደግሞ ሁመራ መሆኑ ሲነገረኝ . . . የምን ወንዝ መዉረድ እዚያዉ ቀዝቅዤ ቀረሁ። አደራ ቦቅቧቃ እንዳትሉኝ . . . አልፈራሁም አልደነገጥኩም። በእርግጥ እንኳን እንደዚያ ቀርቤዉ ከሩቅ ከባህር ማዶም ጠልፎ ሊወስደኝ የሚፈልግ ሰላቢ የነገሰበትን ምድር ሳላዉቀዉ እንደዚያ በድንገት መቅረቤ ትንሽም ቢሆን አሳስቦኛል። ይልቅ እንደዚያ ያፈዘዘኝና ገና ወንዙ ዉስጥ ሳልገባ ያቀዘቀዘኝ እናት አገሬን ኢትዮጵያን በ25 አመት ለመጀመሪያ ግዜ ማየት መቻሌ ወይም የእናት ኢትዮጵያ ናፍቆት ነዉ። ለነገሩ አገርም ሰዉም የሚናፍቀዉ ርቀዉ ሲሄዱ ነዉ። ዬኔ ናፍቆት ግን ልዩ ጭራሽ ልዩ ነዉ። አጠገቧ ቆሜ አገሬ ናፈቀችኝ። አዎ! መግቢያዬ ቀረበ መሰለኝ ኢትዮጵያ ስቀርባት ይበልጥ ናፈቀችኝ።

በቃ አንሂድ አለ ይዞን የመጣዉ የበላይ መኮንን . . . አዎ እንሂድ እንጂ ከዚህ በላይ መቆየት ለወያኔ ካልሆነ ለሌላ ለማንም አይበጅም አሉ ሌላዉ በዕድሜ ጠና ያሉ የበላይ መኮንን። እኚህ ሰዉ የወያኔ ስም ሲነሳ ደማቸዉ ይፈላል ፤ እሳቸዉ እራሳቸዉ እንደ ዳዊት ሲደጋግሙት ግን ምንም አይሰማቸዉም። ከሰዐት በኋላ ረፋዱ ላይ ሁላችንም ወደየመኪናችን ገብተን ኦምሀጀርን ለቅቀን ወደ ጀግኖቹ አገር ወደ ሀሬና አቀናን። ሀሬና አርበኞች ግንቦት 7ን፤የጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ንቅናቄን፤ የአማራ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄን፤ የቤንሻንጉል ህዝብ ነጻነት ድርጅትንና ደምህትን ወላድ ማህፀንዋ ዉስጥ አምቃ የያዘች እርጉዝ ምድር ናት። እርግጠኛ ነኝ በቅርቡ ትወልዳለች።

የአስመራ ምፅዋ መንገድ እንደ ጥምጥም እየተጠመጠመ እየቀናና እየጠመመ ለረጂም ሰዐት የሚዘልቅ ያዋቂንም የልጅንም ቀልብ የሚሰልብ ሰላቢ መንገድ ነዉ። እግዚኦ . . . የከረን መንገድ በስንት መልኩ! ከአስመራ ምፅዋ መሄድ ማለት ከ2500 ሜትር ተራራ ላይ ቁልቁል ወርዶ ባህር ወለል መድረስ ማለት ነዉ። ትንፋሼን ቋጥሬ በቀኜ ገደሉን በግራዬ ተራራዉን እያየሁ ለሰዐታት ቁልቁለቱን ከተያያዝኩት በኋላ የቋጠርኩትን ትንፋሽ አዉጥቼ እፎይ ማለት የጀመርኩት ማይ አጣል ስደርስ ነዉ። ከማይ አጣል በኋላ ምፅዋ ድረስ መንገዱ ሜዳ ነዉ።

ምፅዋ ልንደርስ ትንሽ ሲቀረን ሆዴን ባር ባር አለዉ። የደስታ ይሁን የሀዘን ወይም የሲቃ አላዉቅም ብቻ ልቤ ሌላ ሌላዉን ሰዉነቴን ትቶ ደረቴ ዉስጥ ብቻዉን ይዘላል። “ዉስጥ እጄን ይበላኛል” ምን ሊያሳየኝ ይሆን . . . ይል ነበር የልጅነት ጓደኛዬ። ምነዉ እኔም እንደሱ ሆኜ ዉስጥ እጄን በበላኝ . . . ልቤ ደረቴን ጥሶ የሚወጣ እሰኪመስል ድረስ ደረቴ ዉስጥ ከሚዘል። አይፎኔን አወጣሁና ግራና ቀኙን አይኔ ያረፈበትን ቦታ ሁሉ ፎቶ አነሳሁ። ቦታዉ ዶጋሌ ይባላል. . . አዎ! ዶጋሌ . . . ጀግናዉ ራስ አሉላ 500 የጣሊያን ወታደሮችን ዶጋ አመድ ያደረጉበት የድል ቦታ። ለካስ ልቤ አለምክንያት አልዘለለም! ጣሊያን ዋና ከተማ ሮም ዉስጥ የአምስት መቶዎቹ አደባባይ የሚባል ቦታ አለ (ፒያዛ ዴ ቺንኮ ቼንቶ)። እመኑኝ እኛም አገር አይቀርም! ባንዳ ባንዳዉንና ልክ ልኩ ሲነገረዉ ደንግጦ የሞተዉን ምናምንቴ ሁሉ ትተን ሞተዉ ህይወት የሆኑልንን የትናንትናና የዛሬ ጀግኖቻችንን እናስታዉሳለን።

ምፅዋ ሁለት ቀን ብቻ ነዉ ያደርኩት – ቅዳሜና እሁድን። በጦርነቱ የፈራረሱ ህንጻዎች አሁንም አልፎ አልፎ ይታያሉ፤ ያም ሆኖ ምፅዋ ዉብ ከተማ ናት፤ ደግሞም አያሌ አዳዲስ ህንጻዎች ተሰርተዉባታል። የቀድሞዉ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ጠ/መምሪያ የነበረዉ ማዕከል ግን በጦርነቱ እንደፈረሰ ነዉ፤ ያየዉም የነካዉም ያለ አይመስልም።

እሁድ ነኃሴ 16 ቀን ከምፅዋ ተነስተን 45 ደቂቃ ከነዳን በኋላ ዊሃ ደርስን። ዊሃ ሌላዉ የአርበኞች መንደር ነዉ። ዊሃ ያለዉ አርበኛ እንዴት እንደተቀበልን ለመግለጽ አማርኛ ቋንቋ እንደገና “ሀ” ብዬ መጀመር የሚኖርብኝ ይመስለኛል። በዚያ የወፍ ማረፊያ በሌለበትና በየሴኮንዱ ዉኃ ዉኃ በሚያሰኝበት ንዳድ ዉስጥ ወታደራዊ ሥልጠና መዉሰድ ቀርቶ አንድ ሜትር መራመድም እጅግ በጣም ይከብዳል። እንግዲህ ይታያችሁ የኛዎቹ ጀግኖች እንደዚህ የምድር ሲኦል በመሰለ ቦታ ነዉ ወገኖቻቸዉን ከወያኔ መንጋጋ ነፃ ለማዉጣት እልህ አስጨራሽ የሆነ ወታደራዊ ሥልጠና የሚወስዱት። እኔም የኢትዮጵያን ህዝብ ከወያኔ ዘረኞች ለማላቀቅ እንደወያኔ 17 አመት ጫካ ለጫካ መንፏቀቅ እንደሌለብን ቁልጭ ብሎ የታየኝ ዊሃ ሄጄ እነዚህን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ስመለከት ነዉ።

ሰኞ ነኃሴ 17 ቀን በጧት ተነስተን ጉርጉሱም ሄድን። ጉርጉሱም ቀይ ባህር ዳርቻ ላይ የሚገኝ ቆንጆ የመዋኛ ቦታ ነዉ። ቁርስ አዝዘን ሳንጨርስ የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ መሪ አቶ ሞላ አስገዶም ከተፍ አለ። ታጋይ ሞላ በድንገት አልነበረም የመጣዉ፤ ልክ በቀጠሮዉ ሰዐት ነበር የደረሰዉ። አብሮን ቁርስ በላና እኛ ቀይ ባህር ዉስጥ ገብተን ስንምቦጫረቅ እሱ ማይ አጣል እንገናኝ ብሎ መኪናዉን አስነስቶ ከነፈ።

ከጥዋቱ 11፡30 ሲሆን ዋናችንን ጨርሰን የምፅዋ አስመራን መንገድ ተያያዝነዉ። ከምፅዋ አስመራ ጉዞ ማለት ሽቅብ ወደሰማይ የሚደረግ ጉዞ ማለት ነዉ፤ እንደኔ አይነቱ የዋህ ሰዉ ሰማዩን ደርሶ በእጁ የሚነካ ይመስለዋል ፤ ግን ሰማዩም ሞኝ አይደለም ደረስኩብህ ሲሉት ይሸሻል። ከቀኑ 12፡30 ሲሆን ማይ አጣል ደረስንና አስፋልቱን ትተን ወደ ደምህቶች ካምፕ የሚወስደዉን የኮረኮንች መንገድ ተያያዝነዉ። ወደ ካምፑ ስንደርስ ዊሃን፤ ሄሬናን፤ አምሀጀርንና ሌሎቹንም የአርበኞች ግንቦት 7 ካምፖች ስንጎበኝ ያየነዉ ፍጹም ኢትዮጵያዊ የሆነ የእንግዳ አቀባበል ተደረገልን። በነገራችን ላይ የደምህቶችን ካምፕ ስንጎበኝ ይህ የመጀመሪያችን አይደለም። ለእግራችን ዉኋ ቀረበልንና ነጠላ ጫማ ያደረገዉ ሁሉ እግሩን በቀዝቃዛ ዉኃ አራሰዉ። ቀዝቃዛ ዉኋ ለእግር ማቅረብ በሁሉም አርበኞች ካምፕና በበረሃዉ የኤርትራ ክፍል የተለመደ ባህል ነዉ። ከቀኑ እንድ ሰዐት ሲሆን ምሳ ቀርቦ እየተበላ ቡና ይፈላ ጀመር። ረከቦቱ፤ጀበናዉ፤ ማቶቱ፤ የከሰል ምድጃዉ፤ ፈንዲሻዉና የተደረደረዉ ስኒ በቀጥታ ወደ አደኩበት ሠፈሬ ፒያሳ ወሰደኝ። አዎ! ፒያሳ… የአዲስ አበባዉ ሳይሆን የአዋሳዉ ፒያሳ።

ቡናዉ እየተጠጣ ጨዋታዉ ሞቅ ሲል ቆየት ካሉት የጥላሁን ገሠሠ ሙዚቃዎች አንዱ ከሩቅ በለሆሳስ ተሰማኝ። በዉኔ ነዉ በህልሜ ብዬ ቀና ስል ነአምን ዘለቀ ጥላሁንን ከቴፑ ጋር አብሮ ይጫወታል። በህልሜ አለመሆኔን አወቅኩት። በሞት የተለዩን ድምጻዉያን የኛዎቹም የዉጮቹም ከላይ ከሰማይ ቢጫወቱልን እርገጠኛ ነኝ ጋላክሲዉንና ናሳ “Black Hole” እያለ የሚነግረንን ዬትየለሌ ክስተት አቋርጦ ከፀሐይ ብርሐን ቀድሞ እኛጋ የሚደርሰዉ ዘመን አይሽሬዉ የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ብቻ ነዉ። ይህንን ስሜት የሚኮረኩር፤ ጅማት የሚወጥርና አዕምሮን ሰብስቦ በትዝታ የሚያስዋኝ ዉብ ቃና ነበር ደምህቶች ሲያሰሙን የዋሉት። ብቻ ምን ልበላችሁ. . . ወበቅ የተቀላቀለዉ የምፅዋ ንዳድ ሳይቀር ለጥላሁን ገሠሠ ሙዚቃ ቦታዉን ለቀቀ። እኛም ወታደራዊ ትዕዛዝ የተሰጠን ይመስል የሁላችንም አፍ ተዘግቶ የሚንቀሳቀሰዉ እግራችን፤ ትከሻችንና ጭንቅላታችን ብቻ ሆነ።

“አልማዝን አይቼ እልማዝን ሳያት”፤ “እንጉዳዬ ነሺ” “አመልካች ጣት” “መሳቁን ያስቃል” . . . ብቻ ምን አለፋችሁ የጥላሁን ሙዚቃ ተዥጎደጎደ። ጥላሁን ገሠሠ አስመራ ላይ የሚጠብቀንን ቀጠሮ ብቻ ሳይሆን ጭራሽ እኛነታችንን አስረሳን። ቢበዛ አንድ ሰዐት ብለን የመጣን ሰዎች ከሦስት ሰዐት በላይ ከደምህት ጓዶቻችን ጋር ቆየን። በመጨረሻ የጉዟችን መሪ “አንድ ለመንገድ” ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳ። እሱ ሲነሳ “እንክርዳድ እንክርዳድ የተንከረደደ፤ ስንዴ መስሎ ገብቶ ስንቱን አሳበደ” የሚለዉ ዘፈን እያለቀ ነበር። ነአምን. . . ነአምን ብዬ ስጣራ . . . “One for the road” ይቀረናልኮ አለ ነአምን . . . እንሂድ የምለዉ መስሎት። ይህንን ሙዚቃ እንደ እንክርዳድ ተቀላቅሎን ለሚያሳብደን የዳያስፖራ ቱልቱላ መርጫለሁ አልኩት። ሳቅ አለና ከቴፑ ጋር መጫወቱን ቀጠለ። እርግጠኛ ነኝ ተቦርነ በየነ ወይም መሳይ መኮንን አንድ ቀን “እንክርዳድ እንክርዳድን” በኢሳት ያሰሙናል። አይደል ተቦርነ?

በመጨረሻ የኛም መሄጃ የሙዚቃዉም መገባደጃ ደረሰ። “One for the road” የተባለለት ሙዚቃ (ዘፈን) ገና ሲጀምር ሰማሁና ኢችንማ አምላክ ነዉ የመረጠልን አልኩ በልቤ። ያ በቁሙ “አጥንቴም ይከስከስ” ብሎ ያስተባበረን ጥላሁን ገሠሠ አሁንም ከላይ ከሰማይ ቤት “ቃልሽ አይለወጥ እባክሺ….ን” እያለ ቃል እንድንገባባ አደረገን። ተራ በተራ ከአርበኛ ሞላ አስገዶም ጋር እየተቃቀፍን “ቃልሽ- አይለወጥ- አባክሽን” ብለን ተለያየን። ቃል የዕምነት ዕዳ ነዉ ብዬ ነበር የጀመርኳችሁ፤ አሁንም ቃሌ ይሄዉ ነዉ። ቃላችን አይለወጥ! ቸር ይግጠመን።

ኤፍሬም ነኝ ከአርበኞች መንደር

ebini23@yahoo.com

መልዕክት በድሆች ድህነት ለመክበር መሯሯጥ ላይ ላሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት!!

arbegnoch-ginbot7-300x300

 

መልዕክት በድሆች ድህነት ለመክበር መሯሯጥ ላይ ላሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት!!

የግል ኑሮን ለማደላደል ሲባል የወያኔ አባል መሆን “ወይን ለመኖር” የሚል ስያሜ ከተሰጠው ዓመታት ተቆጥሯል። “ወይን ለመኖር” ዜጎች ነፃነታቸውን ለጥቅም አሳልፈው የሚሸጡበት፤ የሰው ልጅ ክብር የሚዋረድበት ገበያ ነው።

በወይን ለመኖር “የገበያ ህግ” መሠረት እያንዳንዱ ዜጋ ሊያገኘው መብቱ የሆነውን አገልግሎት እንዲያገኝ የህወሓት፣ የብአዴን፣ የኦህዴግ፣ የደህዴግ፣ የአብዴፓ፣ የቤጉህዴፓ፣ የጋህአዴን፣ የሀብሊ ወይም የኢሶዴፓ አባል መሆን፤ አልያም መደገፍ ግዴታ ነው። እነዚህ ሁሉ ድርጅቶች የህወሓት ተቀጽላ ወያኔዎች ናቸው። የእነዚህ ድርጅቶች አባል ወይም ደጋፊ ያልሆነ እንኳስ የመንግሥት አገልግሎት ሊያገኝ ጥሮ ግሮ ያፈራውንም ይነጠቃል።
በዚህም ምክንያት፣ በገጠር ያለው አርሶ አደር ቁራጭ የእርሻ መሬት፣ የግብርና ባለሙያዎች የምክር እገዛ፣ የማዳበሪያና ዘር ግዢ፣ ብድር ወይም እርዳታ ለማግኘት በአካባቢው ባለ የወያኔ ድርጅት አባልነት መመዝገብ፤ አንድ ለአምስት መደራጀት እና የወያኔን የስልጣን እድሜ የሚያራዝሙ ነገሮችን መሥራት ይጠበቅበታል። በከተሞች ውስጥም ሥራ ለመቀጠር፣ ለደረጃ እድገት፣ የመኖሪያ ቤት (ኮንዶሚንየም) ለመግዛት ሲባል መወየን አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ሆኗል:: በንግዱም ዘርፍ የንግድ ፈቃድ፣ የሥራ ቦታ እና የባንክ ብድር ለማግኝት፣ የመንግሥት ጨረታዎችን ለማሸነፍ፣ ከጉምሩክ እቃ ለማስለቀቅ፣ የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት መወየን ግዴታ ነው።
“ወይን ለመኖር” የኢትዮጵያን ሕዝብ ያዋረደ፤ ለትውልድ የሚተርፍ የማኅበራዊ ስነልቦና ኪሳራ ያደረሰ እና ደካማውን ወያኔን ጠንካራ በማስመሰል በሕዝብ የትግል መንፈስ ውስጥ ፍርሃትን የረጨ መሆኑ ግንዛቤ እየዳበረ በመጣ መጠን እየቀነሰ የመጣ ክስተት ነው። በአሁኑ ሰዓት ከቀድሞው እጅግ በተሻለ ኢትዮጵያ ውስጥ የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን ራሳችንን ከህወሓት ባርነት እያላቀቅን ምሬታችንን በግልጽ መናገር የጀመርንበት ወቅት ነው፤ ከዚያም አልፎ የህቡዕ ተግባራዊ የትግል እንቅስቃዎችን ማድረግ ደረጃ ላይ ደርሰናል።

አገር ውስጥ እየተዋረደ የመጣው “ወይን ለመኖር” በአገዛዙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካይነት በውጭ አገራት ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን (ዲያስፓራ) መካከል ነፃነታቸውን በጥቅም የሚለውጡ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን ፍለጋ ተሠማርቷል። አገዛዙ ተስፋ ያደረገው ያህል ባይሆንም ጥረቱ የተወሰነ ውጤት እያስገኘለት ነው። በጥቅማ ጥቅም እየደለለ ካመጣቸው ውስጥ በስርዓቱ ብልሹነት ያዘኑና የተሰማቸውን በግልጽ የተናገሩ መኖራቸው የሚያስደስትና የሚያበረታታ ቢሆንም ከመንደር ካድሬዎች ባነሰ ተለማማጮችና አጎብዳጆች በማየታችን ተሸማቀናል። ኢትዮጵያ ውስጥ ካለነው አብዛኛው ሕዝብ አንፃር ሲታይ በተሻለ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሚገኙት ዲያስፓራዎች መካከልም ነፃነታቸውን በጥቅም ለመለወጥ የሚፈቅዱ መገኘታቸው አሳዛኝ ነው። እነዚህ ክብራቸውን በጥቅም የለወጡ ዲያስፓራዎች ዓለም ባንክንና የዓለም የገንዘብ ድርጅትን (IMF) ተክተው ህወሓት ስላስገኘው ፈጣን እድገት በአገዛዙ ራድዮ እና ቴሌቪዥን ሲነግሩን መስማት ያሳፍራል። የህወሓት አገዛዝ “ፍትህን፣ መልካም አስተዳርንና ዲሞክራሲን አስፍኗል፤ ይህንንም መጥተን በዓይኖቻችን ተመልክተናል” እያሉ የግፉን ገፈት እየቀመስን ላለነው ሲነግሩን መስማት ያማል።

እነዚህ ወገኖቻችን ህወሓትን በማሞካሸት የሚያገኙት መሬት ብዙ ድሆች የተፈናቀለቡት፤ ለእነሱ በብላሽ የተሰጠው ብድር በረሃብ ለሚጠቃ ወገን የተላከ እርዳታ መሆኑ ማሳሰብ ይገባል። ከህወሓትና አጫፋሪዎቹ ጋር ተስማምተው ባገኙት ገንዘብ የሚቆርሱት እያንዳንዱ እንጀራ የብዙ ወገኖቻችን ደምና እንባ የፈሰሰበት መሆኑ ማስገንዘብ ያሻል። ከህወሓት ጋር በማበር በወገኖቻችን ድህነትና ችጋር እየከበሩ ያሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት ከዚህ እኩይ ሥራቸው እንዲታቀቡ ማስጠንቀቅ ይገባል። እኚህ ወገኖች የራሳቸው ክብር ማጉዳፋቸውን ብቻ ሳይሆን የልጅ ልጆቻቸውም የሚያፍሩባቸው መሆኑን ማስታወስ ይገባል። ከዚህም አልፎ የዛሬ ተግባራቸው ነገ በህግ የሚያስጠይቃቸው መሆኑን ሊያውቁ ይገባል።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የአገዛዙን እድሜ በማራዘም ላይ የተሰማሩ፤ በድሆች ድህነት ለመክበር በመሯሯጥ ላይ ያሉ፤ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ለአገዛዙ ጥብቅና የቆሙ የዲያስፓራ አባላት ከዚህ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ያሳስባል።
አርበኞች ግንቦት 7 “ከህወሓት ውድቀት በኋላ ያለው ጊዜ ለእናንተም ከዛሬው የተሻለ ይሆናል። ዛሬ ከህወሓት ጋር ያላችሁን ሽርክና አቋርጡ። ለነፃነት የሚደረገውን ትግል እርዱ፤ መርዳት ባትችሉ እንቅፋት አትሁኑ፤ አለበለዚያ ግን ከተጠያቂነት የማታመልጡ መሆኑን እወቁ” ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!

– See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/9984#sthash.h6pcIhaq.dpuf

የፓርቲዎቹ ጉባኤዎች (ይገረም አለሙ)

ይገረም አለሙ

ሰሞኑን ህውኃትና የፈጠራው ድርጅቶች ጠቅላላ ጉባኤያቸውን አካሂደዋል፡፡ የህውኃት ጭንብል የሆነው ኢህአዴግ ጉባኤም ይቀጥላል፡ከእነዚህ ጉባኤዎች የሚጠበቅ አዲስ ነገር ባለመኖሩ መነጋገሩ አስፈላጊ አይመስለኝም፡፡ ስለሆነም እኔ በዚህች ጽሁፍ የማነሰው የሀገራችንን የዴሞክራሲ ተስፋ በማጨለሙ በታሪክ ሲጠቀስ ሊኖር የሚችለው ምርጫ 2007 ማግስት ስለተካሄዱ የአራት ተቀዋሚ ፓርቲዎች (በሀገር ውስጥና በውጪ) ጉባኤ ነው፡፡

ጠቅላላ ገባኤ የፓርቲ የመጨረሻው የሥልጣን አካል እንደመሆኑ ሲሰበሰብ ያለፈን ገምግሞ የወቅቱን ሁኔታ ፈትሾ ወዴትና አንዴት እንደሚኬድ አቅጣጫ አመላክቶ ውሳኔዎች እንዲያሳልፍ ይጠበቃል፡፡ ነገር ግን ከሁሉም ጉባኤዎች ፍጻሜ በኋላ ያነበብነውም ሆነ የሰማነው እንደስከዛሬው ሁሉ ጉባኤ አካሄድን ከሚለው የፕሮፐጋንዳ ፍጆታ የዘለለ ቁም ነገር አለመከናወኑን ነው፡፡ ጉባኤ በመተዳደሪያ ደንብ ላይ በይህን ያህል ግዜ ይካሄዳል ስለተባለ ብቻ የሚከናወን ከሆነ ለጉባኤው ማካሄጃ የሚወጣውን ገንዘብ ያህል እንኳን ቁም ነገር የሚሰራ አይሆንም፡፡ በመሆኑም የአራቱም ፓርቲዎች ጉባኤዎች መሬቱ የሚፈልገውን ትቶ አራሹ ያሻውን ዘራ ይሉ አይነት ስራ ነው የተሰራባቸው፡፡ እስቲ በትንሽ በትንሹ በተናጠል አንያቸው፡፡

የኢህፓ ጉባኤ ፤በዚህ ጉባኤ አንድ ታላቅ ቁም ነገር ተከናውኗል፤ተበታትነው ግን በአንድ ኢህአፓ ስም ይጠሩ የነበሩ ፓርቲዎችን ወደ አንድ በማምጣት ኢህአፓ አንድነት በሚል ስም ለመንቀሳቀስ የተደረሰበት ስምምነት በጎ ተግባር ነው፡፡ለመለያየት ምክንያት የሆኑ ነገሮች ተመርምረው ዳግም ያ መለያየት መቼምና በማንም እንዳይከሰት የሚያስችል መተማመን ተፈጥሮ የተፈጸመ ከሆነ ይህ ምስጢር አይደለምና ቢገለጽ የእንቧይ ካብ እየሆነ ለሚያስቸግረው ለፓርቲዎች እየተባበሩ መለያየት እየተገነቡ መፍረስ ትምህርት በሆነ ነበር፡፡

ጉባዔው የኢትዮጵያን አጠቃላይ ፖለቲካዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ሁኔታዎችን በጥልቀት ከገመገመ በኋላበማለት የዘረዘራቸው 15 የሚደርሱ ጉዳዮች በሙሉ ወያኔ በኢትዮጵያውያን ላይ ያደረሳቸው በደሎች ናቸው፤ እነዚህ ከቃላት በላይ በቀን ከቀን ህይወታችን የምናያቸው በመሆናቸው አዲስ አይደሉም፡፡ ነገር ግን ኢህአፓ በአንድ ወቅት የትግሉ ግንባር ቀደም ተሰላፊ የነበረና የከተማውንም የጫካውንም ትግል የሞከረ ከአርባ አመት ለሚበልጥ ግዜም በሂደቱ ውስጥ ያለ እንደመሆኑ በተለይ ባለፉት ሀያ አራት አመታት ከወያኔ ጋር የተደረጉ ትግሎች መስዋእትነት እንጂ ውጤት ማስገኘት ያልቻሉበትን ምክንያት መርምሮ ችግሮችን ማሳየት መፍትሄውንም ማመላከት ከወያኔ አገዛዝ የመላቀቂያውን ስልትና መንገድም መጠቆም በቻለ ነበር፡፡ የወያኔን ድርጊትማ በተግባር እያየነው ነው፡፡

ጉባኤው ስለ ቀጣይ ሁኔታ ሲገልጽም ጉባዔው የወያኔ/ኢህአዴግ አገዛዝ ሀገር አፍራሽና አጥፊ ፖሊሲዎቹን በጥብቅ አውግዟል። ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመመሥረት፣ የወያኔ/ኢህአዴግን አገዛዝ ማስወገድ እንደሚገባ አረጋግጦ የበለጠ ተጠናክሮ መታገል እንደሚገባ በድጋሚ አረጋግጧል። ይላል፡፡ ይህ ማንኛውም የወያኔ አገዛዝ የአንገሸገሸው ኢትዮጵያዊ የሚለው ነው፡፡ ከአንድ ያውም የረዥም ግዜ ልምድ ካለው ፓርቲ ጉባኤ መወጣት የነበረበት በሀያ አራት አመታት ትግል የወያኔን አገዛዝ ማስወገድ ያልተቻለው በእነዚህ ምክንያቶች ነው፤እነዚህን ችግሮች ለማስወገድ ይህን ይህን ማድረግ ያስፈልጋል፤ እንዲህ ካደረግን በዚህ ስልትና መንገድ መጓዝ ከቻልን ለድል እንበቃለን፤ይህን ለማድረግም ፓርቲያችን የሚችለውን ሁሉ ያደርጋል፣ወዘተ የሚል መሆን ነበረበት አልሆነም፡፡ በመሆኑም የተበታተኑትን ማሰባሰብ ችሎ ካልሆነ በስተቀር ከጉባኤው የሰማነው አንዳችም አዲስ ነገር ባለመኖሩ ተስፋ አልሰነቀብንም፡፡

ሸንጎ፣ ሸንጎው ከጉባኤው በኋላ ባወጣው መግለጫ ለመመስረት ምክንያት የሆነውን ጉዳይ ሲገልጽ …. ሸንጎ እንዲመሰረት ያስገደደው ዋና የፖለቲካ አደረጃጀትና የአመራር ክፍተት የተበታተነውና እርስ በእርሱ የሚጠላለፈው አገር ወዳድ ተቃዋሚ ኃይል ተባብሮ፤ ተመካክሮ፤ ተናቦ፤ ተደራጅቶ፤ ብቁነት ያለው አመራር መስርቶና የጋራ ሰነድ አዘጋጅቶ በተከታታይ ትውልድና ታሪክ ሊጠቀስ የሚችል አስተዋፆ ለማድረግ ሲችል ብቻ ነው የሚል እምነት ስላለው ነው። ብሏል፡፡ ነገር ግን ይህን ለመመስረቱ ምክንያት የሆነውን ጉዳይ ምን ያህል እንዳሳካ ፣ምን ተግዳሮት እንደገጠመው፣ በሂደት ከተገነዘበው ተነስቶ ምን መደረግ እንዳለበት አላሳየም፡፡

በስልጣን ላይ የሚገኘው የህወሓት/ኢህአደግ አገዛዝ ለዴሞክራሲ መስፈን፤ ለእርጋታ፤ ለሰላም፤ ለዘላቂና ፍትሃዊ እድገት እንቅፋት የሆነ ስርዓት በመሆኑ መወገድ እንዳለበት መቀበልና ያልተቆጠበ ጥረትና አስተዋፆ ማድረግ ናቸው። የሚልም በመግለጫው ወስጥ ተጽፎአል፡፡ የወያኔን ማንነትና ምንነት በመናገር ረገድ ችግርም ልዩነትም የለም፡፡መወገድ ያለበት በመሆኑም እንደዚሁ፡፡ እንዴትና በምን ሁናቴ የሚለውና በተለይም ከቃል ይልቅ ተግባር ላይ መገኘቱ ነው ችግሩ፡፡ ወያኔን የሚያል 17 አመት ገሎና ሞቶ በጠመንጃ ሥልጣን የያዘና ሀያ አራት አመታት በምርጫ እያጭበረበረ በጠምንጃ ሥልጣኑን አስከብሮ የኖረ ሀይል በጥረትና በአስተዋጽኦ ከቤተ መንግሥት ይወጣል ተብሎ አይታሰብም፡፡ ጥረት ሳይሆን ትግል፣ አስተዋጽኦ ሳይሆን መስዋዕትነት ይጠይቃል፡፡ በመሆኑም ነው በሸንጎ ጉባኤ መግለጫ ላይ የሰፈሩት ለለውጥ ሊታገል ከተደራጀ ወይንም የተደራጁ ኃይሎችን ካሰባሰበ ድርጅት ጉባኤ የወጡ ያልመሰሉት፡፡

የሸንጎ ጉባኤ ያለፉትን ትግሎች አደረጃጀት ስልትና ተግባራዊነት ገምግሞ ውጤት አልባ ያደረጋቸውን ምክንያት ተረድቶ መፍትሄ ማመላከት የትግል አይነትና ስልት መንደፍና የተግባር መንገድ ማሳየት ነበረበት፡፡

መድረክ፤ መድረክ በዚህ ስሙ ሁለት ምርጫዎች የተወዳደረ ለ99.6 እና ለመቶ በመቶ ውጤት ባለድርሻ እንደመሆኑ፤በተናጠልም አንዳንዶቹ በተቀዋሚነት የወያኔን የሥልጣን እድሜ ያህል የቆዩ እንደመሆናቸው በዚህ ወቅት የተጠራው ጉባኤ በሰማነው መልኩ የምናውቀውን የወያኔን ድርጊት ነግሮን የተለመደውን ውግዘት አሰምቶን መጠናቀቅ አልነበረበትም፡፡ ለመሆኑ መቼ ይሆን ራስን ማየት የምንደፍረው፡፡

ወያኔ መቶ በመቶ አሸነፍኩ ለማለት የበቃው አጭበርብሮ ቢሆን ተወዳድሮ ነው፡፡ ዋንኛ ተፎካካሪ እየተባለ ሲገለጽ የነበረው ደግሞ መድረክ ነውና ለተገኘው ውጤት ባለድርሻ ነው፡፡ ስለሆነም በጥቅሉ መድረክ በተናጠል አባል ድርጅቶች በምርጫው ወቅት የነበራቸው ድክመትና ጉድለት በጉባኤው በድፍረት መፈተሽ ነበረባቸው፡፡ የ2002 የ99.6 ሽንፈት ሳይፈተሸና ትምህርት ተወስዶ ዝግጅት ሳይደረግ በዘልማድ ጉዞ ምርጫ ለ2007 ተገባና የመቶ በመቶ ሽንፈት መጣ፡፡ አሁንም በተድበሰበሰ ሁኔታ በሰላማዊ ትግሉ እንቀጥላለን በማለት የሚያደርጉት ጉዞ ምንም ተስፋ የሚሰጥ አይደለም፡፡ ድክመት ሳይታወቅ እንዴት መሻሻል ይመጣል፡፡

መድረክ እንደ ስሙ ስራው የገነነ አለመሆኑን ባቀረባቸው እጩዎች ብዛት አይተናል፡፡የፓርላማውን ወንበር ግማሽ እንኳን የሚሆን ዕጩ ማቅረብ ያልቻለው ለምንድን ነው? በዚህ ቁጥርስ እናሸንፋለን የተባለው እንዴት ነው? ምርጫ ቦርድ ትክክለኛውን የመድረክ ዕጩዎች ብዛት ሳይናገር በደፈናው ከኢህአዴግ ቀጥሎ ዕጩዎችን ያቀረበ እያለ ሲያሞካሸው የነበረው ለማባበል ወይንስ ለማማለል፡?( መድረክ ያቀረባቸው የዕጩዎች ብዛት እንደዚህ የሚያስብል አልነበረምና) ኢህአዴግ ምርጫ ቦርድንና ጠመንጃውን ካልጣለ አይሸነፍም ከተባለና እንዳልጣለ ከታወቀ በምርጫ የመሳተፉ ፋይዳ ምንድን ነው? ጫናው አባላትን ከማሰር አልፎ ወደ መግደል ሲደርስ በምርጫው መቀጠል ነበረብን ውይ? ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለመባሉ የእኛ አጃቢነት አስተዋጽኦ አላደረገም ወይ?ወደ ፊት የምንቀጥለው እስካሁን በመጣንበት አኳኋንና መንገድ ነው ወይ? ወዘተ እነዚህና መሰል ጥያቄዎች የጉባኤው መነጋገሪያ ሊሆኑ በተገባ ነበር፡፡

ይህም ብቻ አይደለም በመድረክ ስም ተሰባስበው ያሉ ፖለቲከኞች በርግጥ ለለውጥ ከሆነ የሚታገሉት በዚህ መልክ የምንፈልገውን ለውት ማምጣት እንደማይችል ከመቼውም ግዜ በበለጠ ዛሬ ተረድተናል ስለሆነም በዚህ ጉባኤ ውህደት ፈጥረናል፡ በአንድነትና በጽናት ለለውጥ ለመታገል ቆርጠን ተነስተናል ብለው ማወጅ በቻሉ ነበር፡፡ ነገር ግን ከሀገራዊ ለውጥ በላይ የእነርሱ የፓርቲ መሪነት ያሳስባቸዋልና እስሚቀጥለው ጉባኤ ድረስ እንመክራለን ገና አንደራደራለን አሉ፡፡ አሳዛኝ፡፡ ሌላም ታዝበናል፡፡መድረክ ከምስረታው ጀምሮ ከተጣባው የቁጥር በሽታ ዛሬም አልተላቀቅም፡፡ በዚሁ ጉባኤ ዘገባ ላይ አንዴ የአምስት ፓርቲዎች ሌላ ግዜ የሰባት ፓርቲዎች ስብስብ ተብሎ ሲገለጽ ሰምተናል፡፡ ቁም ነገሩ ብዛቱ አይደለም ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡መድረክ ግን የቁጥር ጨዋታ ይወዳል፡፡

ሰማያዊ፤ ይህኛው ፓርቲ ምርጫ ሲወዳደር የመጀመሪያው ነው፡፡ የምርጫ ቦርድ የግዜ ሰሌዳ ባወጣ ሰሞን ነጻነት ለፍትሀዊ ምርጫ የሚል ዘመቻ የጀመረው ሰማያዊ ወደ ምርጫ የገባው ነጻነት መኖሩን አረጋግጦ ነው ማለት አይቻልም፡፡ እናም ወደ ምርጫ የገባው አለምንም ዝግጅት በመሆኑ ምርጫ የገባበት ምክንያት ወዶ ይሁን ተገዶ ግልጽ አይደለም::

ሰማያዊ ያወዳደራቸው እጩዎች ከመቶ የዘለሉ አልነበሩም፡፡ (ትክክኛውን ቁጥር እነርሱም ም/ቦርድም አልተናገሩ) ከእነዚህም አብዛኛዎቹ አንድነት ሲፈርስ ወደ ሰማያዊ የሄዱ ናቸው፡፡ታዲያ በቂ ዝግጅት ሳይደረግ ምርጫ ውስጥ የተገባው ለምንድን ነው? የአንድነት አባላት ወደ ሰማያዊ መሄድ በፓርቲው በኩል የአቋም ለውጥ አስከትሏል ወይ ? ምርጫ ቦርድ ከመቶ በላይ ዕጩዎቻችንን አልመዘግብ አለን ፤ለቅስቀሳ የምንጽፈው ሳንሱር ይደረግብናል፤አባላቶቻችን ወከባ እየደረሰባቸው ፣እየታሰሩ ነው ወዘተ ከተባለ በዚህ አይነቱ ሂደት እስከመጨረሻው አጃቢ ሆኖ መዝለቅ ለምን አስፈለገ? ሰላማዊና ዴሞካራሲያዊ ምርጫ ለመባሉ የእኛ አስተዋጽኦ የለም ወይ? ወዘተ እነዚህና መሰል ጉዳዮችን አንስቶ የሰማያዊ ጉባኤ ሊመክርና ስለ ቀጣዩ የትግል ሂደት ምንነትና እንዴትነት ላይ ውሳኔ ሊያሳልፍ በተገባ ነበር፡፡የወጣቶች እየተባለ የሚነገርለት ፓርቲ በአስተሳሰብም ሆነ በአሰራር ከተለመደው መንገድ ያልወጣ መሆኑን በዚህ ጉባኤው አረጋገጠ፡፡ሳይድግ ያረጀ እንዳይሆንም ያሰጋል፡፡

ብዙ ከሚጠበቅበት ጉባኤ ከጉባኤው ጉልቶ የወጣው ዜና ኢ/ር ይልቃል በድጋሚ ተመረጡ የሚለው ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሥልጣን ሽኩቻ ነበር እንዴ የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡ፓርቲዎችን ሁሉ እግር ከወርች እያሰረ በዳዴ የሚያስኬዳቸው የሥልጣን ጉዳይ ነው፡፡ብዙ ምለው ተገዝተው ከወንበሩ ሲቀመጡ በአንዴ ይለወጡና አጠገቤ አትድረሱ ይላሉ፡፡

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ችግር አዲስ ፓርቲ በመመስረት ወይንም አዲስ ሰው ወደ መሪነት በማምጣት የሚፈታ አይደለም፡፡ወጣት ሽማግሌ ሳይል፣በፖለቲካው ውስጥ የኖረ ወይንም አዲስ የመጣ ብሎ ሳይለያይ ሁሉንም ያጠቃና ስር የሰደደ የአስተሳሰብ በሽታ አለ፡፡ስለሆነም መጀመሪያ የአስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልገናል፡፡ራስን ሳይለውጡ ለውጥ ማምጣት አይቻልምና፡፡ ከአራቱም ጉባኤዎች አዲስ ነገር ማየት ያልቻልነውም በዚሁ በሽታ ምክንያት ነው፡፡

አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአትሌቶች ላይ የሚሰራው በደል እየተሸፈነ ማለፍ ይቁም!!! (ከተማ ዋቅጅራ)

9973910113-large

 

በአትሌቶች ላይ የሚሰራው በደል እውነቱ ይወጣ ዘንድ ይገባል።

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ውስጥ ያለው ችግር ቢዘረዘር ዘርፈ ብዙ ችግር እንዳለበት ይታወቃል። በቦታው ላይ የተቀመጡት ሰዎች እራሳቸው ችግር እስከሚመስሉ ድረስ በምስኪኑ አትሌቶች ላይ ከፍተኛ በደል ፈጻሚ እና ችግር አምጪ ናቸው። በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ቢሮ ሰዎች  ያልተሰደበ፣ ያልተገፋ፣ ያልተንቋሸሸ፣ ያልተንገላታ፣ አትሌት የለም። አትሌቶቹ በዚህ ቢሮ ሰዎች ከሚደርስባቸው ያለአግባብ በደልና ግፍ ያላለቀሰ አትሌት አለ ብዬ ለመናገር ይከብደኛል። በዚህ ቢሮ  ውስጥ የሚሰሩ ሰዎች አትሌቶችን ለማገልገል ሳይሆን በደል ለመፈጸም የተቀመጡ ይመስለኛል። አትሌቶቹ በፌዴሬሽኑ ላይ በየግዜው ቅሬታቸውን ቢያቀርቡም ሰሚ ባለማግኘታቸው በደል ፈጻሚዎችም በስልጣን ላይ ስልጣን ሲሰጣቸው ሲመለከቱ አንገቱን ደፍቶ እየተሰደበ እና እየተናቀ የተሻለ ቀን ይመጣል እያሉ በደላቸውን በሆዳቸው ይዘው ተቀምጠዋል። የተወሰኑት አትሌቶች ዜግነት ቀይረው ሌላ አገር ወክለው መሮጥ የተጀመረውም ፌዴሬሽኑ በሚያደርስባቸው በደል ነው።

Ethiopian-Athletes-Association

ኃይሌ ገብረ ስላሴ የፌዴሬሽኑ ሰዎች የተሰጠው ዘለፋ <<አንተ አርጅተኸል ከእንግዲ ወዲያ ምንም አታመጣም>> ብለው ሲተቹት የማራቶንን ሪከር ሰብሮ  አሳፍሯቸዋል።

ቀነኒሳ በቀለ ታዋቂ ከመሆኑ በፊት ወደ ትራክ ትሬኒግ ለመስራት ሲመጣ እግሩ ወፍራም ስለነበረ የተሰጠው ዘለፋ<< ይሄንን እግር ይዘህ ልትሮጥ ነው የመጣኸው? አንተ እሯጭ አትሆንም ይልቅስ ሂድና አገርህ ገብተህ እርሻህን እረስ>> የሚል ነበረ።

ብርሃኔ አደሬ በአንድ ወቅት በፊት ከነበራት ብቃቷ ትቀንሳለች የተሰጣት ትችት ግን ልብ የሚያደማ ነው። <<ከአሁን በኋላ አንቺ መሮጥ አትችይም ሂጂና ኩበትሽን ጠፍጥፊ>> የሚል ነበረ። ብርሃኔ በጣም እልኽኛ ስለነበረች ብቃቷን መልሳ እስከ አለም ሻንፒዮና ድረስ ለመሳተፍ በቅታለች።

ፀጋዬ ከበደ የመጀመሪያውን የውጪ ጥሪ መቶለት ከፌዴሬሽኑ ወረቀት ሊያጽፍ ሲሄድ <<አንተ አጭር አሁን አንተ ማራቶን እሯጭ ነኝ ብለህ ነው የመጣኸው>> እያሉ ይቀልዱበት ነበረ  ፀጋዬ ግን እኔ ምንም የለኝም እባካችሁ እድሌን አታስመልጡብኝ እያለ ሲለምናቸው እነሱ ግን ይሳለቁበት ነበረ።

ተፈሪ የሚባል አንድ አትሌት ከክፍለ ሃገር መቶ ማራቶን ይወዳደራል ያደረገው ቁምጣ የእግር ኳስ ተጫዋች ቁምጣ ነው። በዚህ ውድድር ላይ ሰባተኛ ይወጣና ውድድሩን ይጨርሳል በኋላ ላይ ቁጥር ሊቀበል ሲሄድ አመናጭቀው አባረሩት በኋላለይም ፌዴሬሽን ሄዶ ሲያናግራቸው <<ሂድ አንተ ዝም ብለህ ከመንገድ መተህ ማራቶን እሯጭ ነኝ ትላለህ ሂድ ውጣ>> ብለው አመነጫጭቀውት ሲናገሩት ተፈሪ ግን አንድ ነገር ብሎአቸው ነበረ የወጣው ትሰማላችሁ አላቸው የሚቀጥለውን ማራቶን ውድድር ሳሸንፍ ምን እንደምትሉኝ አያለው ብሎ ይወጣል። በሌላ የማራቶን ውድድር ላይ በዛው ቁምጣ እሮጦ ሁለተኛ በመውጣት ውድድሩን ይጨርሳል ያላቸው ነገር ቢኖር ዛሬስ ቁጥሩን አትሰጡኝም ዛሬስ ከመንገድ ነው የመጣሁት ትሉኝ ይሆን? ብሎአቸው ብቃቱን አሳይቷል።

ከላይ እንደገለጽኩት እነዚህን ታላላቅ እና ብርቅዬ አትሌቶቻችንን ለምሳሌነት ጠቀስኳቸው እንጂ በፌደሬሽኑ  ሰዎች  በደል ያልደረሰበት እና ያላለቀሰ  አትሌት አለ ብዬ ለመናገር ይከብደኛል።

አንድ አትሌት በክለብ ታቅፎ መስራት ከጀመረ በክለቡ ውስጥ ጥሩ ተፎካካሪ ከሆነ ኢንተርናሽናል ውድድር እንዳይወዳደር የሚከለክለው ህግ እስከሌለ ድረስ የውጪ ውድድሮችን የመጋበዝ እድሉን ካገኘ ፌዴሬሽኑ አትሌቱ በፌዴርሽኑ ስር ታቅፈው ከሚሰሩት ክለብ ውስጥ መሆኑን ጠቅሶ በሚጻፍ ፋንታ ወረቀት በመከልከል የአትሌቶቻችንን እድገት እየቀጩት ይገኛሉ። አትሌቶቹም እራሳቸውን ችለው ለአገርም እንዳይጠቅሙ አድርጎ በማምከን አዳዲስ አትሌቶች እንዳይወጡ እያደረገ ነው። አዲስ አትሌት ከማየት ይልቅ በኛ አገር የተለመደው ሁለት ወይም ሶስት አትሌቶች ላይ ትኩረት በማድረግ የአትሌቲክስ አገር የነበረችውን አገራችንን ምንጩን  እያደረቁት ይገኛሉ። ለዚህም ደግሞ ትክክለኛው መፍትሄው በአትሌቶቹ ላይ  በደል  በመስራት ያሉትን ወንጀለኞች በህግ ተጠይቀው መጪው ፌዴሬሽኑን የሚረከበው አካል በንጹ አዕምሮ  እና ተጠያቂነት ባለው ስራ እንዲሰራ ማድረግ ሲቻል ሊጠፋ የተቃረበው አትሌታችንን ማዳን ይቻላል።

በዚህ አጋጣሚ አንድ ነገር ጠቆም አድርጌ ልለፍ

በፌዴሬሽኑ ህጋዊ እውቅና ተሰጥቶአቸው አትሌቶችን በመመልመል በማናጀር ስር በማቀፍ የሚያሰሩ ግለሰቦች አሉ። እነዚህ ግለሰቦች ከፌዴሬሽን ሶዎች ጋር ጥብቅ ሚስጢራዊ ስራ  አላቸው ያም ህገ ወጥ አሰራር ነው ። ለዛሬ በዚህ ጉዳይ ላይ ጥቂት ልበል ወደፊት ግን በሰፊው እመለስበታለው።

በፌዴሬሽኑ በኩል እና  በፌዴሬሽኑ እውቅና በተሰጣቸው እንዚህ ማናጀሮች ተብለው ሚጠሩት እየተሰራ ያለው ስራ አሳፋሪ እና መንግስትም ሆነ ህብረተሰቡ በአትክሮት ሊያየው የሚገባ ጉዳይ ነው። በፌዴሬሽኑ ወይም በማናጀሮች በኩል ወደተለያዩ  አገራት ውድድር ለማድረግ በስራቸው የሚሰለጥኑትን አትሌቶች ይልካሉ። ይሄ የሚደገፍ እና የሚያበረታታ ጥሩ ስራ ነው ወደ ውጪ ወጥቶ  ለመወዳደር ጥሩ አጋጣሚ ነውና። ችግሩ ያለው በአትሌቶች ስም የሚደረገው ወንጀል ነው። ፌዴሬሽኑ ወይም ማናጀሮች ከተለያየ አገራት ለአትሌቶች የውድድር ግብዛ ጥሪ ማስመጣት ይችላሉ በዚህ መሃል ለምሳሌ አምስት አገር በአንድ ወር ውስጥ ቢያስመጡ ለዚህ ውድድር የሚሆኑ እሯጮች አንድ አገር ላይ አራት ሰው ቢልኩ ለአምስቱ አገር ሃያ እሯጮችን መላክ ይችላሉ። ለሁሉም አትሌቶች እኩል የሆነ አገልግሎት በመስጠት የውጪ የመወዳደር እድላቸው የተዘጋ ባይሆን ከበቂ በላይ አትሌቶችን ማፍራት እንደሚቻል ይታወቃል። ነገር ግን በጠበበው የውጪ እድል ላይ በአትሌቶች ስም ፌዴሬሽኑ እና ማናጀሮች የሚሰሩት ቢዝነስ ከአምስት አገር ሊልኳቸው ከታሰቡት ሃያ አትሌቶች መካከል ከግማሽ የሚበልጠው እሯጭ ያልሆኑ ሰዎች ዳጎስ ያለ ገንዘብ ከፍለው የሚሄዱ አልያም የፌዴሬሽኑ ወይም የማናጄሩ ዘመድ የሆኑት በህገ ወጥ መንገድ  በአትሌቶቹ ስም የሚሰራ ወንጀል ነው። አትሌቶቹ ሲመለሱ እነዛ ግን በዛው የሚቀሩ ናቸው። እውነተኛው እና ደሃው አትሌት ጥሪ አስመጥቶ  አልያም ጥሪ የሚያስመጣለት አጥቶ በፌዴሬሽን ቢሮ በራፍ ላይ እና ማናጀሮቹ ላይ ሲያለቅሱ የሚያጥላላ ስድብ ከመስደብ በተጨማሪ በስፖርቱ ተስፋ እንዲቆርጡ የሚያደርግ ድርጊትን ሲያደርጉ እስከዛሬ ድረስ ዝም መባላቸው ኢትዮጵያውስጥ ህግ እንደሌለ የሚያሳይ ጉዳይ ነው። አትሌቶቹ ላይ የሚደርሰውን በደል ለማወቅ የሚፈልግ ማንኘውም አካል ከጀማሪው አትሌት እስከ ታዋቂዎች አትሌቶችን ጠይቆ እውነቱን መረዳት ይቻላል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ከሞሞቱ በፊት ፌዴሬሽን ያሉት ኮሚቴዎችን በአትሌቶቹ ላይ ለሚሰሩት ስህተት ተጠይቀው አትሌቲክሱን የሚያሳድጉ በቦታው ሊይዙት ይገባል እላለው።

ከተማ ዋቅጂራ

Email- waqjirak@yahoo.com

– See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/9975#sthash.CTXIG1uc.dpuf

ኢትዮጵያውያን ጦማርያን በዝንጀሮ ችሎት

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

የወያኔ ኢፍትሐዊነት በዝንጀሮው ፍርድ ቤት፣

ባለፈው ሳምንት በጥቅል ስማቸው “የዞን 9 ጦማሪያን” (ከዋና መዲናይቱ እምብርት በስተደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ በጥቂት ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ከሚገኛው እና ንጹሀን ዜጎችን በማሰቃየት በአስከፊነቱ ከሚታወቀው ከአምባገነኑ የመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት 8ኛ ህንጻ/Block ቀጥሎ የተገነባው ህንጻ) እየተባሉ የሚጠሩት ወጣት ኢትዮጵያውያን ጦማሪያን እ.ኤ.አ ሚያዝያ 2014 በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ጊዜ ጀምሮ 33 ጊዜ እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ ለሚጠራው ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ስርዓት የዝንጀሮው ፍርድ ቤት ችሎት ቀርበው ነበር፡፡Ethiopian Bloggers in Kangaroo (Monkey) court

(ፖሊስ በጥርጣሬ የሚታይን ሰው በቁጥጥር ስር በማዋል እና በወንጀል የተጠረጠረን ሰው በእስር ቤት ካሰረ በኋላ ተጠርጣሪው ፈጽሟቸዋል ለተባሉት የውንጀላ ጥፋቶች መረጃዎችን ለመፈለግ እና ለማሰባሰብ በሚል ከሕግ አግባብ ውጭ ለሆነ ድርጊት ለወራት ከዚያም አልፎ ለዓመታት በእስር ቤት በማማቀቅ የሚያቆይ ሀገር አለ ከተባለ ብቸኛይቱ ሀገር ኢትዮጵያ ናት!)

የዘገዬ ፍርድ እንደተነፈገ ይቆጠራል፡፡ 33 ጊዜ የተንዛዛ የችሎት የጊዜ ቀጠሮ በመስጠት የዘገዬ ፍርድ 33 ጊዜፍትሕ እንደተነፈገ ይቆጠራል፡፡

ወጣት ጦማሪያኑ ለፍትህ አካል ከመቅረባቸው በፊት ለበርካታ ጊዚያት በእስር ቤት ታጉረው እየማቀቁ፣ ዋስትና ተከልክለው፣ ውጤታማ የሆነ የሕግ የምክር አገልግሎት እንዳያገኙ ተነፍገው፣ ፈጣን የሆነ የፍትሕ አገልግሎት ማግኘት አለመቻላቸው፣ ከአድልኦ የጸዳ እውነት አፈላላጊ አካል አለመመደብ እና ለ33 ጊዜ የተንዛዛ የችሎት የጊዜ ቀጠሮ መስጠት በፍትሕ አካል ላይ እንደመቀለድ እና እንደተነፈገ ፍትሕ ይቆጠራል፡፡

ባለፈው ሐምሌ 2015 ባራክ ኦባማ ኢትዮጵያን እንደሚጎበኝ በመገመት የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ሁለት ጦማሪያንን እና ሶስት ጋዜጠኞችን ከማጎሪያው እስር ቤት ባልተሰበ እና ባልተጠበቀ ሁኔታ ለቋቸዋል፡፡ ለማድለብ እንደተዘጋጀ ሰንጋ ሲፈልግ የሚያስር ሲፈልግ የሚፈታ እንደዚህ ያለ አምባገነን ስርዓት በኢትዮጵያ ካልሆነ ሌላ በየትኛው ሀገር ይገኛል!

እ.ኤ.አ ከ2006 ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ስለወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ስርዓት የዝንጀሮ ፍርድ ቤት ትችቶችን ስጽፍ እና ሳቀርብ ቆይቻለሁ፡፡

“የዘበት ፖሊሶች፣ አቃቤ ሕጎች እና ዳኞች ሚና በፖሊስ መንግስት” በሚል ርዕስ እ.ኤ.አ ታህሳስ 2006 የመጀመሪያውን ትችቴን አቅርቤ ነበር፡፡ ያ ትችት እ.ኤ.አ የ2005 ሀገር አቀፍ ምርጫን ተከትሎ ተከስቶ በነበረው ሁከት ሳቢያ በአሁኑ ጊዜ በህይወት በሌለው በአምባገነኑ በመለስ ዜናዊ ትዕዛዝ በቃሊቲ የማጎሪያ እስር ቤት ታስረው በነበሩት “የቃላቲ ተከላካዮች” (የተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎች) ላይ እየተካሄደ ባለው የችሎት ሂደት ላይ ምርመራ የሚያደርግ ነበር፡፡

እ.ኤ.አ ታህሳስ 2007 “የጦጣ የፍትሕ ችሎት በዝንጀሮው ፍርድ ቤት“ በሚል ርዕስ በዚያን ጊዜ የአክሽን ኤይድ ዓለም አቀፍ በኢትዮጵያ ማኔጀር/Manager of Action Aid International in Ethiopia በነበሩትና በአሁኑ ጊዜ ደግሞ በሂዩማን ራይትስ ዎች የአፍሪካ ዴስክ ዋና ክፍል ኃላፊ /Executive Director of the African Division of Human Rights Watch ሆነው ባማገልገል ላይ ባሉት በአቶ ዳንኤል በቀለ እና የማሕበራዊ ፍትሕ በኢትዮጵያ ድርጅት/Organization for Social Justice in Ethiopia መሰራች እና አመራር ሰጭ በነበሩት በአቶ ነጻነት ደምሴ ላይ ላይ ተመስርቶ የነበረውን የፍትሕ ሂደት የሚመረምር ትችት አቅርቤ ነበር፡፡ የእነርሱን የፍትሕ ሂደት የፍራንዝ ካፍካን የፍርድ ሂደት ከሚዘግበው የጆሴፍ ኬ.ን አስቀያሚ እና ተስፋ አስቆራጭ ልብወለድ የፍትሕ ታሪክ ጋር በማነጻጸር አቅርቤ ነበር፡፡

ለበርካታ ዓመታት ስለወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የተሰበጣጠረ መንግስት እና በአብዛኛው ግን በውጭ የገንዘብ ድጋፍ እርዳታ ላይ ተንጠልጥሎ ስለሚገኘው አምባገነን ስርዓት እንዲሁም ስለዝንጀሮው የፍርድ ስርዓቱ ብዙ ትችቶችን ስጽፍ ቆይቻለሁ፡፡

እ.ኤ.አ ሰኔ 2014 “የኢትዮጵያን ጦማሪያን ማን ይፈራቸዋል?“ በሚል ርዕስ በዞን 9 ጦማሪያን ላይ እየተፈጸመ ያለውን የሕግ ሸፍጥ የሚያጋልጥ ትችት አቅርቤ ነበር፡፡

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብን የይስሙላ ኢፍትሐዊ ስርዓት ለመግለጽ ከተንኮል በመነጫ ሳይሆን ከገለጻትክክለኛነት ፍላጎት አንጻር የዝንጀሮ እና የጦጣ ፍርድ ቤት የሚሉ ተመሳስሎዎችን እጠቀማለሁ፡፡

“የዝንጀሮ (ካንጋሮ ) ፍርድ ቤት” የሚለው ሀረግ የአውስትራሊያ አጥቢ እንስሳት ከሆኑት ማርሱፒያል ካንጋሮዎች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የለውም፡፡

ይህ ሀረግ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በምዕራብ አሜሪካ እራሳቸውን የሾሙ የሸፍጥ፣ ሀፍረተቢስ እና አታላይ የፍትሕ ሂደትን ያራምዱ የነበሩ ሰዎችን ለመግለጽ በስራ ላይ የዋለ ነው እየተባለ ይነገርለታል፡፡

ይህ ሀረግ አብዛኛውን ጊዜ ከሚከተሉት ጋር አንድ ዓይነት ትርጉም እንዳለው ሆኖ ሲገለጽ ቆይቷል፣

1ኛ) የሕግ እና የፍትሕ መርሆዎች ወደ ጎን የተጣሉበት ወይም ደግሞ የተዛቡበት አስመሳይ የፍርድ ችሎት፣

2ኛ) ዓይን ባወጣ መልኩ እና ሆን ብሎ ታስቦበት ዕውቅና ያላቸውን የሕግ ወይም ደግሞ የፍትህ መርሆዎችን እና መስፈርቶችን ወደ ጎን ገሸሽ አድርጎ መተው፣

3ኛ) የፍርድ ቤቱን ሕጋዊ ወይም ደግሞ የስነምግባር ግዴታዎችን ሆን ብሎ ወደ ጎን የሚተው ሕጋዊ የፍትሕ ስልጣን ያለው ፍርድ ቤት፣ እና

4ኛ) የፍርድ ውሳኔው በእርግጠኝነት የፍርድ ችሎቱ ሂደት ከመጀመሩ በፊት የተወሰነ እና የታወቀ ቢሆንም እንኳ “የፍርድ ሂደቱ ለሕዝብ ፍትሐዊ እና ትክክለኛ ቅርጽ ያለው እንዲመስል” እየተነበዬ የሚሰራ ፍርድ ቤት የሚሉት ናቸው፡፡

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የፍርድ ሂደት ስርዓት ከዚህ በላይ ከተገለጹት ሁሉም ትርጉሞች ጋር መሳለመሳ ነው፡፡

ይህ ሀረግ በዩናይትድ ስቴትስ የሕግ ታሪክ ውስጥ በጣም ጠቃሚ እንደምታ ካላቸው የወንጀል የሕገ መንግስት ጉዳዮች መካከል የእራሱን መንገድ አግኝቷል፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ ጠቅላይ ፍርድ ቤት “ፖሊሶች ጉዳዮችን በእራሳቸው እጆች የሚይዙበትን ሁኔታ፣ የጥቃት ሰለባዎችን የሚይዙበትን መንገድ፣ የጥቃት ሰለባዎች በግድ የእምነት ቃል እስኪሰጡ ድረስ የሚደበድቡበትን እና በኃይል የሚመቱበትን ጥንታዊ የሆኑ የሕግ ጉዳዮች አወገዘ፡፡ ክስ የቀረበበት ማንኛውም ሰው ጉዳዩ በይስሙላ የዝንጀሮ ፍርድ ቤት ሳይሆን ሕጋዊ በሆነ የፍትህ አካል የመታየት እና የመዳኘት መብት አለው፡፡”

እንግዲህ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የይስሙላ የዝንጀሮ ፍርድ ቤቶች ዋና መለያ ባህሪ ይኸው ነው፡፡ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ወሮበላ ዘራፊ ፖሊሶች በፖለቲካ ወንጀል የሚጠረጥሯቸውን ንጹሀን ዜጎች በፖለቲካ ኃላፊ ጌቶቻቸው ትዕዛዝ መሰረት በቁጥጥር ስር ያውላሉ፣ ጭካኔ በተመላበት ሁኔታ ድብደባ በመፈጸም በግድ የእምነት ቃል እንዲሰጡ ያደርጋሉ፣ ክስ ሳይመሰረት በእስር ቤት ታጉረው እንዲቆዩ ያደርጋሉ፣ የሕግ የምክር አገልግሎት እንዳያገኙ ያደርጋሉ፣ እንዲሁም በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የሚሾሙ ሸፍጠኞች የይስሙላ የፍርድ ሂደቱን እስከሚጀምሩ ድረስ እስረኞችን ከወዲያ ወዲህ እያመላለሱ ያሰቃያሉ፣ ፈጣን የሆነ የፍትሕ አገልግሎት እንዳያገኙ ያደርጋሉ፣ አይጦችና ቅማል ቱሃን ሌላም ተውሳክ  በሚተራመሱበት እና ጽዳቱ ባልተጠበቀ ክፍል (በረት ማለቱ ይቀላላ) ውስጥ ለወራት ወይም ደግሞ ለዓመታት በእስራት እንዲማቅቁ ያደርጋሉ፡፡ ይህ ሁሉ ህግን ያልተከተለ ድርጊት የሚፈጸመው ሸፍጠኛ የሆኑ እና ለርካሽ ጥቅም ሲሉ ለስርዓት ያጎበደዱ ዳኞች አቃብያነ ሕግ ተብዬዎች የቆሸሸ የስብዕና ድሪቶ መንፈሳቸውን በመጠቀም በንጹህን ተጠርጣሪዎች ላይ የሀሰት ማስረጃዎችን ፈብርከው እስከሚያጠናቅቁ ድረስ መጨረሻ የሌለው የጊዜ ቀጠሮ እየሰጡ እጅ እና ጓንት ሆነው ፍትህን በመደፍጠጥ በንጹሀን ዜጎች ላይ ደባን እና ሸፍጥን ስለሚሰሩ ነው፡፡

በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ፕላኔት (ዓለም) ላይ የይስሙላ የዝንጀሮ/የጦጣ ፍርድ ቤቶች ይኖራሉ፡፡

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ኢፍትሐዊ ስርዓት የዝንጀሮ/የካንጋሩ ችሎት በማለት ለትዮጵያውያን አንባቢዎቼ ተመሳስሏቸውን ለመግለጽ እጠቀማለሁ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የዝንጀሮ የፍርድ ስርዓት የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ አመራሮች እና አባላት ተቀናቃኞቻቸውን ለማጥቂያነት የሚጠቀሙባቸው መሳሪያዎቻቸው መሆናቸውን ላሰምርበት እፈልጋለሁ፡፡

በዞን 9 ጦማሪያን የፍርድ ሂደት ላይ እንደዚህ ያለ የማስመሰል የፍትሕ ሸፍጥ እየተካሄደ በመሆኑ ምክንያት ነው በአሁኑ ጊዜ ዋና ዋና የሆኑት ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እኩይ ድርጊቱን በማውገዝ ላይ የሚገኙት፡፡

በእርግጥ ከፖለቲካ እና ትክክለኛ ከመሆን አንጻር ማናቸውም ቢሆኑ ስርዓቱን የበቀል መወጫ መሳሪያ የዝንጀሮ ፍርድ ቤት ወይም ደግሞ የጦጣ ፍርድ ቤት ብለው ለመጥራት ድፍረቱ የላቸውም፡፡

ሆኖም ግን የዘንጀሮ/የጦጣ ፍርድ ቤት በየትኛውም በሌላ ስያሜ ቢሰየምም ያው የዝንጀሮ/ጦጣ ፍርድ ቤት ከመሆን የሚለየው ነገር በፍጹም የለም፡፡ በሌላ አባባል ለመቆንጀት ሲባል ፉንጋዋ ዓሳማ የከንፈር ቀለም ብትቀባም እንኳ በዕለቱ መጨረሻ የከንፈር ቀለሙ ያው ፉንጋ ዓሳማነቷን አይቀይረውም፡፡

ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የዝንጀሮ/የጦጣን ፍርድ ቤት ስርዓት የፖለቲካ ተቀናቃኞቹን ለማጥቃት የሚጠቀምበት መሳሪያ ነው በማለት ገልጾታል፡፡ ሂዩማን ራይትስ ዎች የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ላይ እንዲህ በማለት ተቃውሞውን አቅርቦበታል፣ “ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም፡፡“

የጋዜጠኞች ተከላካይ ኮሚቴ (ጋተኮ) ሽብርተኝነትን ከጋዜጠኝነት ጋራ በማቀላቀል በመንግስት እየተደረገ ያለውን ሰላማዊ ዜጎችን የማሰቃየት የፍርድ ሂደቱን አውግዟል፡፡

ፍሪደም ሀውስ/Freedom House የተባለው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት በጦማሪያን ላይ የተመሰረተው የክስ ጉዳይ በእውነታ ላይ ያልተመሰረተ ቅንነት የጎደለው ነው፣ መንግስት የግንቦቱ ምርጫ እየተቃረበ በሚመጣበት ወቅት በዴሞክራሲ ወትዋቾ ላይ ፖለቲካዊ እንደምታ ያለው የሀሰት ክስን በመፈብረክ ጥቃት በመሰንዘር ላይ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ይህንን ኢፍትሐዊ የሆነ ድርጊት ለማስቆም ለጋሽ ድርጅቶች በመንግስት ላይ ጫና በመፍጠር ድርጊቱን ማስቆም ይኖርባቸዋል ብሎ ነበር፡፡

እ.ኤ.አ ጥር 2015 የአሜሪካ መንግስት መምሪያ በ6 ጦማሪያን እና በ3 ጋዜጠኞች ላይ በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የተሰጠው የፍርድ ውሳኔ ላይ የጸረ ሽብር አዋጁ እየተተገበረ መሆኑ አሳስቦኛል በማለት ስጋቱን ገልጾ ነበር፡፡

መምሪያው እንዲህ በማለት አውጆ ነበር፣ ውሳኔው ነጻ እና ለሁሉም ክፍት የሆነ የሜዲያ ከባቢ አየር እንዳይሰፍንየሚያደርግ፣ .. ግንቦት 2015 በኢትዮጵያ ታማዕኒነት ያለው እና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዳይካሄድያደርጋል፡፡

እ.ኤ.አ ሰኔ 2015 የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ በግንቦት የተካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ መቶ በመቶ አሸንፊያለሁ በማለት አወጀ፡፡

እ.ኤ.አ ሀምሌ 2015 ባራክ ኦባማ ኢትዮጵያ ከደረሰ በኋላ “በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠው የኢትዮጵያ መንግስት“ በማለት ስምምነቱን ገልጿል፡፡ (ኦባማ ይህንን ነገር የተናገረ የአታላይነቱን ጉብዝና ለማሳየት ፈልጎ ነውን?)

በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ፕላኔት ውስጥ የመጦመር ወንጀለኝነት፣

በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የዝንጀሮ/ጦጣ ፍርድ ቤት የሸፍጥ ክስ የተመሰረተባቸው ተከላካይ ጦማሪያን የሚከተሉትን ያካትታል፡ በፈቃዱ ኃይሉ ተጫኔ፣ ናትናኤል ፈለቀ አበራ፣ ማህሌት ፋንታሁን ተፈራ፣ አጥናፍ ብርሀኔ አያሌው፣ ዘላለም ክብረት ቤዛ፣ አቤል ዋቤላ ሱጌቦ፣ አስማማው ኃይለጊዮርጊስ ግዛው፣ ኤዶም ካሳዬ ገላን፣ ተስፋለም ወልደዬስ አራጌ እና (በሌለበት የሸፍጥ ክስ የተመሰረተበት ሶሊያና ሽመልስ ገብረማርያም) ናቸው፡፡

ተከላካይ ጦማሪዎች በኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ እና በወያኔ ጸረ ሽብር ሕጉ አዋጅ ቁጥር 652/2009 በሁለት ክሶች በአንድ ላይ ከስ ተመስርቶባቸዋል፡፡

በአንደኛው ክስ “ዋና ወንጀለኞች” ወይም ደግሞ በወንጀለኛ ሕጉ አንቀጽ 32 በተራ ቁጥር 1 እና 2 ላይ የተጠቀሰውን በመተላለፍ ዋና ወንጀል የመፈጸም ሙከራ የሚል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡

በሁለተኛው ክስ ላይ ደግሞ ተከላካዮቹ በወንወጀለኛ መቅጫ ሕጉ በአንቀጽ 27 በተራ ቁጥር (1 እና 2) የተጠቀሱትን በመተላለፍ (ወንጀል የመፈጸም ሙከራ)፣ በአንቀጽ 38 በተራ ቁጥር (1) በሕገ መንግስቱ ወይም ደግሞ በመንግስት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎች የሚሉ ክሶች ተመስርተውባቸዋል፡፡

የውንጀላ ክሶቹ እንደማስረጃ ሊሆኑ የሚችሉ በርካታ ገጾች ያሏቸውን የእምነት መግለጫዎች ፈርመዋል ተብሏል፡፡ የገጾቹ ብዛትም እንደተከላካዮቹ ፊርማ እንደሚከተለው ቀርበዋል፡ በፈቃዱ ኃይሉ ተጫኔ (31 ገጾች)፣ ናትናኤል ፈለቀ አበራ (27 ገጾች)፣ ማህሌት ፋንታሁን ተፈራ (12 ገጾች)፣ አጥናፍ ብርሀኔ አያሌው (16 ገጾች)፣ ዘላለም ክብረት ቤዛ (16 ገጾች)፣ አቤል ዋቤላ ሱጌቦ (12 ገጾች)፣ አስማማው ኃይለጊዮርጊስ ግዛው (13 ገጾች)፣ ኤዶም ካሳዬ ገላን (10 ገጾች) እና ተስፋለም ወልደዬስ አራጌ (13 ገጾች፣ እና በሌለበት ክስ የተመሰረተበት ሶሊያና ሽመልስ ገብረማርያም ናቸው፡፡)

ተከላካዮቹ በውንጀላ የእምነት ቃል እንዲሰጡ በሚደረግበት ጊዜ የሕግ ምክር አገልግሎት እንዳያገኙተከልክለዋል። 

ለሕዝብ የህሊና ዳኝነት ክፍት ለማድረግ እንዲቻል በማሰብ በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የሸፍጥ ውንጀላ የተከሰሱት ጦማሪያን በዝርዝር እና የቀረቡባቸው የጽሁፍ እና የቁስ ማስረጃዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡

1) በፈቃዱ ኃይሉ ተጫኔ፡ የተመሰረተበት ክስ “የሀገር ውስጥ የሚስጥር የሽብር ድርጅት ማቋቋም“ እና “ለአባላቱ ዕቅድ ማውጣት እና የሚከናወኑ ተግባሮችን እና ኃላፊነቶችን ለአባላቱ መመደብ“ የሚሉ ናቸው፡፡ በፍቃዱ መንግስትን በኃይል ለማስወገድ በማሰብ “የሳጥን ደህንነት ” እየተባሉ የሚጠሩትን ጽሁፎችን ወደ ኮድ የሚለውጡ መሳሪያዎችን እና የግንኙነት ስልጠናዎችን በመውሰድ ግንቦት 7 እየተባለ የሚጠራውን “አሸባሪ” ድርጅት ለማገዝ ስትራቴጂ በመንደፍ ድጋፍ አድርጓል የሚል ነው፡፡

በበፈቃዱ ላይ የቀረበው የሰነድ ማስረጃ የሚከተሉትን ያካትታል፡ 31 ገጽ የእምነት ቃል እና ከእራሱ ላፕቶፕኮምፒውተር እና ከቤቱ የተሰበሰበ መረጃ፡ “ለለውጥ ፈላጊዎች እና ለጀግኖች” በሚል ርዕስ የተጻፈ ጽሁፍ እና “ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ለትግራይ እንዴት ሕጋዊ እንደሆነ”፣ “80 ሚሊዮን እስከምንሆን ድረስ እንዋጋለን“፣ “እኛ ህብረት ከፈጠርን አምባገነኖች ምንድን ሊሆኑ ይችላሉ“፣ “በድረ ገጾች የሚለቀቁ ጽሁፎችን የመመርመር ዘመቻ ይቁም“፣  “ዋኤል ጎኒም ኢትዮጵያዊ ቢሆን ኖሮ የሚል (ከግብጽ ምዕናባዊ የኢንተርኔት አክቲቪስት ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ-18 ገጾች“፣ “የሲቪል ነጻነቶች ተሟጋቾች የስልጠና ሰነድ“፣ “መንግስት አለን? ወይም ደግሞ መንግስት የማን ነው? እና ምን ዓይነት ነው? -10 ገጾች“፣ “የኢሕአዴግ አባል ያልሆነ ዳኛ ይኖራልን?”፣ “የቴሌኮም የሸፍጥ ሕግ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነትን ለመሸበብ የወጣ መሳሪያ – 12 ገጾች“፣ “የተሰበሰበ የሕዝብ አስተያየት እና የድረ ገጽ ዘመቻ ዕቅድ – 3 ገጾች“፣ እና “ለዘጋቢ ፊልም ዝግጅት በኢትዮጵያ ሀሳብን በነጻ በመግለጽ ሁኔታ ላይ ያተኮሩ በእጅ የተጻፉ ቃለመጠይቆች ዝርዝር“ በሚሉ የተለያዩ ርዕሶች የተዘጋጁ ጽሁፎች ናቸው፡፡

2) ናትናኤል ፈለቀ አበራ፡ የአሸባሪ ቡድኑ ዋና አቀነባባሪ የሚል የውንጀላ ክስ ተመስርቶበታል፡፡ “በሀገር ውስጥ የሚስጥር የሽብር ድርጅት ማቋቋም“ እና “ሁሉንም የሽብር ቡድኑን እንቅስቃሴዎች ማስተባበር“፣ “ናትናኤል ከግንቦት 7 ጋር በመተባበር ሕብረተሰቡ የአመጽ ድርጊት እንዲጀምር በርካታ ስልጠናዎችን ለመስጠት ተነሳሽነትን በማሳየት ማደራጀት፣ ሙሉ ተሳታፊ መሆን፣ ስራዎችን ሁሉ ማሳለጥ” የሚሉ ውንጀላዎች ቀርበውበታል፡፡

የጽሁፍ ማስረጃ ተብለው የቀረቡት የሚከተሉትን ያካትታል፡ የእምነት ቃል የተሰጠባቸው 27 ገጾች፣ “ከላፕቶፕ ኮምፒውተሩ የተሰበሰቡ እና ከኢሜይል ድረ ገጽ የወረዱ/download የተደረጉ ጽሁፎች“፣ ሌሎች ሰነዶች ማለትም በሚከተሉት ርዕሶች የተዘጋጁ፣ “ዋኤል ጎኒም ኢትዮጵያዊ ቢሆን ኖሮ የሚል (ከግብጽ ምዕናባዊ የኢንተርኔት አክቲቪስት ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ-18 ገጾች – በበፈቃዱ ኃይሉ የተጻፈ“፣ “ዳቦ እና ነጻነት በሚል፣ ለጽሁፍ ምርመራ ይቁም ዘመቻ የተጻፈ“፣ “የጽሁፍ ምርመራ ዋጋ – 8 ገጾች ጽሁፍ“፣ “አሁን በህይወት የሌለውን መለስ ዜናዊን የሚተች የግንቦት 7 ደብዳቤ – 4 ገጾች“፣ “ከቢዝነስ እና ኮንስትራክሽን ባንክ ገንዘብ የተቀበለበት ደረሰኝ“፣ “በኢንተርኔት የደህንነት ጉዳይን በማስመልከት ከሶሊያና ሽመልስ ፓስፖርት ጋር በተያያዘ የተደረገ የኢንተርኔት መልዕክት ልውውጥ – 26 ገጾች“፣ “ስለኢትዮጵያ በናትናኤል ፈለቀ በእጅ ጽሁፍ የተዘጋጀ ግጥም እና ከቤቱ የተሰበሰበ – 1 ገጽ“ በሚሉ ርዕሶች የተዘጋጁ ናቸው፡፡

3) ማህሌት ፋንታሁን ተፈራ፡ “የግንቦት 7ን አሸባሪ ቡድን ዓላማዎች ለማስፈጸም በርካታ የሚስጥር መረብ በመዘርጋት ተባባሪ ሆና መገኘት”፣ “በርካታ የሆኑ የአመጽ እና የሽብር ስልጠናዎችን በማዘጋጀት እና በመሳተፍ ትብብር አድርጋለች“ የሚሉ ውንጀላዎች ቀርበውባታል፡፡

በማህሌት ላይ የቀረቡባት የጽሁፍ ማስረጃዎች የሚከተሉትን ያካተተ ነው፡ “የእምነት ቃል እንድትሰጥ የተደረገችበት – 12 ገጾች”፣ እንደዚሁም ሌሎች ማስረጃዎች “ከኮምፒውተር የተሰበሰቡ ሰነዶች“፣ “የኃይል አመጽ ለመቀስቀስ መንቀሳቀስ እና የምጣኔ ሀብት ዕድገቱን ዕውቅና ያለመስጠት የሚሉ ጹሁፎችን ያካተተ – 2 ገጾች“፣ እና “ከሲዲ እንዲታተም የተደረገ የኦነግ የፖለቲካ ፕሮግራም – 22 ገጾች“ የሚሉ የውንጀላ ክሶች ናቸው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ባልታሰበ እና ባልተጠበቀ ሁኔታ ክሱ እንዲቋረጥ ተደርጎ .. ሀምሌ 9/2015 ከማጎሪያውእስር እንድትለቀቅ ተደርጓል፡፡

4) አጥናፍ ብርሀኔ አያሌው፡ ሆን ብሎ እያወቀ በሚስጥር ከሚንቀሳቀሰው የግንቦት 7 አሸባሪ ቡድን ጋር በሚድብቅ ተሳትፎ አድርጓል“፣ “የመንግስት የደህንነት ኃይሎችን እንዴት አድርጎ መቀስቀስ እንደሚቻል እና በመካከላቸው የጎሳ ክፍፍልን በመፍጠር ሁከት ለማስነሳት እና እራስን እንዴት አድርጎ ፊትን በመሸፈን፣ሄልሜቶችን በእራስ ላይ በማድረግ ከአደጋ መከላከል እንደሚቻል፣ የሚፈነዱ ነገሮችን እና ድንጋይን እንዴትመጠቀም እንደሚቻል ስልጠና ወስዷል፡፡“ (አጽንኦ ተጨምሯል፡፡)

በአጥናፍ ላይ የቀረቡት የጽሁፍ ማስረጃዎች የሚከተሉትን ያካትታል፡ “የእምነት ቃል እንዲሰጥ የተደረገበት – 16 ገጾች”፣ እና ሌሎች ሰነዶች ማለትም “ነጻነት በኢትዮጵያ – 34 ገጾች“፣ “ስለኢንተርኔት ደህንነት የስልጠና ሰነድ“፣ “በእጅ ጽሁፍ የተዘጋጀ የሚስጥር የአመጽ ቅደምተከተል ሰነድ – 61 ገጾች“፣ “በፍላሽ ላይ ያለ ስለደህንነት ቅደምተከተል የተዘጋጀ ሰነድ“፣ “በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ስለነጻነት ሊታዩ የሚችሉ አጫጭር ፊልሞችን ለማዘጋጀት የቀረበ ንድፈ ሀሳብ – 7 ገጾች“፣ “ለሚመጣው ምርጫ ዓላማ ሊውል የሚችል የኢንተርኔት አድራሻ ስያሜ ለመግዛት ዕቅድ መያዝ – 8 ገጾች“፣ “እ.ኤ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ስለሚካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ የማህበራዊ ድረ ገጽ ሚና- 9 ገጾች“፣ “የጽሁፍ ምርመራን እንዴት ማስቀረት እንደሚቻል በሲቪል መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች አስተባባሪነት የተዘጋጀ የስልጠና ሰነድ“፣ “በኢንተርኔት የመጠቀሚያ የሚስጥር ኮዶችን እና ፓስወርዶችን የመለወጥ ዘዴ – 129 ገጾች“፣ “የዲጂታል የደህንነት ስልጠና ለመውሰድ ለእርሱ የተላለፈ የግብዣ ደብዳቤ“፣ “የጉዞ ዕቅድ እና ቲኬት – 18 ገጾች“ የውንጀላ ክሶች ቀርበውበታል፡፡

5) ዘላለም ክብረት ቤዛ፡ “የሀገር ውስጥ የሚስጥር የሽብር ድርጅት ማቋቋም“ እና ሆን ብሎ እያወቀ በሚስጥር ከሚንቀሳቀሰው የግንቦት 7 አሸባሪ ቡድን ጋር በሚስጥር የግነኙነት መረብ ዘርግቷል“፣ “ህዝቡን ለማነሳሳት አመጽ እንዲጀመር ለማድረግ እንዲቻል በሀገር ውስጥ እና ከኢትዮጵያ ውጭ በርካታ ስልጠናዎች እንዲዘጋጁ አድርጓል፣ ተሳትፏል፣ እንዲሳለጡም አድርጓል፡፡“

በዘላለም ላይ የቀረቡት የጽሁፍ ሰነድ ማስረጃዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፡ “የእምነት ቃል እንዲሰጥ የተደረገበት – 16 ገጾች“፣ እና ሌሎች የተሰበሰቡ ሰነዶች ማለትም “ከውጭ ሀርድ ዲስክ ጭቆና እና የሰብአዊ ልማት ጽሁፍ“ የሚል ያለበት፣ “ዋኤል ጎኒም ኢትዮጵያዊ ቢሆን ኖሮ የሚል (ከግብጽ ምዕናባዊ የኢንተርኔት አክቲቪስት ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ-18 ገጾች – በበፈቃዱ ኃይሉ የተጻፈ“፣ “የጽሁፍ ምርመራ ዋጋ“፣ “ድምጻችን ከሚዘረፍ እንዲሰማ ማድረግ“፣ “በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ስለነጻነት ሊታዩ የሚችሉ አጫጭር ፊልሞችን ለማዘጋጀት የቀረበ ንድፈ ሀሳብ“፣ “የመለስ ዜናዊ ራዕይ እና ትሩፋት – 4 ገጾች“፣ “የሞተው ፓርላማ – 22 ገጾች“ የሚሉ ውንጀላዎች ቀርበውበታል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ባልታሰባ እና ባልተጠበቀ ሁኔታ ክሱ እንዲቋረጥ ተደርጎ .. ሀምሌ 9/2015 ከማጎሪያውእስር እንዲለቀቅ ተደርጓል፡፡

6) አቤል ዋቤላ ሱጌቦ፡ የተመሰረተበት ክስ “የሀገር ውስጥ የሚስጥር የሽብር ድርጅት ማቋቋም“፣ “ከግንቦት 7 ጋር በመተባበር ህዝቡን ለአመጽ ለማነሳሳት፣ አመጽ እንዲጀመር ለማድረግ እንዲቻል በሀገር ውስጥ እና ከኢትዮጵያ ውጭ በርካታ ስልጠናዎች እንዲዘጋጁ አድርጓል፣ ተሳትፏል፣ እንዲሳለጡም አድርጓል፡፡“

በአቤል ላይ የቀረቡት የጽሁፍ ሰነድ ማስረጃዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፡ “የእምነት ቃል የተሰጠበት – 12 ገጾች“፣ እና ሌሎች ሰነዶች ማለትም “ለሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ዲጂታል የደህንነት ሰነድ – 18 ገጾች“፣ “በእርሱ ቤት ውስጥ የተመደቡ የቡድን አባላት ሚናዎች እና ኃላፊነቶች – 26 ገጾች“፣ “ለሚመጣው ምርጫ ዓላማ ሊውል የሚችል የኢንተርኔት አድራሻ ስያሜ ለመግዛት ዕቅድ መያዝ – 8 ገጾች“ የሚሉ ውንጀላዎች ቀርበውበት ነበር፡፡

7)  አስማማው ኃይለጊዮርጊስ ግዛው፡ የተመሰረተበት የክስ ውንጃላ “የሀገር ውስጥ የሚስጥር የሽብር ድርጅት ማቋቋም“፣ “አስቦበት እና ሆን ብሎ እያወቀ ግንቦት 7 እየተባለ ከሚጠራው “አሸባሪ” ድርጅት ጋር ግንኙነት ፈጥሯል፡፡“ የሚል ነው፡፡

በአስማማው ላይ የቀረቡት የጽሁፍ ማስረጃዎች የሚከተሉትን ያካትታል፡ “የእምነት ቃል የሰጠበት – 13 ገጾች“፣ እና ሌሎች የተሰበሰቡ ሰነዶች ማለትም “ከምግብ በፊት ፍትሕ እና ሰላም”፣ “ሙስሊሞች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ተሳትፎ ማድረግ መጀመር አለባቸው – 6 ገጾች“፣ “የሁሉም ንቅናቄ ተከሳሾች የምርመራ ውጤት በኢትዮጵያ የመረጃ ደህንነት ተመዝግቦ እንደተያዘ- 31 ገጾች“፣ “በኢትዮጵያ የፌዴራል የመረጃ ደህንነት አገልግሎት የተጻፈ ደብዳቤ   56 ገጾች“፣ “የዲጂታል ደህንነት ለጋዜጠኖች“፣ “በኢትዮጵያ መንግስት ሀሳብን በነጻ የመግለጽ መብትን የሚነጥቅባቸው መንገዶች“፣ “በዳሽን ባንክ የተጻፈ ደብዳቤ – 31 ገጾች“፣ “የተከሳሹ የፓስፖርት ፎቶኮፒ ቅጅዎች ለተከሳሹ ውንጀላ ማጠናከሪያ እንዲመጡ ተደርጓል፡፡“ የሚሉት ናቸው፡፡        

ይህ በእንዲህ እንዳለ ባልታሰባ እና ባልተጠበቀ ሁኔታ ክሱ እንዲቋረጥ ተደርጎ .. ሀምሌ 9/2015 ከማጎሪያውእስር እንዲለቀቅ ተደርጓል፡፡

8) ኤዶም ከሳዬ ገላን፡ የተመሰረተባት የክስ ውንጀላ “ሆን ተብሎ ታስቦበት እና እያወቀች የግንቦት 7 አሸባሪ ቡድንን ስትራቴጂዎች ባካተተ መልኩ ለተፈጻሚነታቸው ተሳትፎ አድርጋለች“፣ “ከግንቦት 7 ጋር በመተባበር ህዝቡን ለአመጽ ለማነሳሳት እና አመጽ እንዲጀመር ለማድረግ እንዲቻል በሀገር ውስጥ እና ከኢትዮጵያ ውጭ በርካታ ስልጠናዎች እንዲዘጋጁ አድርጋለች፣ ተሳትፋለች፣ እንዲሳለጡም አድርጋለች“ የሚሉ ናቸው፡፡

በኤዶም ላይ የጽሁፍ ሰነድ ማስረጃ ምንም ዓይነት ዝርዝር አልቀረበም! 

ይህ በእንዲህ እንዳለ ባልታሰበ እና ባልተጠበቀ ሁኔታ ክሱ እንዲቋረጥ ተደርጎ .. ሀምሌ 9/2015 ከማጎሪያውእስር እንድትለቀቅ ተደርጓል፡፡ 

9) ተስፋለም ወልደዬስ:  የተመሰረተበት የክስ ውንጀላ “ሆን ተብሎ ታስቦበት እና እያወቀ የግንቦት 7 አሸባሪ ቡድንን ስትራቴጂዎች ባካተተ መልኩ ለተፈጻሚነታቸው ተሳትፎ አድርጓል“፣ “ከግንቦት 7 ጋር በመተባበር ህዝቡን ለአመጽ ለማነሳሳት እና አመጽ እንዲጀመር ለማድረግ እንዲቻል በሀገር ውስጥ እና ከኢትዮጵያ ውጭ በርካታ ስልጠናዎች እንዲዘጋጁ አድርጓል፣ ተሳትፏል፣ እንዲሳለጡም አድርጓል“ የሚል ነው፡፡

በተስፋለም ላይ የጽሁፍ ሰነድ ማስረጃ ምንም ዓይነት ዝርዝር አልቀረበም! 

ይህ በእንዲህ እንዳለ ባልታሰበ እና ባልተጠበቀ ሁኔታ ክሱ እንዲቋረጥ ተደርጎ .. ሀምሌ 9/2015 ከማጎሪያውእስር እንዲለቀቅ ተደርጓል፡፡ 

የአሸባሪነት ቁሳዊ ማስረጃዎች፣ 

የውንጀላ ክስ የተመሰረተባቸው የቁስ አካል ማስረጃዎች የሚከተሉትን ያካትታል፡ 2 ቶሽባ  ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች፣ 3 ሳምሰንግ ተንቀሳቃሽ ስልኮች ከ2 ሲምካርዶች ጋር፣ 1 አሰስ ላፕቶፕ ኮምፒውተር፣ 1 ቴክኖሞባይል ተንቀሳቃሽ ስልክ ከ2 ሲምካርዶች ጋር፣ 1 ሳምሰንግ ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ 2 የመቅጃ ፍላሾች፣ 1 ተች ሰክሪን ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ 2 በሳጥን ውስጥ ያሌ የደህንነት መጽሐፎች፣ 3 ኖኪያ ተንቀሳቀሽ ስልኮች፣ 1 ዴል ላፕቶፕ ኮምፒውተር፣ 1 አፕል ላፕቶፕ ኮምፒውተር፣ 1 ሁአዌ ተንቀሳቃሽ ስልክ ከ3 ሲም ካርዶች ጋር፣ 12 የቪዲዮ ማጫዎቻ ሲዲዎች ናቸው፡፡

በኃይል በማስገደድ የተገኘ የእምነት ቃል እና በሕገወጥ መልክ ኃይልን በመጠቀም የሕግ የምክር አገልግሎትእንዳያገኙ በማድረግ የተገኘ የአሸባሪነት ማስረጃ ሆኖ ሊቀርብ ይችላልን? 

የሚከተሉትን ሁሉንም ወይም ደግሞ አንደኛቸውን ነገሮች እንደበቂ ማስረጃዎች በመያዝ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስርበማዋል የሽብር ድርጊት ፈጽመዋል ወይም ደግሞ የሽብር ድርጊት ሙከራ አድርገዋል በማለት በችሎት በማቅረብየሕግ ሂደት ስርዓት ማከናወን ይቻላልን?:

“ለለውጥ ፈላጊዎች እና ለጀግኖች የተጻፈ ጽሁፍ” በሚል ርዕስ የተጻፈ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ህወሀት ለትግራይ ህዝብ እንዴት ያለ ህጋዊ ድርጅት ሊሆን እንደሚችል የሚጠይቅ ጽሁፍ” በሚል ርዕስ ተዘጋጀ ሰነድ ይዞ መገኘት፣

“80 ሚሊዮን እስከምንሆን ድረስ እንዋጋለን” በሚል ርዕስ የተጻፈ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“እኛ ህብረት ከፈጠርን አምባገነኖች ምንድን ሊሆኑ ይችላሉ?“ በሚል ርዕስ የተጻፈ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“በድረገ ገጽ በሚወጣ ጽሁፍ ላይ የሚደረግ የጽሁፍ ምርመራ ዘመቻ ይቁም” በሚል ርዕስ የተጻፈ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ዋኤል ጎኒም ኢትዮጵያዊ ቢሆን ኖሮ (ከግብጽ ምዕናባዊ የኢንተርኔት አክቲቪስት ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ – 18 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ለሲቪል ነጻነት ተሟጋቾች የስልጠና ሰነድ” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ይዞ መገኘት፣

“መንግስት አለን? ወይም ደግሞ መንግስት የማን ነው? ምንስ ዓይነት ነው? – 10 ገጾች” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የኢህአዴግ አባል ያልሆነ ዳኛ ሊኖር ይችላልን?“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የቴሌኮም የሸፍጥ ሕግ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነትን ለመሸበብ የወጣ መሳሪያ – 12 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የተሰበሰበ የሕዝብ አስተያየት እና በደረ ገጽ ላይ የሚደረግ ዘመቻ ዕቅድ“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ለዘጋቢ ፊልም ዝግጅት በኢትዮጵያ ሀሳብን በነጻ በመግለጽ ሁኔታ ላይ ያተኮሩ በእጅ የተጻፉ ቃለመጠይቆች ዝርዝር“ በሚል ርዕስ በእጅ የተጻፈ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ዳቦ እና ነጻነት፣ ለጽሁፍ ምርመራ ይቁም ዘመቻ“ በሚል ርዕስ የተጻፈ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የጽሁፍ ምርመራ ዋጋ – 8 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተጻፈ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“አሁን በህይወት የሌለውን መለስ ዜናዊን የሚተች የግንቦት 7 ደብዳቤ – 4 ገጾች“ የተጻፈ ትችት ይዞ መገኘት፣

“ከቢዝነስ እና ኮንስትራክሽን ባንክ ገንዘብ የተቀበለበት ደረሰኝ“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ደረሰኝ ይዞ መገኘት፣

“በኢንተርኔት የደህንነት ጉዳይን በማስመልከት ከሶሊያና ሽመልስ ፓስፖርት ጋር በተያያዘ የተደረገ የኢንተርኔት መልዕክት ልውውጥ – 26 ገጾች” በሚል ርዕስ የተጻፈ የመልዕክት ልውውጥ ይዞ መገኘት፣

“ስለኢትዮጵያ በናትናኤል ፈለቀ በእጅ ጽሁፍ የተዘጋጀ ግጥም እና ከቤቱ የተሰበሰበ – 1 ገጽ“ በሚል ርዕስ የተጻፈ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የኃይል አመጽ ለመቀስቀስ መንቀሳቀስ እና የምጣኔ ሀብት ዕድገቱን ዕውቅና ያለመስጠት የሚሉ ጹሁፎችን ያካተተ – 2 ገጾች” በሚል ርዕስ የተጻፈ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ከሲዲ የታተመ የኦነግ የፖለቲካ ፕሮግራም – 22 ገጾች“ በሚል ርዕስ የቀረበ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ነጻነት በኢትዮጵያ – 34 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተጻፈ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ስለኢንተርኔት ደህንነት የስልጠና ሰነድ“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ይዞ መገኘት፣

“በእጅ ጽሁፍ የተዘጋጅ የሚስጥር የአመጽ ቅደምተከተል ሰነድ – 61 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“በመቅጃ ፍላሽ ላይ ያለ ስለደህንነት ቅደምተከተል የተዘጋጀ ሰነድ“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ስለነጻነት ሊታዩ የሚችሉ አጫጭር ፊልሞችን ለማዘጋጀት የቀረበ ንድፈ ሀሳብ – 7 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ለሚመጣው ምርጫ ዓላማ ሊውል የሚችል የኢንተርኔት አድራሻ ስያሜ ለመግዛት ዕቅድ መያዝ – 8 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጅ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“እ.ኤ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ስለሚካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ የማህበራዊ ድረ ገጽ ሚና- 9 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የጽሁፍ ምርመራን እንዴት ማስቀረት እንደሚቻል በሲቪል መብት ተሟጋች ድርጅቶች አስተባባሪነት የተዘጋጀ የስልጠና ሰነድ“፣

“በኢንተርኔት የመጠቀሚያ የሚስጥር ኮዶችን እና ቁልፎችን የመለወጥ ዘዴ – 129 ገጾች“፣ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የዲጂታል የደህንነት ስልጠና ለመውሰድ ለእርሱ የተላለፈ የግብዣ ደብዳቤ“ “የጉዞ ዕቅድ እና ቲኬት – 18 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የጉዞ ዕቅድ እና ቲኬት – 18 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ይዞ መገኘት፣

“ከውጭ ሀርድ ዲስክ ጭቆና እና የሰብአዊ ልማት ጽሁፍ“፣ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ዋኤል ጎኒም ኢትዮጵያዊ ቢሆን ኖሮ የሚል (ከግብጽ ምዕናባዊ የኢንተርኔት አክቲቪስት ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ-18 ገጾች – በበፈቃዱ ኃይሉ የተጻፈ“ ሰነድ ይዞ መገኘት፣

“የጽሁፍ ምርመራ ዋጋ“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ድምጻችን ከሚዘረፍ እንዲሰማ ማድረግ“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ስለነጻነት ሊታዩ የሚችሉ አጫጭር ፊልሞችን ለማዘጋጀት የቀረበ ንድፈ ሀሳብ“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የመለስ ዜናዊ ራዕይ እና ትሩፋት – 4 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የሞተው ፓርላማ – 22 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ለሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ዲጂታል የደህንነት ሰነድ – 18 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ይዞ መገኘት፣

“በእርሱ ቤት ውስጥ የተመደቡ የቡድን አባላት ሚናዎች እና ኃላፊነቶች – 26 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ለሚመጣው ምርጫ ዓላማ ሊውል የሚችል የኢንተርኔት አድራሻ ስያሜ ለመግዛት ዕቅድ መያዝ – 8 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ከምግብ በፊት ፍትሕ እና ሰላም” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“ሙስሊሞች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ተሳትፎ ማድረግ መጀመር አለባቸው – 6 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የሁሉም ንቅናቄ ተከሳሾች የምርመራ ውጤት በኢትዮጵያ የመረጃ ደህንነት ተመዝግቦ እንደተያዘ – 31 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“በኢትዮጵያ የፌዴራል የመረጃ ደህንነት አገልግሎት የተጻፈ ደብዳቤ 56 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የዲጂታል ደህንነት ለጋዜጠኖች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የሁሉም ንቅናቄ ተከሳሾች የምርመራ ውጤት በኢትዮጵያ የመረጃ ደህንነት ተመዝግቦ እንደተያዘ – 31 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“በኢትዮጵያ የፌዴራል የመረጃ ደህንነት አገልግሎት የተጻፈ ደብዳቤ – 56 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“የዲጂታል ደህንነት ለጋዜጠኖች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“በኢትዮጵያ መንግስት ሀሳብን በነጻ መግለጽ መብትን የሚነጥቅባቸው መንገዶች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ ይዞ መገኘት፣

“በዳሽን ባንክ የተጻፈ ደብዳቤ – 31 ገጾች“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ደብዳቤ ይዞ መገኘት፣

“የተከሳሹ የፓስፖርት ፎቶኮፒ ቅጅዎች ለተከሳሹ ውንጀላ ማጠናከሪያ እንዲመጡ ተደርጓል” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ይዞ መገኘት የሚሉ ናቸው፡፡

የሚከተሉት ቁሶች በአሸባሪነት የሕዝብ ዕልቂትን ሊያስከትሉ የሚችሉ ተመራጭ መሳሪዎች ናቸውን? 

2 ቶሽባ ላፕቶፖች፣ 3 ሳምሰንግ ተንቀሳቃሽ ስልኮች ከ2 ሳም ካርዶች ጋር፣ 1 አሰስ ላፕቶፕ ኮምፒውተር፣ 1 ቴክኖሞባይል ተንቀሳቃሽ ስልክ ከ2 ሲም ካርዶች ጋር፣ 1 ሳምሰንግ ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ 2 የመቅጃ ፍላሾች፣ 1 ተች ስክሪን ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ 2 በሳጥን ውስጥ ያሉ የደህንነት መጽሐፎች፣ 3 ኖኪያ ተንቀሳቃሽ ስልኮች፣ 1 ዴል ላፕቶፕ ኮምፒውተር፣ 1 አፕል ላፕቶፕ ኮምፒውተር፣ 1 ሁአዌ ተንቀሳቃሽ ስልክ ከ3 ሲምካርዶች ጋር፣ 12 የቪዲዮ ማጫዎቻ ሲዲዎች የሚሉ ናቸው፡፡

ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ከAK 47 ጋር እኩል ናቸውን?

ተንቀሳቃሽ ስልኮች ከእጀ ቦምቦች ጋር እኩል ናቸውን?

የመቅጃ ፍላሽ ድራይቮች ከፍላሽ ቦምቦች ጋር እኩል ናቸውን?

በሳጥን ውስጥ ያሉ የደህንነት መጽሐፍት የተሻሻሉ የፍንዳታ መሳሪዎች ናቸውን?

የቪዲዮ ማጫዎች ሲዲዎች ከአርፒጂዎች/RPGs (ፈንጂ መተኮሻ ) እኩል ናቸውን?

ሲም ካርዶች ከጥይቶች ጋር እኩል ናቸውን?

በአጠቃላይ ከዞን 9 ጦማሪያን ጉዳይ ጋር በተያያዘ መልኩ እነዚህ ጦማሪያን የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ግንቦት 7 የተባለውን ድርጅት አሸባሪ ብሎ የሰየመው የነጻነት ንቅናቄ ድርጅት አባላት ናቸው በማለት በምዕናቡ ፈጥሮ የሚያራምደው እና የሚያናፍሰው እኩይ ምግባር ነው፡፡

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ እነዚህ ለመብቶቻቸው በጽናት በመቆም ሰላማዊ ትግል የሚያካሂዱ እና ለሀገራቸው ለውጥ በሰላማዊ መንገድ ይመጣል በማለት እምነታቸውን የሚያራምዱ ትንታግ ወጣት ጦማሪያን ለግንቦት 7 ይቅር እና ለሌላ ለየትኛውም ድርጅት አባል ስለመሆናቸው ቅንጣት ታህል ማስረጃ የለውም፡፡ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ እራሱ በፈጠረው ባዶ ምዕናቡ በመመራት በእነዚህ ጦማሪያን ላይ የደቦክስ በመመስረት ጥፋተኛ እንዲባሉለት ይፈልጋል፡፡

የዞን 9 ጦማሪያን ምንም ዓይነት የሰሩት ወንጀል የለም፡፡ በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ወንጀል ተብሎ የተያዘባቸው ሀሳባቸውን የመግለጽ መብታቸውን በመጠቀማቸው ብቻ ነው!

ይልቁንም የዞን 9 ጦማሪያን እራሳቸው የወንጀል እና የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የሽብር ሰለባዎች ናቸው፡፡

እንዲያው ለመሆኑ እትብታቸው በተቀበረችበት በእራሳቸው ሀገር ዘመኑ ያፈራቸውን የግንኙነት ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ሀሳብን በነጻ የመግለጽ መብት የተከበረባት ሀገር አድርጊያታለሁ እያለ ሌት ከቀን እንደበቀቀን ከሚለፈልፍባት ሀገር ሆነው ሀሳባቸውን የመግለጽ መብታቸውን በመጠቀም ሰላማዊ እና የምሁራዊ አንደበት ክህሎታቸውን በማከል ግንኙነት ማድረጋቸው በየትኛው መለኪያ እና መስፈርት እንዲሁም የሕግ አንቀጽ ነው ሽብረተኞች ተብለው ከሕግ አግባብ ውጭ በእስር ቤት እየማቀቁ እንዲኖሩ የሚደረገው?

ምን ዓይነት የፍትሕ አካል ቢኖርስ ነው ለእንደዚህ ያለው የሸፍጥ መንግስታዊ ውንብድና እኩይ ምግባር ተባባሪ ሆኖ በዜጎቹ ላይ እንደዚህ ያለ ግፍ እየሰራ የአምባገነኖች ተባባሪ ሊሆን የሚችለው?

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ፕላኔት የዝንጀሮዎች ፕላኔት አፈታሪክ ቢሆን ኖሮ የዞን 9 ጦማሪያን እጅግ በጣም ጥሩ የሆነ የማምለጫ ዕድል ይኖራቸው ነበር፡፡

የመከላክል ጥረቱ በምንም ዓይነት መንገድ ለወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ቡድን አያጎበድድም፡፡

ሆኖም ግን ጉዳዬን በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ፕላኔት ላይ ላለው የዝንጀሮ/ጦጣ ችሎት ትቻለሁ!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

ነሐሴ 20 ቀን 2007 .

በመተካካት ተሸኝተው የነበሩት የሕወሓት ነባር አመራሮች ተመለሱ

በመተካካት ተሸኝተው የነበሩት የሕወሓት ነባር አመራሮች ተመለሱ

– ሦስቱ አባል ድርጅቶችም ጉባዔያቸውን አካሂደዋል

ከነሐሴ 16 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ በመቐለ ሰማዕታት አዳራሽ እየተደረገ ባለው 12ኛው የሕወሓት ጉባዔ፣ በመተካካት ተሸኝተው የነበሩ የሕወሓት አመራሮች በጉባዔው እንዲመረጡና እንዲመርጡ ተወሰነ፡፡ አዘጋጅ ኮሚቴው የጋበዛቸው ያለ ድምፅ እንዲሳተፉ ነበር፡፡

ከ1,650 በላይ ጉባዔተኞች በታደሙበት ጉባዔ የተገኙ አንድ ተሳታፊ ከዚህ ቀደም ተገፍተው የወጡ ያሏቸው ነበር አመራሮች በድምፅ እንዲሳተፉ ጥያቄ ካቀረቡ በኋላ፣ በጉዳዩ ላይ የመከረው ጉባዔ በጭብጨባ በሙሉ ድምፅ ጥያቄውን ተቀብሎታል፡፡ በዚህም መሠረት ዶ/ር አርከበ እቁባይ፣ አቶ ስብሃት ነጋ (አቦይ)፣አምባሳደር ሥዩም መስፍን፣ አምባሳደር ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ፣ አቶ ፀጋዬ በርኼን ጨምሮ 17 ነባር አባላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

ጉባዔው በእስካሁኑ ቆይታው በአንደኛው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ፣ በመልካም አስተዳደርና በመተካካት ላይ ተወያይቷል፡፡ በመልካም አስተዳደር እጦት ክልሉ እየተጠቃ እንደሆነ በርካታ አስተያየቶች ተሰጥተዋል፡፡ በተለይ በአንድ የሃይማኖት አባት የቀረበው የመልካም አስተዳደር እጦት ትኩረት የሳበ ነበር፡፡ የሕወሓት አመራሮች ድርጅቱ ቀድሞ አንግተውት የነበረውን ዓላማ እንደረሱ በአጽንኦት ገልጸው፣ ፍትሕ በገንዘብ እየተገዛ የክልሉ ሕዝብ የማያውቀው አዲስ ባህል በመጎልበቱ ይህንንም እንደሚዋጉት አመልክተዋል፡፡ ‹‹እሳት ያልፈራ ሕዝብ እናንተን የሚፈራ ይመስላችኋል?›› ሲሉም ጥያቄአቸውን አቅርበዋል፡፡ መተካካትን በተመለከተም ወደ መገፋፋት በመቀየሩ ያለ ዕድሜና አቅም ማነስ ዶ/ር አርከበና አምባሳደር ብርሃነ እንዲወጡ መደረጉን ተችተዋል፡፡ እንደ ድሮው መገማገምና አንዱ አንዱን ተጠያቂ ማድረግ በመሸፋፈንና በመጠባበቅ መቀየሩም ተገልጿል፡፡

የሕወሓት ሊቀመንበርና የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ዓባይ ወልዱ የቀረበውን ቅሬታ ተቀብለው፣ የተሠራ ነገር ቢኖርም ትልቅ ዳገት እንደሚጠብቅ ገልጸዋል፡፡ የአመራር አባላት ራሳቸውን ማጥራትና ወደ ራሳቸው መመልከት እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል፡፡

ዶ/ር አርከበ በጉባዔው ንቁ ተሳትፎ ያደረጉ ሲሆን፣ ሕዝቡ ቅሬታ እያቀረበ ያለው በፍትሕ አካላትና በፓርቲው አባላት መሆኑ አሳሳቢ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ጉባዔው ዛሬ የሚጠናቀቅ ሲሆን፣ የሥራ አስፈጻሚና የማዕከላዊ ኮሚቴ እንዲሁም የቁጥጥር ኮሚሽን አባላትን ይመርጣል፡፡

11ኛው የብአዴን ድርጅታዊ ጉባዔ በባህር ዳር በድርጅቱ ሪፖርት ላይ ተወያይቷል፡፡ ጉባዔው በክልሉ የተመዘገበውን የኢኮኖሚና ዕድገትና የግብር ምርት ውጤታማነት የገመገመ ሲሆን፣ ኢኮኖሚያዊ ዕድገቱ 10.4 በመቶ በመድረሱ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ መቻሉ ተገልጿል፡፡ የመጀመርያው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ መልካም አስተዳደር፣ ትምህርት፣ ጤናና ሌሎች መስኮችም በግምገማው ተካተዋል፡፡

መልካም አስተዳደርን በተመለከተና በሥራ ፈጠራ ጉድለቶች መኖራቸውን የገመገመው ጉባዔው፣ የክልል ከፍተኛ አመራሮችም ለችግሩ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙ አውስቷል፡፡ የድርጅቱ ጉባዔ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት፣ የብአዴንና የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን፣ የድርጅቱን ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበር በመምረጥ ማክሰኞ ምሽት ተጠናቋል፡፡ ማክሰኞ ምሽት የተመረጡት እነማን እንደሆኑ ግን አልታወቀም ነበር፡፡

ኢሕዴድ በአዳማ ከተማ 8ኛ ጉባዔው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል፡፡ በጉባዔው በክልሉ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን ለማምጣት የሚችሉ አዳዲስ ሐሳቦች እንደ ግብዓት ሲሰባሰቡ እንደነበር ተገልጿል፡፡ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን በክልሉ የ11.2 በመቶ ዕድገት ለማስመዝገብና የኢኮኖሚውን መዋቅራዊ ሽግግር ለማፋጠን የሚያስችሉ ውሳኔዎች ይተላለፋሉ ተብሏል፡፡

የኦሕዴድን ድርጅታዊ ህልውና ይፈታተናሉ የተባሉት ትምክህትና ጠባብነት፣ ኪራይ ሰብሳቢነት፣ የተንዛዙ አሠራሮችና ፍትሐዊነት የጎደላቸው አመራሮች በጉባዔው ወቅት መነሳታቸው ታውቋል፡፡ ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የኦሕዴድ ጉባዔ ማክሰኞ ምሽት ማተሚያ ቤት እስከገባንበት ጊዜ ድረስ ይጠናቀቃል ተብሎ እየተጠበቀ ነበር፡፡

የደኢሕዴን ጉባዔ በሐዋሳ ማክሰኞ ነሐሴ 19 ቀን 2007 ዓ.ም. ተጠናቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሊቀመንበር ሆነው እንዲቀጥሉ ሲመረጡ፣ የትምህርት ሚኒስትሩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ለምክትል ሊቀመንበርነት ተመርጠዋል፡፡ ጉባው በሦስተኛ ቀን ውሎው የመጀመርያውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ገምግሞ፣ በምግብ እህል ራስን መቻል ላይ አበረታች ውጤት መገኘቱን ተወያይቶበታል፡፡

አበረታች የተባሉ ስኬቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ፣ ይቀራቸዋል የተባሉት ላይ ደግሞ በተጠናከረ ሁኔታ ርብርብ እንዲረደረግ ውሳኔ ተላልፏል፡፡ የጤናና የትምህርት ዘርፍ ተደራሽነታቸው መልካም መሆኑ ተወስቶ፣ የጥራት ጉዳይ ግን እንዲታሰብበት ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም ጠባብነት፣ ብልሹ አሠራርና ሙስና በድርጅቱ ውስጥ ቦታ እንደማይኖራቸው ውሳኔ ላይ መደረሱ በውይይቱ ወቅት ተነስቷል፡፡ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት፣ የደኢሕዴንና የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ አባላትም ተመርጠዋል፡፡ የተሟላ ዝርዝር ግን ማግኘት አልተቻለም፡፡

በተያያዘ ዜና የብአዴን ነባር ታጋይና ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ አዲሱ ለገሠ በክብር መሰናበታቸው የተገለጸ ሲሆን፣ አቶ ዮሴፍ ረታም እንዲሁ ተሰናብተዋል፡፡ የደኢሕአዴን ሊቀመንበር፣ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል በመሆን ያገለገሉት ዶ/ር ካሱ ኢላላ እንዲሁ ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት በክብር መሰናበታቸው ተገልጿል፡

ርዕዮት አለሙ አራዳ ነች (ከተማ ዋቅጅራ)

(ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ)

አባቴ ሁሌ የሚነግረኝ ነገር ነበር አራዳ ማለት ይለኛል  አራዳ ማለት፡-  ለነብሱ ያደረ፣ እውነተኛ፣ ፈሪ ያልሆነ፣  አላማውን በእውነት የሚገልጽ፣ ታዛዥ፣ ህብረተሰቡን በቅን የሚያገለግል፣ የሚያውቀውን በቅንነት የሚያሳውቅ፣ የፍቅር ሰባኪ፣ የሰላም መዝሙረኛ፣ የጥበብ ቅኝት ተቀኚ፣ የፍልስፍና አባት፣ የተበላሹ መንገዶችን ጠራጊ፣ ማስተዋልና ጥበብን በልቡ አስቀማጭ፣ በእውነት የዘነጠ፣  ለውሸት ቦታ የሌለው፣ ስጋን አደላዳይ፣ ነፍሱን አዳኝ፣ ከፍ ባለ ማማ ተቀምጦ ከአትሮኑሱ ስር የሚገኝ፣ የእውቀት ጫፍ ላይ ደረሶ ከፊደል ቆጣሪወች ጋር ፊደል የሚቆጥር፣ ከራሱ ከፍታ የህዝቡ ከፍታን የሚወድ፣ ከራሱ ድምቀት የአገርን መድመቅን የሚናፍቅ፣ ለታናሹ ታዛዥ፣ ለታላቁ አገልጋይ፣ አባቶቹን አክባሪ፣ እናቶቹን አፍቃሪ፣ ሲጠሩት አቤት ሲልኩት ወዴት የሚል፣ ቢዘምር ላገሩ፣ ቅኔ ቢቀኝ ለህዝቡ፣ ለነብሱም ለስጋውም ያደረ ማለት ነው። ይለኝ ነበር

ሁሉም ሰው እኩል ተሰጥኦ አይሰጠውም ለአንዱ ድምጽ፣ ለሌላው ደራሲነት፣ ለአንዱ መካሪ፣ ለሌላው አስተማሪ፣ ለአንዱ ቀዳሽ፣ ሌሌላው አራሽ፣ ብቻ ሁሉም የራሱ ተሰጥኦ አለው ዋናው ነገር ተሰጥኦህን በአግባቡ እና በእውነተኛ መንገድ መጠቀሙ ነው። እናም ርዕዮት ንጽ አእምሮ፣ ቆራጥ ልቦና፣ እውነት የሚናገር ብዕር፣ ተሰጥቷታል። ለዚህም ምስክር የምትጽፋቸው ጽሁፍ ይናገራል። እስር ሳይበግራት ጥንካሬዋን ያሳየች ከስር ከወጣችም በኃላ የብዕሯ ቀለም ሳይነጥብባት ስራዋን የቀጠለች ንጹህ  ህሊና ያላት ያወቀችውን የምታሳውቅ የአገር አለኝታ የህዝብ መከታ የሆነች በኢትዮጵያዊያኑ ልቦና  ውስጥ የሴት ጀግና ሆና የተቀመጠች አራዳ ነች።

እንዲህም ሆኗል ሁለት ጓደኛሞች ቡና እና ጊዮርጊስ ሲጫወቱ አንድ የጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ደጋፊ ሌላኛው  ደግሞ የቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊ ናቸው። ዘንድሮማ የደጋፊ ነገር ችግር የለብንም ንብ ደግፉ፣ ቢራቢሮን ደግፉ፣ ዝንብን ደግፉ፣ ጢንዝዛን ደግፉ፣ በግድም በእጅም ግንቦት20 ደግፉ፣ የሚባልበት ጊዜ ላይ ስለደረስን ድጋፌን በደንብ ትረዱታላቹሁ ብዬ እገምታለው። እናም የቡናው ደጋፊ ቡና ያሸንፋል  የጊዮርጊስ ደጋፊ ጊዮርጊስ ያሸንፋል በማለት በ 1000 ብር ያሲዛሉ።  ለማንኛው እንድንተማመን  ውል ተጻጽፈን እንፈራረም ይላሉ። በውሉ መሰረት እንደሚተገበር ይስማማሉ። እንዲህ ይል ነበር ውሉ፡-

እከሌ የተባለው እና እከሌ  የተባለው ዛሬ በዚህ ቀን ቡና እና ጊዮርጊስ በሚያደርጉት የእግር ኳስ ጨዋታ ቡና ካሸነፈም፣ ቡና ከተሸነፈ፣  እንዲሁም አቻ ከወጣ የቡና ደጋፊ የሆነው  2000 ብር የእከሌ መሆኑን በፊርማችን  እናረጋግጣለን ብሎው ተፈራርመው ወደ እስታዲዮሙ ይገባሉ። በጨዋታውም ጊዮርጊስ ያሸንፍና በል ብሬን ብሬን እኛ እንደዚህ ነን ይለዋል የጊዮርጊስ ደጋፊ። የጎርጊሱ ደጋፊ መጻፍና ማንበብ አይችልም ነበር።   ውሉን ምን እንደሚል ስላልተረዳው  ክርክር ተጀመረ። በኋላ ላይ ክርክሩ ሲያይል ወደ ጋደኞቻቸው ወሰዱት ዳኝነትን ጠየቁ ጋደኞቻቸው ውሉን ሲያዩት በጣም ሳቁ። ቡና ቢያሸንፍም ቢሸነፍም አቻ ቢወጣም እሱ ይውሰደው ብለህ ነው እኮ ነው የፈረምከው አሉት። የዚህን ጊዜ በጣም ተናደደ። ብር ከመቁጠርህ በፊት ፊደል ቁጠር አሉት። እስከአሁንም እንዲህ እየተባለ ይቀለድበታል።

የብዕር አርበኛዋ ርዕዮት አለሙ በአንድ ብእር 17 አመት ጫካ ነበርን፣ ጀግና ነበርን፣ የሚሉትን ያርበደበደ ታንክ አለን፣ አዳፍኔ አለን፣ የሚሉትን ያዳፈነች። እውነት በመጻፏ ሽብር የመሰላቸው፣ ብዕሯን ከወረቀትጋር በማዋሃዷ ጀግና ነን ብለው የተኮፈሱትን ያራደች፣ የድንጋይ መሰረት ሳይሆኑ የእንቧይ ካብ መሆናቸውን ያሳየች፣ ብዕርተኛ ነች። የእርዮት ብእር ሰለ ሕዝብ ነጻነት የሚናገር፣ ሰለ አገሯ ክብር ቀለምን የሚተፋ፣ አስተማሪ ብእር ነው።  መለስ ዜናዊ |<<ከሺ ጦር ባተሌ አንድ ብዕር የያዘ ሰው ለኛ ከባድ ነው>> ብለው እንደተናገሩት በአንዲት ብዕር ማንም አይደፈረንም ብለው  የውሸት ፕሮፖጋንዳ ሲናገር የነበረውን የወያኔን ምሽግ ሚግ አብራሪ  ወይም ታንከኛ ሆና ሳይሆን ያራደችው፣ ብዕሯ አሁን ስልጣን ላይ ያለውን ገዥ ፓርቲ ምን እንደሚል ያልገባቸው አልያም እውነት ውስጣቸው ስለሌ  በብዕሯ ቀለም የተሸበሩት። እርሷ ግን  እውነትን በመግለጽ፣ አገርን በመውደድ፣ ህዝብን በማክበር ብዕራን ያነሳች አራዳ ነች። እናም ብር ከመቁጠር  ፊደል መቁጠር ይሻላል የሚለውን አባባል ጋብዥያቸዋለው። በእውቀት የበለጸገ እና በእውነተኛ መንገድ ላይ የቆመ  ብዕር ያስተምረዋል እንጂ አያስፈራውምና ነው በብዕር የሚሸበር ያልተማረ ወይም  በእውነተኛ መንገድ ያልቆመ ብቻ ነው።

እርዮት ስጋዋ የታሰረ ህሊናዋ ያልታሰረ ብዕርተና ነች። ገራፊን ገርፈሃል፣ አሳሪን አስረሃል፣ ገዳይን ገድለሃል፣ የምትል የእውነት ብዕር ያነሳች  በዕረኛ ነች። ስጋችን ሲያገኝ የሚወፍር፣ ሲያጣ ደግሞ የሚከሳ ነው። አእምሮአችን ግን እውነትን ስንሰጠው ብቻ ነጻ አድርጎ የሚያኖረን የራሳችን ፍርድ ቤት ነው። ለአእምሮዋ እውነትን ያስገባች፣ እውነትንም ያወጣች፣ ከዘላለም ጸጸት የጸዳች፣ ከራሳ ጋር የተስማማች ብዕርተኛ ነች። ሕዝብ ማለት እሷ፣  እሷ ማለት ሕዝብ፣ መሆኑን ያስመሰከረች የዘመኑ የሴት ተምሳሌት የሆነች አራዳ ነች።

እንጂ  አራዳ የሚለው ትርጉም እንደኛ ዘመን ትርጉም እንደተሰጠው  የቃመና ያስቃመ፣ ያጨሰና ያስጨሰ፣  የጠጣና ያስጠጣ፣ ከፍ ብሎ የዘለለ እና የወደቀ፣  የሰረቀና ያሰረቀ፣ ያመሸና ያስመሸ፣ የጨፈረ እና ያስጨፈረ፣ እስታ በል፣ ላሽ በል፣ ተቄ በል፣ ጩባ፣ ፍሉስ፣ ሼባው፣ ጌጃው፣ ማኛው ,… የሚለው የሚጠቀም እና የሚያደርግ አራዳ አይደለም። እንደዚ አይነቱ ከራስ መጣላት፣ ከቤተሰብ መጣላት፣ ከጎረቤት መጣላት፣ ከህብረተሰብ መጣላት፣ ከአገር መጣላት፣ ብሎም ከእግዛቤሔር ጋርም መጣላት ነው። ስጋውንም ነብሱንም የሚጎዳ አራዳ የሚለው ትርጉምን አይስማማውም።

ሁላችንም አራዳ ለመሆን የአባቶቻችንን ምክር እንስማ እላለው። አራዳ በኢትዮጵያ ምድር በዝቶ ይብቀልባት፣ ይውጣባት፣ ይታይባት፣ ያብብባት።  አራዳ ዶክተር ወላ እንጅነር፣ አራዳ ወታደር ወላ መምህር፣ አራዳ አርሶ አደር ወላ ኢንቨስተር፣ አራዳ ደራሲ ወላ ሃያሲ፣, አራዳ ሳይንቲስት ወላ ጂኦሎጂስት፣ አራዳ ፖለቲከኛ ወላ ዳኛ፣ አራዳ መሪ ..ሆኖ ታታሪ.. በህግ አዳሪ.. ህዝቡን አስከባሪ.. ያብዛልን ፈጣሪ።

ከተማ ዋቅጅራ

21.08.2015

Email- waqjirak@yahoo.com

– See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/46150#sthash.jgZmzLSt.9vf1YEuE.dpuf

ከብሄር ፖለቲካ እንውጣ! የተባበረችውን ኢትዮጵያን እንገንባ! (ገለታው ዘለቀ)

ethnic politics

በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚንስትር ኣቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ሲናገሩ ኣገራችንን የሚበትኑ ኣጥፊ ዘሮች ያሏቸውን ሶስት ጉዳዮች ኣነሱ። ኣንደኛው ጠባብነት፣ ሁለተኛው ትምክህተኛነት፣ ሶስተኛው በሃይማኖት ሽፋን የሚራመድ ኣክራሪነት ናቸው ኣሉ። በመሰረቱ እነዚህን ጉዳዮች ኣቶ ሃይለማርያም ለመጀመሪያ ጊዜ ያነሷቸው ጉዳዮች ኣይደሉም። በ”ኢህዓዴግ” ውስጥ ብዙ ጊዜ የሚነሱ ሁሌም ሲባሉ የነበሩ ናቸው። ኣቶ ሃይለማርያም ኣዲስ ነገር ኣልተናገሩም ።

ለማናቸውም ግን እነዚህ ኣደገኛ ዘሮች ከየት መጡ? ኣገሪቱንስ ወዴት እየወሰዱ ነው? በርግጥ ከብሄር ፖለቲካው ኣዝማሪዎች ኣልፎ ወደ ታች ወርዶ የኔብጤው ተራው ህዝብ ኣካባቢ እነዚህ ዘሮች ጎልተው እየታዩ ነው ወይ? የሚለው ጉዳይና ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ያለመቻሏ ጉዳይ፣ የሰብዓዊ መብት ኣያያዝ ጉዳይ ሃላፊነት ለሚሰማው ኢትዮጵያዊ፣ ለዓለማቀፍ ተቋማትና ለኢትዮጵያ ወዳጅ ሃገራት ዲፕሎማቶች በጣም ኣሳሳቢ ጉዳይ ሆኖባቸው ኣያለሁ።

ወደ ጠቅላይ ሚንስትሩ ንግግሩ እንመለስና በመጀመሪያ እሳቸው ራሳቸው ያመኗቸው እነዚህ ሶስት ጉዳዮች በሰፊው የሚታዮት በኣንድ ሃገር ውስጥ ፖለቲካው በጠባቡ ሲቀረጽ፣  ወይም በየቤትህ እደር ኣይነት የፖለቲካ ጨዋታ ሲጀመር ወይም የፖለቲካው ጥብቆ ሲጠብ ነው። ሳይንሳዊ በሆነ ኣገላለጽ የማንነት ፖለቲካ (Identity Politics) የሚባለው ሲሆን በተለይ ብዙህ በሆነ ማህበረሰብ ውስጥ ይህ የፖለቲካ ስርዓት ሲዘረጋ የሚያመጣቸው ወይም ከዚያ የሚፈለፈሉ ችግሮች ብዙ ናቸው። የብሄር ፖለቲካ የማህበራዊ ካፒታል ምስጥ ነው። ለዚህም ነው ምሁሩ፣ ተማሪው፣ የተማረው፣  ያልተማረው ሁሉ ላለፉት ሃያ ዓመታት በላይ የብሄር ፖለቲካን ሲነቅፍ የነበረው:: የማንነት ፖለቲካ እነዚህን ኣደገኛ ነገሮች እንደሚያመጣ ብዙ ሳይንሳዊ ምርምር የሚጠይቅም ኣልነበረም። የብሄር ፖለቲካ ስነ- ልቦናው ራሱ ጠባብነት ነው። ከጎሳው ያላለፈ የፖለቲካ ስብእና ይዞ እንዲያድግ የሚያደርግ የፖለቲካ ኣስተሳሰብ የተጫነው በመሆኑ የጠባብነት መነሻው ይሄው የብሄር ፖለቲካ ነው።

ትምክህተኝነት የሚባለውም ከዚሁ ከጠባብ ኣስተሳሰብ የሚመነጭ የኣንድ ዛፍ ቅርንጫፍ ነው። ሰው ጠባብ ሲሆን ነው የሚመካው። በወንዙ በጎሳው ሲመካ ጠባብ ሆኖ ነውና። ጠባቦች ሁል ጊዜም ትምክህተኝነት ኣያጣቸውም። ሁለቱም ባህርያት የተያያዙ ከኣንድ መራራ የብሄር ፖለቲካ ምንጭ የሚቀዱ ናቸው።  ጠቅላይ ሚንስትሩ ሲናገሩ ተማሪው ላይ ተጽእኖው ይታያል እንጂ እነዚህን ዘሮች የሚዘራው  ኣስተማሪው ነው ኣሉ። ማን ነው የጠባብነትን ፖለቲካ የሚያስተምረው? ህወሃት “ኢህኣዴግ” ኣይደለምን? ህወሃት “ኢህዓዴግ” ከመምጣቱ በፊት ትግሬው፣ዓማራው፣ኦሮሞው ወዘተ. ኣብሮ ቁጭ ብሎ ሲጫወት መች የብሄር ነገር ትዝ  ብሎት ያውቅ ነበር? ቢታወሰውም እየተቀላለደ ከመኖር ውጭ መራራ ስር ኣልነበረውም። ለእነዚህ ኣደገኛ ዘሮች መፈጠርና ማደግ ጥሩ መፈልፈያ የሆነው ራሱ የፖለቲካው ቤት መሆኑን መረዳት ብዙ ምርምር ኣልጠየቀም።

ቡድኖች ለምንድነው የብሄር ወይም የሃይማኖት ማንነታቸውን ይዘው ወደ ፖለቲካ የሚሳቡት? ካልን  የፖለቲካን ሃይል መሳሪያ በማድረግ የቡድንን የወል ጥቅምና የበላይነት ለማረጋገጥ ነው። የፖለቲካው ስልጣን የመሳሪያ ሃይል ያለውንና የኢኮኖሚውን ክፍል ስለሚያዝ ያንን ቡድኖች መቆጣጠር ከቻሉ ለቡድናቸው ኣቋራጭ እድገት ዓይነተኛ መሳሪያ ሆኖ ስለሚያዩት ነው። በዚህ የፖለቲካ ድባብ ውስጥ ኣክራሪነት፣ ልዮነትን ማድመቅ የመከሰታቸው እውነት ለምን ጥያቄ ውስጥ ይከተናል? ሃይማኖታዊ ኣክራሪነትም የሚከሰተው ኣጠቃላይ የፖለቲካው ቅርጽ በማንነት ላይ ሲረብብ ሃይማኖታዊ ማንነታቸውን ይዘው ወደ ስልጣን እንዲሳቡ የሚያደርግ ስነ ልቡናዊ ድባብ ሲፈጠር ነው። በመሰረቱ ሃይማኖትን ማጥበቅ ማለት ኣይደለም ኣክራሪነት ማለት። ሃይማኖታዊ ኣክራሪነት የሚፈጠረው በሃይማኖቱ መሰረት ላይ የቆመ ፖለቲካ ለመመስረት መጣርና በጋራ ህልውና (coexistence) ኣለማመን ነው። በግለሰብ ደረጃም ሆነ በቡድን እንዲህ ዓይነት ባህርያት ሲገለጹ ኣክራሪነት መጣ እንላለን። ይህ ኣክራሪነት በኢትዮጵያ ከታየ ኣካባቢያዊ ኣስተዋጾዎች እንዳሉ ሆነው ራሱ የፖለቲካው ተፈጥሮና የመንግስት ኣያያዝ ከፍተኛ ኣስተዋጾ ማድረጋቸው ኣይካድም።  በኣጠቃላይ ምንጩ የማንነት ፖለቲካ ሆኖ ሳለ ለምን የመንግስት ሰዎች እነዚህን ችግሮች እየጠቀሱ  ኣጥፊዎች ናቸው እንደሚሉ ዶክተር ዳኛቸው በቅርቡ በ VOA እንዳስረዱት ለማንም ኣይገባም። “ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል” ነው ያሉት?

ጠቅላይ ሚንስትሩ ራሳቸው  እኮ ቢያንስ እንደ ብሄር ራሳቸውን የሚገልጹበት ታእታይ የፖለቲካ ስብእና ባይኖራቸውም በመልክዓምድር በተወሰነ የፖለቲካ ታእታይ ስብእና የታጠሩና ለፈጠራቸው ህወሃት ኣድርባይ ናቸው።  የህወሃት ኣባላትም እንዲሁ የፖለቲካ ውስጣዊ ወይም ታእታይ ሰውነታቸው በብሄር ላይ የቆመ ጠባብ ነው። በርግጥ “ኢህዓዴግ” የሚባለውን ለብሰናል ለማለት ከሆነ ህዝቡ ኣይዋጥለትም። ከዚህ በፊት እንደገለጽኩት “ኢህዓዴግ” የሚባል ድርጅትም በዓለም ላይ የለም። ለምን የለም? ከተባለ ከማንነት ፖለቲካ ተፈጥሮ ጋር ያለውን ፍልስፍናዊውን ጉዳይ ልተወውና  ኣንድ ጥቂት ተግባራዊ ነገር በማንሳት ላሳይ።

የዛሬ 40 ኣመት ገደማ ሁሉም እንደሚያውቀው ህወሃት ይቋቋማል።በዚህ ወቅት ህወሃት ሲፈጠር የነበረውን ህልም ተግባራዊ ለማድረግ ውሎ ኣድሮ ያስባል።  ወደዚያ የሚያደርሰው ኣድራሽ፣ ኣድራሽ ብቻ ሳይሆን እስከ ፈለገው ጊዜ እንዲቆይ፣ ጊዜ እንዲያገኝ የሚያደርገው፣ የሚያግዘው የፕሮጀክት ግብዓት ፈለገ። ጥሩ ኣድራሽና ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚሆነው የተለያዩ ብሄሮችን ስም የያዙ የፖለቲካ ድርጅቶችን መፈልፈል ሆኖ ኣገኘው:: በመሆኑም እንደ ኦህዴድ፣ ብዓዴን የመሳሰሉትን ሁሉ ፈለፈለ። እነዚህ ድርጅቶች የህዝብ ብሶት የወለዳቸው፣ ህዝብ የጠየቃቸው ኣይደሉም። ህወሃት ራሱ ለፕሮጀክቱ ግብዓት ይሆኑለት ዘንድ በኣምሳሉ የቀረጻቸው ናቸው። በሌላ ኣገላለጽ እነዚህ ድርጅቶች ራሳቸው ህወሃት ናቸው። ምንምን እንኳን የተለያየ ብሄር ኣባላትን ይዘው ቢመሰረቱም ተገትረው ብናይም በህወሃት ብሶት፣ በህወሃት ራእይ፣ በህወሃት እጅ የተፈጠሩ በህወሃት የህወሃት ናቸው። ኣንዳንዶቹ ድርጅቶች በተለይም ኦህዴድ እንደሚወራው ኣንዳንድ መሪዎቹ የህወሃት ኣባላት ስማቸውን እየቀየሩ ኣመራር ላይ የነበሩበት ሁኔታም ነበር።

ኣቶ በረከት ስምዖን በህወሃት 40 ዓመት ላይ ንግግር ሲያደርጉ እንዲህ ኣሉ

እኛ ብአዴኖችም ሁሌም ቢሆን ራሳችንን ከህወሓት ነጥለን ያየንበት ጊዜ የለም። ሁላችንምወየንቲ ኢና” (ወያኔዎች ነን) ነው የምንለው።

                                             (በረከት ስምዖን)

የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ዶክተር ቴድሮስ ኣድሃኖም ደግሞ ይህንን ያስረግጡልናል።

አንዳንድ ወገኖች …. ስድብ መስሏቸውወያኔ አሉኝ ከጥቂት አመታት በፊት ለተመሳሳይ ጉዳይ በረከት ስምዖንያለውን አስታወሱኝሁላችንም ወያኔ ነንአዎ አሁንም ሁላችንም ወያኔን ነን…..እኔ ወያኔ ኢህአዴግ ነኝ! Je Suis Woyane!   …. በዚህም ኩራት ይሰማኛል፡፡ እኔ ወያኔ ነኝ! ሁላችንም ወያኔ ነን! ይህን ችግርየሚፈታውም በወያኔነት ነው! እንበርታ፡፡”              

       (ዶክተር ቴድሮስ ኣድሃኖም)

በኣንጻሩ ከህወሃት ኣባላት መንደር ሁላችንም ኦህዴድ ነን ወይም ደህዴግ ወይም ብዓዴን ለማለት ጨርሶ ታስቦ የማያውቅ ጉዳይ ነው። ምክንያቱም እነዚህ ድርጅቶች እንደ ፖለቲካ ድርጅት በህወሃት ህሊና የሉምና። እንዴውም ኣቶ መለስ  እንኳን ከዚህ ቡድን ተወለድኩ ብለው ጠባብና ትምክህተኛነታቸውን በኣደባባይ ሲናገሩ ተደምጠው ነበር። ይሄ ነው ጠባብነት፣ ትምክህትና ኣክራሪነት የሚባለው።

በኣጠቃላይ የሆነ ኣጀንዳ ይዞ የተነሳው ህወሃት ሲሆን በየመንገዱ ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚሆኑትን የፖለቲካ ድርጅቶችን የፈለፈለ ሲሆን እነዚህን ግብዓቶች ይዞ ሁዋላ ላይ “ኢህዓዴግ” የሚል ስያሜ ይዞ ብቅ ይላል። “ኢህዓዴግ”  የራሱ የህወሃት ፕሮጀክት ማስፈጽሚያ ሲሆን እንደ ፖለቲካ ድርጅት ግን ኣለ ማለት ኣይቻልም። ለዚህም ነው  ራሱ በኣድራሽነት የተሰራውና የሚኖረውም። ግንባር በተፈጥሮው ኣድራሽ ሲሆን ይህ በግንባርነት የተዋቀረ ቤት የዚሁ የህወሃት ሌላው የኣዲስ ኣበባ  ቤት ነው።  በርግጥ ወደ  ተራው ኣባል ኣካባቢ ስናይ የዋህነት ሊኖር ይችላል። ተሰብስበው ግምገማ ሲባል፣ እቅድ ኣውጡ ኣውርዱ ሲባል “ኢህዓዴግ” በህይወት ያለ ይመስላቸው ይሆናል። የለም። ተላላ መሆን ኣያስፈልግም። ህወሃት እነዚህን ድርጅቶች ሲያቆም ኣዲስ ኣበባን ለመቆጣጠር ብቻ ሳይሆን ከዚያ በሁዋላ ደህንነቱንና ወታደሩን እንዲሁም ኢኮኖሚውን እስኪቆጣጠር ግብዓት ስለሚሆኑት ነው። በርግጥም በኣሁኑ ሰዓት በነዚህ ድርጅቶች እገዛ ህወሃት እነዚህን ህልሞቹን ኣሳክቷል። ኣቅጣጫ ነው ያጣው። በመሆኑም የነዚህ ድርጅቶች ኣባላት መታለሉን ማቆም ኣለባቸው። መንቃትና ለለውጥ መነሳት ያስፈልጋል። በቂምና በበቀል ላይ ሳይሆን  ሁሉን ነጻ የሚያወጣ የወደፊቱን በማሰብ ላይ የተመሰረተ ቢሆን ነው የሚሻለው።

በኣጠቃላይ የሚንስትሮቻችን የመሪዎቻችን ታእታይ የፖለቲካ መሰረት የወንዝ ፖለቲካ በመሆኑ ከዚህ የብሄር ፖለቲካ ዘር የሚወለደው ያው ጠባብነትና ኣክራሪነት ከመሆን ኣያልፍም።ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዶክተር ቴድሮስ ኣድሃኖም ከፍ ሲል እንዳየነው እኔ “Je Suis ወያኔ ነኝ” ብለዋል። ይሄ እውነተኛ የፖለቲካ መሰረታቸው ሊሆን ይችላል። የሚገርመው ግን እኚህ ሰው ኣንድ ጊዜ ኒዮርክ  በተደረገ ስብሰባ ላይ “ ኒውዮርክ ሜልቲንግ ፖት ናት” ብለው በስሜት ተናገሩ። መልቲንግ ፖት የህወሃት ኣስተሳሰብ ጸር ነው። ባህላዊ ውህደት ማለት ነው ሜልቲንግ ፓት ማለት። እኚህ ሰው ምን ኣልባት ተለውጠው ከሆነ ይህን ያሉት እንዳንል የኒውዮርኩን ንግግር ካደረጉ በሁዋላ ነው እኔ  “ Je Suis ወያኔ ነኝ” የሚሉን። እሳቸው ይህን ይበሉ  ፣ እኔ ደግሞ Je Suis ኢትዮጵያዊ! እናንተስ?

እንግዲህ ጠቅላይ ሚንስትር ኣቶ ሃይለማርያም ይህን ዘር ኣጥፊ ነው ብለው ካመኑ በዚህ የወንዜ ፖለቲካ ቤት ውስጥ መዋል ማደር የለባቸውም። ሌሎች ምስጢሩ ያልገባቸው የዋህ የህወሃት፣ የብኣዴን፣የደህዴግ ወዘተ ኣባላት ከዚህ የፖለቲካ ኣስተሳሰብ ወጥተው ጠባብነትን የህወሃትን የበላይነት መዋጋት ኣለባቸው። የጠባብነትና የትምክህት ዋና የሆነውን የብሄር ፓለቲካ ቤት ግድግዳውንና ጣራውን ለመንደል የውስጥ ኣርበኞች መሆን ኣለባቸው። ለለውጥ መነሳት ኣለባቸው።የተባበረችውን ኢትዮጵያን ለመገንባት ትውልዱ ሁሉ ኣምርሮ መነሳት ኣለበት።የተባበረችውን  ኢትዮጵያን የምንገነባው ደግሞ ከብሄር ፖለቲካ ስንወጣ፣ ስምምነት ውስጥ ስንገባ ነው። ይህ ስምምነት የህዝብ ውክልና በሌላቸው በዚህ ኣርባ ኣመት ባፈራናቸው እዚህም እዚያም በተኮለኮሉ ፓርቲዎች መካከል ኣይደለም። ወደ ባህላዊ ቡድኖች ታች ድረስ ወርዶ ህዝቡ ተወያይቶ ቁሳዊና መንፈሳዊ ባህሉን ኣዋጥቶ ኣገሩን እንዲገነባ የሚያደረግ ሰፊ ስምምነት ነው።ለዚህ ደግሞ ኣገሪቱ የሆነ የጽሞናና የሽግግር ጊዜ የሚያስፈልጋት ሲሆን በዚህ ከፍተኛ ኣሳብ ላይ ሁሉም መጠቅለል ይኖርበታል። ይህ ካልሆነ ህወሃት የዘራው ዘር ከፍተኛ ኣደጋ ውስጥ ሊጥለን ይችላል።

ኣዲሲቱ የተባበረችው ኢትዮጵያ  ከብሄር ፖለቲካ ወጥታ በተሻለ ውቅር ልትሰራ ይገባል። የማንነት ኪሳራ እንዳይመጣብን በኣንድ በኩል የተደራጀ የባህል መንግስት መስርተን ባህላችንን እየተንከባከብንና እየተደሰትን በሌላ በኩል ፖለቲካዊ ቤት መስራት እንችላለን። እንደ ኢትዮጵያ ብዙ መልካም ታሪክና ባህላዊ እሴቶች ያሉዋትን ኣገር ለማስተዳደር የዚህ ዓይነት ሲስተም መዘርጋቱ ሰላምን፣ ልማትና ዴሞክራሲን ያፋጥንልናል። ከዚህም በላይ ለዜጎች ርካታን ይሰጣል።

ከልጅነት ጊዜየ ጀምሮ በእድሜ የበሰሉ ሰዎች የሚሰጡት ትምህርት ይማርከኝ ነበር። ኣረጋውያን ሲያወሩ ጠጋ ብሎ ማዳመጥ ርካታን ይሰጠኛል ። ከእለታት ኣንድ ቀን እንዲሁ ኣንድ የእድሜ ባለጸጋ ኣገኘሁና በተፈታ ስሜት ወግ ጀመርን:: እኚህ ሰው ከሚናገሩት የሚበዛው ያለፈው ዘመን ምን ያህል የተሻለ እንደነበር ነው። ምን ኣልባት በኢኮኖሚ ጥንት የተሻሉ ነበሩ ማለት ነው፣ ኣሁን ኑሯቸው ኣሽቆልቁሏል ማለት ነው፣ ብየ እንዳላስብ ኣይደለም። ልጆቻቸው  የተሻለ ገቢ ኣላቸው። እሳቸውም ድሃ የሚባሉ እንዳይደሉ ኣውቃለሁ። ምንድነው ወደ ኋላ የሚጎትታቸው? ምን ኣጥተው ነው? የሚል ጥያቄ ይዞኝ ነበር። በሳቸው የልጅነት ጊዜ በእግር ነበር ይጓዙ የነበሩት፣ ኣሁን በመኪና ይሄዳሉ፣ የተሻለ ልብስ ፣ የተሻለ ጫማ፣ የተሻለ ምግብ፣ የተሻለ ነገር…. እንዳላቸው መረዳት ችያለሁ። እኚህ ሰውም ይህንን ሁሉ ይደሰቱበታል። ይሁን እንጂ ያጡት ነገር ደግሞ ወደ ሁዋላ ሲጎትታቸው ኣየሁና ሁዋላ ላይ ለራሴ የተረዳሁት ነገር እኚህ ሰው ያጡት ባህል ነው ማለት ነው ብየ ደመደምኩ። በለውጥ ስም የሚወዱዋቸውን  ባህሎቻቸውን ኣጥተዋል። ኣንቱ የተባሉ ሽማግሌዎችን ከሰፈራቸው ኣያዩም፣ ክብረ በዓላትን ሲያዩ ይገረማሉ፣ የጠፉ ባህላዊ ተቋማት ይናፍቋቸዋል፣ ወዘተ.

እኚህ ሰው ዘመናዊውን ዴሞክራቲክ የሆነ መንግስት ማየት ይፈልጋሉ። በርግጥ ደግሞ ባህላዊ ተቋሞቻቸው ቢያንስ ከነ ሙሉ ሃይላቸውም ባይሆን በቅርስነት በህይወት ማየት እንደሚፈልጉ ተማርኩ። እኚህ ሰው ኢትዮጵያን ቢወዱም ኣገራቸው የድሮ ሞገሷን የተገፈፈች ኣድርገው እንደሚያስቡ ገመትኩ። ርግጥ ነው ቁሳዊም ሆነ መንፈሳዊ ባህልን ማጣት እንደ ሃገርም እንደ ዜጋም ይከነክናል ይጎዳልም።ሌሎች የኢኮኖሚ ህይወታቸው እያደር እየደቀቀ የመጣ ሰዎችም እንዲሁ የድሮውን ጊዜ ሲናፍቁ ብዙ ጊዜ እሰማለሁ። ጥያቄያቸው ኢኮኖሚያዊ ብቻ ሳይሆን ባህላቸውንም እንደናፈቁ መረዳት ይቻላል። ለዚህ ነው ኣዲሲቱ ኢትዮጵያ የተደባለቀውን ፖለቲካዊ ማንነትና ባህላዊ ማንነት በመለየትና በተለያየ ቤት እንዲያድሩ በማድረግ የተሻለ ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋታል የሚያስብለን ። የተባበረችውን ኢትዮጵያን የምንመሰርተውም እንዲህ በጠነከረ ማህበራዊና ፖለቲካዊ መሰረት ላይ መሆን ኣለበት። ለዴሞክራሲ፣ ለለውጥ የምናደርገው ትግል ሁሉ  Je Suis  ኢትዮጵያ መርሃችን ኣድርገን የተባበረችውን ኢትዮጵያን እንገንባ። ኢትዮጵያውያን የተባበረችውን ኢትዮጵያን ገንብተን ትኩረታችንን ሁሉ በምግብ ዋስትና ላይ ልናደርግ ይገባናል። ተመልከቱ እስቲ። ኢትዮጵያ ባለፉት ኣስር ኣመታት ያለማቋረጥ በጥንድ ቁጥር እያደገች ነው ተባለ። ጠቅላይ ሚንስትሩ በቅርብ ጊዜ ኢትዮጵያ በምግብ  በብሄራዊ ደረጃ ራሷን ቻለች ኣሉ። እነሆ በማግስቱ ዛሬ በጥቂት ወራት ውስጥ ለ4.5  ሚሊዮን ህዝብ ኣስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋል ተባለ። የተባበሩት ህዝቦች ድርጅት የሰባዊ መብት ኣጋር  ድርጅትና መንግስት ይህን ገልጸዋል። በእኔ እምነት ይህም ይፋ የሆነው በተባበሩት  ህዝቦች ድርጅት ቅስቀሳ እንጂ መንግስት ይህ ነገር ወደ ኣደባባይ ሳይወጣ የሆነው ቢሆን የሚመርጥ ነው የሚመስለኝ። የሚገርመው ዛሬ በብሄራዊ ደረጃ ራሳችንን በምግብ ቻልን ያሉን ጠቅላይ ሚንስትር ለተራቡ ሰዎች ቀለብ ለመግዛት ከሚያስፈልገው ተጨማሪ $ 230 ሚሊዮን ውስጥ $33 ሚሊዮን  የሚሆነውን ብቻ ነው መንግስት መሸፈን የሚችለው። ቀሪውን 200  ሚሊዮን ገደማ  ዶላር ባስቸኳይ የዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ርዳታ እንዲያደርግ ልመና ጀምረናል። ይህ ማለት ደግሞ በምግብ በብሄራዊ ደረጃ ራሳችንን ኣልቻልንም ነበር ማለት ነው። ለብዙ ዓመታት በጥንድ ቁጥር ኣድጊያለሁ ዓለም ያጨብጭብልኝ ስትል የነበረች ኣገር ዛሬ ለጥቂት ወራት እንኳን ዜጎቿን መታደግ ኣልቻለችም።  ዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብስ ምነው ዛሬ ጠዋት በምግብ ራሳችንን ቻልን ብልችሁ የለም እንዴ? ቢለን ……ያሳፍራል። ኢትዮጵያውያን ፖለቲከኞች በውነት ኣጃንዳቸው ሁሉ ይህ ነው ሊሆን የሚገባው። ይህቺን ኣገር በምግብ ራስዋን የማስቻል ስራ ነው መቅደም ያለበት። ሰው በሚራብበት ኣገር የብሄር ፖለቲካ ቅብጥርሴ ሃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው።  ለውጥና ሪፎርሜሽን ይመግበናል፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ችግሮቻችንን ይፈታልና ለለውጥ ታጥቀን እንነሳ።

እግዚኣብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!

geletawzeleke@gmail.com

– See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/9861#sthash.pFGHLqbv.dpuf

Ethiopian Bloggers in Kangaroo (Monkey) Kourt

by Alemayehu G. Mariam

Kangaroo/monkey kourt (in)justice T-TPLF style

Last week, young Ethiopian bloggers collectively known as “Zone 9 Bloggers” (named after a cell block  holding political prisoners at  the infamous  Meles Zenawi Kality Prison, a few kilometers outside of the capital) returned to  the kangaroo/monkey  kourt system of the Thugtatorship of the Tigrean People’s Liberation Front (T-TPLF) for  the 33rd time  since April 2014.

TPLF kangaroo (monkey) court system.

(Ethiopia is the ONLY country in the world where the police arrest and detain a criminal suspect and then go out looking for evidence of wrongdoing for months and even years!)

“Justice delayed is justice denied.”  Justice delayed 33 times is justice denied 33 times.

Justice delayed 33 times while the young bloggers are held in prolonged pretrial detention, denied bail, effective assistance of counsel, speedy trials and an impartial fact finder is a travesty of justice.

In anticipation of Barack Obama’s visit in July, the T-TPLF released two bloggers and 3 journalists.

Since 2006, I have been writing about the T-TPLF kangaroo (monkey) kourt system.

I wrote my first commentary in December 2006 entitled, “Keystone Cops, Prosecutors and Judges in a Police State.” That commentary examined the “trials” of the “Kality defendants” (opposition leaders) jailed by the late Meles Zenawi following the 2005 election.

In December 2007, I wrote “Monkey Trial in Kangaroo Kourt” examining the “trial” of Daniel Bekele (manager of ActionAid International in Ethiopia at the time), presently Executive Director of the Africa Division of Human Rights Watch, and Netsanet Demessie who founded and directed the Organization for Social Justice in Ethiopia. I compared their “trial” to the grim and chilling fictional story of Joseph K., in Franz Kafka’s “The Trial“.

I have written numerous commentaries on the T-TPLF’s Banana Republicand its monkey kourts for years.

In June 2014, I wrote a commentary entitled, “Who is afraid of the Ethiopian bloggers?, on the legal plight of the Zone 9 bloggers.

I use the metaphor of “kangaroo” and “monkey” kourt to describe the T-TPLF’s (in)justice system, not out of malice, but out of necessity for descriptive precision.

The phrase “kangaroo court” has nothing to do with the marsupial kangaroos of Australia.

The phrase is said to have originated in the American West in the 19thcentury to describe bogus, sham and phony judicial proceedings run by self-proclaimed judges.

The phrase has often been defined as 1) “a mock court in which the principles of law and justice are disregarded or perverted”, 2) “a court which blatantly and intentionally disregards recognized standards of law or justice”, 3) a “court held by a legitimate judicial authority who intentionally disregards the court’s legal or ethical obligations”,  and 4) a court projecting the “appearance of a fair and just trial, even though the verdict has in reality already been decided before the trial has begun.”

The T-TPLF judicial system fits all of the foregoing definitions to a T.

The phrase has found its way into one of the most important landmark criminal constitutional cases in the U.S. legal history. In In Re Gault, the U.S. Supreme Court condemned a judicial process “where police take matters in their own hands, seize victims, beat and pound them until they confess. It is the right of the accused to be tried by a legally constituted court, not by a kangaroo court”.

That is the essence of the T-TPLF’s kangaroo courts. T-TPLF police thugs arrest suspects in political crimes on instruction of the T-TPLF political bosses, place them  in detention, beat the hell out of them and extract confessions, delay filing charges, deny them counsel and shuttle them to and fro before judicial hacks appointed by the T-TPLF, deny them speedy trials and force them to languish in vermin-ridden jails for months or years as hack judges grant endless continuances to “prosecutors” to gather (fabricate) evidence on the suspects.

Kangaroo courts on Planet T-TPLF become monkey kourts.

I use the apt phrase monkey kourt (with a “k”) system (yezinjero chilot) interchangeably with kangaroo court to describe the T-TPLF (in)justice system as a metaphorical equivalent for my Ethiopian readers. I also aim to underscore the dominance hierarchy of the T-TPLF monkey kourt legal system, accentuated by extreme agonistic behavior of T-TPLF leaders and members against their perceived opponents.

The “trial” of the Zone 9 bloggers is such a travesty of justice that all of the major international human rights organizations have condemned it.

Of course, being politically correct, none of them would dare call it kangaroo or monkey kourt system.

But a kangaroo/monkey court by any other name is still kangaroo/monkey kourt. In other words, a pig with lipstick and makeup is still a pig at the end of the day.

Human Rights Watch (HRW) has described the T-TPLF kangaroo/monkey kourt system as a “political witch-hunt.” HRW protested to the T-TPLF: “Journalism is not a crime.”

The Committee to Protect Journalists condemned the prosecutions (persecutions) for “conflating terrorism with journalism.”

Freedom House said the case against the bloggers is based on “spurious charges” and urged donors to  “press the government to stop pursuing politically motivated charges against pro-democracy activists as the country prepares for elections in May.”

In January 2015, the U.S. State Department expressed its “concern” over the T-TPLF’s “decision to proceed with the trial of six bloggers and three independent journalists on charges under the Anti-Terrorism Proclamation.”

The Department declared, “The decision undermines a free and open media environment—critical elements for credible and democratic elections, which Ethiopia will hold in May 2015.”

In June 2015, the T-TPLF declared it had won the May election by 100 percent of the vote.

In July Barack Obama showed up in Ethiopia and chimed in, “The government of Ethiopia, that has been democratically elected.” (Was Obama trippin’ when he said that?)

The crime of blogging on Planet T-TPLF

The blogger defendants in the T-TPLF kangaroo/monkey kourt facing trumped up charges include: Befekadu Hailu Techanie,  Natneal Feleke Abera, Mahlet Fantahun Tefera, Atnaf Brehanie Ayalew, Zelalem Kibret Beza, Abel Wabella Sugebo, Asmamaw Hailegiorgis Gizaw, Edom Kassaye Gelan, Tesfalem Weldeyes Arage and (charged in absentia) Soliyana Shimeles Gebremariam.)

The defendants are alternatively “charged” in two counts under the Ethiopian “Criminal Code” [“Code”] and “Proclamation No. 652/2009” [“Proclamation”]  (“Anti-terrorism law”).

In count one, they are accused of being a “Principal Criminal” or attempted “Principal Criminal” in violation of  Article 32 (1 & 2) of the Code.

In count two, the defendants are charged with violation of Article 27 (1 & 2) (attempt to commit a crime),  38 (1) (criminal conspiracy) and 238 (1) (“Crimes Against the Constitution or the State”).

The charge alleges that all of the defendants have “signed” multipage “confessions statement (sic) which can be used as evidence”:   Befekadu Hailu Techanie (31 pages); Natneal Feleke Abera (27 pages);  Mahlet Fantahun Tefera (12 pages); Atnaf Brehanie Ayalew (16 pages); Zelalem Kibret Beza (16 pages); Abel Wabella Sugebo (12 pages); Asmamaw Hailegiorgis Gizaw (13 pages); Edom Kassaye Gelan (10 pages) and  Tesfalem Weldeyes Arage (13 pages).  (Charged in absentia is Soliyana Shimeles Gebremariam.)

The defendants were denied counsel when they allegedly “confessed”.

Befeqadu Hailu Techanie is accused of “establishing a domestic secret terror enterprise” by “sketching and allocating duties & responsibilities for the members.” To avoid “government” detection Befeqadu “  assisted, organized and took part in a training communication encryption tools called ‘Security in Box’” and “embraced the strategies and sought support of the terrorist organization called Ginbot7.”

The documentary evidence against Befeqadu include:  31 pages of “confessions” and information collected from his laptop and house including: “an article written for change seekers and patriots”, and documents entitled, “how legitimate is TPLF to Tigray”, “We will fight until we become 80 million”, “What would happen to dictators if we are united,” “Stop censorship online campaign,” “Had Wael Ghonim been an Ethiopian (an imaginary interview with Egyptian internet activist)- 18 pages”),   “Training manual for defenders  of civil  liberties,” “Do we have government or whose is government and what kind – 10 pages”, “Is there a judge who is not a member of EPRDF?”, “Telecom fraud law as a tool to stifle freedom of expression – 12 pages,” “Poll collected and online campaign plan – 3 pages” and “A hand written list of interviewees for a documentary film on state of freedom of expression in Ethiopia”.

Natnael Feleke Abera, alleged to be the mastermind of the terror group,  “established a domestic secret terror enterprise” and “coordinated all activities of the terror group.” Natnael in coordination with “Ginbot 7 organized, took part and facilitated various trainings to initiate the public to incite violence.”

The documentary evidence against Natnael include: 27 pages of confessions, “documents collected from his laptop and E-mail (downloaded)”; other documents entitled, “Had Weal Ghonim been an Ethiopian an imaginary interview written by Befekadu Hailu,” “Bread and freedom article written for stop censorship campaign”, “The price of censorship (article – 8 pages); “Ginbot 7 news letter criticizing the late Meles Zenawi – 4 pages;” “Receipt of money transfer from Construction & Business Bank”, “Email message exchange about internet security with Soliyana Shimeles with his passport – 26 pages”, “A poem written by Natnael about Ethiopia collected from his house – hand written 1 page”.

Mahlet Fantahun Tefera allegedly “became an operative in various covert networks” for “Ginbot 7 in order to accomplish the objectives of the terrorist group.”   She “lent a hand in organizing and participating in various trainings of violence and terror.”

The documentary evidence against Mahlet include: 12 pages of “confessions” and other “documents collected from her computer” including “articles found to be denigrating, incite violence (sic) and deny the economic development  – 2 page” and  “Political program of OLF printed from CD – 22 pages.”

CHARGES DROPPED AND RELEASED ON JULY 9, 2015.

 Atnaf Birahane Ayalew is accused of “intentionally and knowingly participated in the covert terror group.” He “participated in the training which focuses on how to provoke government security people and create tribal divisionism amongst them to incite violence and defend oneself using apparatuses such us face covering, helmets, explosives, stones.” (Emphasis added.)

The documentary evidence against Atnaf include: 16 pages of “confessions” and other “documents collected” entitled, “Freedom in Ethiopia – 34 pages,” “Training manual about internet security”, “Hand written security procedures of covering a rally – 61 pages,” “Manual of security procedures located in flash drive,” “Proposal for producing short films about freedom in rural Ethiopia – 7 pages,” “Domain name (korogo.com) intended to be purchased for the upcoming election -8 pages,” “The role of social media in the 2015th  Ethiopia election – 9 pages, “Training manual organized by civil rights defenders on how to circumvent censorship, “Encryption tools and changing passwords  – 129 pages,” “Invitation letters send to him to attend digital security training,” “Travel itinerary and tickets – 18 pages”.

Zelalem Kibret Beza is alleged to be “a founding member of the secret terror enterprise” and intentionally and knowingly created a link with of the terrorist organization called Ginbot 7.” He “organized, took part and facilitated various trainings both inside and outside of Ethiopia to initiate the public to incite violence.”

The documentary evidence against Zelalem include 16 pages of “confessions” and other “documents collected” from his  “external hard disk” including documents entitled, “Repression and human development article,” “Had Weal Ghonim been an Ethiopian an imaginary interview written by Befekadu Hailu,” “The price of censorship,” “From hijacking our vote to let our voice be heard,” “Proposal for producing short films about freedom in rural Ethiopia with his passport,” “Vision and legacy of Meles Zenawi – 4 pages,” “The dead parliament – 22 pages.”

CHARGES DROPPED AND RELEASED ON JULY 9, 2015.

Abel Wabela Sugebo is alleged to have been “a founding member of a domestic secret terror enterprise.” He  “organized, took part and facilitated various trainings both inside and outside the country to initiate the public to incite violence” in coordination with Ginbot 7.

The evidence against Abel include 12 pages of “confessions” and other “documents collected” from him including, “Digital security manual for human rights defenders  – 18 pages,” “Roles and responsibilities of the group located in his house – 26 pages,” “Domain name (korogo.com) intended to be purchased for the upcoming election – 8 pages”.

Asmamaw Hailegiorigis Gizaw  is alleged to have been “a founding member of the secret terror enterprise.” He   “intentionally and knowingly created a link with of the terrorist organization called Ginbot7.”

The documentary evidence against Asmamaw include 13 pages of “confessions” and other “documents collected” from him including, documents entitled “Justice and peace before food,” “Muslims should start participating in Ethiopian politics – 6 pages,” “Surveillance results of movements of all accused as recorded by Ethiopia’s Information Security Service – 31 pages,” “Letter written by Ethiopia’s Federal Information Security Service – 56 pages,” “Digital security for journalists”, “Ways of hijacking freedom of expression by Ethiopia’s government,” “Letter written by Dashen Bank – 31 pages,” “Passport copies of the accused are brought to support the allegation – 6 pages”.

CHARGES DROPPED AND RELEASED ON JULY 9, 2015.

Edom Kassaye Gelan is accused of “intentionally and knowingly participated in the terror group which has embraced the strategies of Ginbot 7.” She “ took part and facilitated various trainings both inside and outside of Ethiopia to initiate the public to incite violence.”

The evidence against Edom: None listed!

CHARGES DROPPED AND RELEASED ON JULY 9, 2015.

Tesfalem Weldeyes “intentionally and knowingly participated in the terror group which has embraced the strategies of Ginbot 7.” He  “took part and facilitated various trainings both inside and outside of Ethiopia to initiate the public to incite violence.”

The evidence against Tesfalem: None listed!

CHARGES DROPPED AND RELEASED ON JULY 9, 2015.

Physical evidence of terrorism

Physical evidence of the alleged terrorist crimes include: 2 Toshiba laptop, 3 Samsung mobile phone with two SIM cards, 1 Asus laptop, 1 Techno mobile with two SIM cards, 1 Samsung mobile phone, 2 Flash drives, 1 Touch screen mobile phone, 2 Security in a box books, 3 Nokia mobile phone, 1 Dell laptop, 1 Apple laptop, 1 HUAWE mobile phone with three SIM card, 12 video CDs.

Is a “confession” obtained by force and duress without the presence of counsel sufficient evidence of terrorism”?

Is possession of any or all of the following sufficient evidence to arrest and prosecute a suspect for committing “terrorism” or a terrorist act:

“an article written for change seekers and patriots”;
“[an article questioning] how legitimate is TPLF to Tigray”,
“[an article entitled] We will fight until we become 80 million”,
“[an article entitled] What would happen to dictators if we are united,”
“[an article entitled] Stop censorship online campaign,”
“[an article entitled] Had Wael Ghonim been an Ethiopian (an imaginary interview with Egyptian internet activist)- 18 pages”),
“A Training manual for defenders  of civil  liberties,”
“[an article entitled] Do we have government or whose is government and what kind – 10 pages”,
“[an article entitled] Is there a judge who is not a member of EPRDF?”,
“[an article entitled] Telecom fraud law as a tool to stifle freedom of expression – 12 pages,”
“a poll collected and online campaign plan – 3 pages”,
“A hand written list of interviewees for a documentary film on state of freedom of expression in Ethiopia”,
 “[an article entitled] Bread and freedom article written for stop censorship campaign”
“The price of censorship (article – 8 pages);
“A Ginbot 7 news letter criticizing the late Meles Zenawi – 4 pages;”
“Receipt of money transfer from Construction & Business Bank”,
“Email message exchange about internet security with Soliyana Shimeles with his passport – 26 pages,
“A poem written by Natnael about Ethiopia collected from his house – hand written 1 page”,
“Articles found to be denigrating, incite violence and deny the economic development  – 2 page”,
“[The] Political program of OLF printed from CD – 22 pages.”
“[an article entitled] Freedom in Ethiopia – 34 pages,”
“[A] Training manual about internet security”,
“[A] hand written security procedures of covering a rally – 61 pages,”
“[A] Manual of security procedures located in flash drive,”
“[A] Proposal for producing short films about freedom in rural Ethiopia – 7 pages,”
“[A] Domain name (korogo.com) intended to be purchased for the upcoming election -8 pages,”
“[an article entitled] The role of social media in the 2015th  Ethiopia election – 9 pages,
“[A] Training manual organized by civil rights defenders on how to circumvent censorship,
“Encryption tools and changing passwords  – 129 pages,”
“Invitation letters send to him to attend digital security training,”
“[A] Travel itinerary and tickets – 18 pages”,
“[an article entitled] Repression and human development,”
“[an article entitled] Had Weal Ghonim been an Ethiopian an imaginary interview written by Befekadu Hailu,”
“[an article entitled] The price of censorship,” “From hijacking our vote to let our voice be heard,”
“[A] Proposal for producing short films about freedom in rural Ethiopia with his passport,”
“[an article entitled] Vision and legacy of Meles Zenawi – 4 pages,”
“[an article entitled] The dead parliament – 22 pages.”
“[an article entitled] Digital security manual for human rights defenders  – 18 pages,”
“[an article entitled] Roles and responsibilities of the group located in his house – 26 pages,”
“[A] Domain name (korogo.com) intended to be purchased for the upcoming election – 8 pages”.
“[an article entitled] Justice and peace before food,”
“[an article entitled] Muslims should start participating in Ethiopian politics – 6 pages,”
“[an article entitled] Surveillance results of movements of all accused as recorded by Ethiopia’s Information Security Service – 31 pages,”
“[an article entitled] Letter written by Ethiopia’s Federal Information Security Service – 56 pages,”
“Digital security for journalists”, “Ways of hijacking freedom of expression by Ethiopia’s government,”
“[A] Letter written by Dashen Bank – 31 pages,”
“Passport copies of the accused are brought to support the allegation – 6 pages”.

Are the following items the preferred weapons of mass destruction in the arsenal of terrorists?

2 Toshiba laptop, 3 Samsung mobile phone with two SIM cards, 1 Asus laptop, 1 Techno mobile with two SIM cards, 1 Samsung mobile phone, 2 Flash drives, 1 Touch screen mobile phone, 2 Security in a box books, 3 Nokia mobile phone, 1 Dell laptop, 1 Apple laptop, 1 HUAWE mobile phone with three SIM card, 12 video CDs.

Are laptops the equivalent of AK-47s?

Are cell phones the equivalent of hand grenades?

Are flash drives the equivalent of flash grenades?

Are security-in-a-box books the equivalent of improvised explosive devices (IEDs)?

Are video CDs the equivalent of RPGs?

Are SIM cards the equivalent of ammunition?

The entire case against the Zone 9 Bloggers is manifestly based on the T-TPLF’s warped imagination that the bloggers are members and operatives of Ginbot 7, an opposition movement the T-TPLF has declared a “terrorist organization”.

There is not an iota of evidence the bloggers are members of any organization, let alone Ginbot 7. The T-TPLF wants to “convict” the bloggers on the basis of imaginary guilt by association.

The Zone 9 bloggers have committed no crime. Their crime is exercising their right free speech!

The Zone 9 bloggers are themselves victims of crime and T-TPLF terrorism.

If Planet T-TPLF were the legendary Planet of the Apes, the Zone 9 bloggers would have had an excellent chance of escape.

The defense shall never rest.

But I rest my case in kangaroo/monkey kourt on Planet T-TPLF!

Professor Alemayehu G. Mariam teaches political science at California State University, San Bernardino.