የፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ንግግር በትግራይ ነጻ አውጪው መከላከያ ሠራዊቱ ውስጥ መናጋገሪያ ሆኗል

 

Birhanu

ከናትናኤል ኃይለማርያም

የአርበኞች ግንቦት ሰባትሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ለመከላከያ ሰራዊት አባላት፣የፌደራለ እና የክልል ፖሊስ አባላት፤ለአጋዚ ልዩ ጦር አባላት እና ለሌሎች ስርአቱ ታጣቂዎች ያደረጉት ጥሪ በሰራዊቱ ዉስጥ ከፍተኛ መነጋገሪያ ከመሆኑም በተጨማሪ ሰራዊቱ ከህዝብ ጋር ለመቆም የመጨረሻ ዉሳኔ ላይ እንዲደርስ ያደረገዉ ጥሪ ነዉ ሲሉ እነዚሁ ምንጮች ጠቅሰዋል።የተደረገዉን ጥሪ መቀበላቸዉን ለማመላከት ሀሳባቸዉን የገለጹት የሰራዊቱ አባላት እንዳሉት “ መከላከያዉ የህዝብ ሳይሆን የህዉሀት ቡድን አገልጋይ እየሆነ መምጣቱን ሙሉ በሙሉ ያወቁበት ደረጃ ላይ መድረሳቸዉን እና ሊቀመንበሩ እንዳሉት ሰራዊቱ የቁም እስረኛ ሲሆን በተለይ ህዝባዊ እምቢተኝነቱ ከተጀመረ ጀምሮ ምን እንደሚያደርግ እና ወዴት እንደሚሄድ የጠራ አቅጣጫ ባለማግኘቱ እና ባለበት ከፍተኛ ጫና የተነሳ አማራጭ በማጣት በሰራዊቱ ዉስጥ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

አክለዉም በአሁኑ ሰአት አዛዦቻቸዉ ድንጋጤ ዉስጥ ከመሆናቸዉ የተነሳ በሰራዊቱ ላይ ያለዉ ቁጥጥር እና ማስጠንቀቂያ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን እንዲሁም ከአንድ ብሄር የሆኑ አባላት ባንድ ላይ ለግዳጅም ሆነ ለስምሪት እንደማይመደቡና በግል ህይወታቸዉ ዉስጥ ስለላን እያካሄዱ ነጻነታቸዉን ፍጹም እንደነጠቋቸዉም ገልጸዋል፡፤በዚህም ምክንያት ከሰራዊቱ መካከል ያሉ አንዳንድ አድር ባይ አባላትን ሳይቀር የሕዉሐት ገደብ ያለፈ ጥርጥር ወደተቃዋሚነት ስለለወጣቸዉ በአሁኑ ሰአት በጥቂት ቁጥር ከሚቆጠሩ የግል ሰዎቻቸዉ በቀር ሰራዊቱ ልቡ ከህዝብ ጎን ሆኗል ብለዋል፡፤ በየጊዜዉ ለግዳጅ ሲወጡ ወደነጻነት ታጋዮች ከነትጥቃቸዉ የሚቀላቀሉ እና በቡድን በመደራጀት በየጫካዉ የሚመሸጉ የሰራዊት አባላት ቁጥር ከቀን ወደቀን እየጨመረ መምጣቱንም አመልክተዋል።
ፕሮፈሰር ብርሀኑ ነጋ ለሰራዊቱ ያደረጉትን ጥሪ በርካታ ሰዎች ለዉጥ የሚያመጣ ጥሪ መሆኑን በመግለጽ እነሱን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ መከላከያ ሰራዊቱ ወገኑ ላይ መተኮስ እንዲያቆም እና የመሳሪያ ነጠቃን እና በ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሰበብ የሚደረግባቸዉን የጅምላ አፈሳ እንዲሁም ግድያ በመቃወም ወደጫካ ከገቡ ወጣቶች እና አርሶ አደሮች እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበዉ፤ ከሳምንታት በፊት በፍኖተ ሰላም ከተማ 18 የመከላከያ ሰራዊቶች እና አራት ያጋዚ አባላት ሰራዊቱን ከድተዉ መዉጣታቸዉን አስታዉሰዋል።በተለይ በአማራ ክልል አገዛዙ በስፋት ለማከናወን አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ያለበትን የመሳሪያ ነጠቃ ሽሽት ወደየጫካዎች በመግባት ላይ ያለዉ ህብረተሰብ እየጨመረ መምጣቱን እና የኮማንድ ፖስት አባላት ወጣቶችን ያለምንም ምክንያት ስለሚያስሩዋቸዉ በፍኖተ ሰላም በከተማዋ ዉስጥ አዛዉንቶች፤ሴቶች እና ህጻናት ብቻ እየቀሩ እንደሆነ ገልጸዋል።
በተያያዘ ዜናም በባህር ዳር ከተማ ከስድስት ሳምንት በፊት ወቶ የነበረዉና መመዘኛዉ ከ10ኛ ክፍል በላይ የነበረዉ የመከላከያ ምዝገባ ፤ተመዝጋቢ በማጣቱ ምክንያት ማስታወቂያዉ ከወጣ ከሁለት ሳምንት በሗላ መስፈርቱ ወደ 6ተኛ ክፍል ዝቅ ብሎም ባለመሳካቱ በአሁኑ ሰአት ወጣቶች ወደ መከላከያ ቢገቡ ጥቅማጥቅሞችን እንደሚያገኙ ዉስጥ ዉስጡን በቅስቀሳ መልክ እየተወራ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ይህ በእንዲ እንዳለ የክልሉ አየር መንገድ ለአዉሮፕላን አብራሪነት እና ለቴክኒሺያንነት የቅጥር ማስታወቂያ ማዉጣቱን ተከትሎ ምናልባት በስራ አጥነት ሲሰቃይ የከረመዉን ወጣት በዚ መልክ በመመዝገብ ወደመከላከያ ስለጠና ሊወስዱት ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳላቸዉም ጠቁመዋል። የህዋት መንግስት ለመከላከያ እና ለፖሊስ አባላት መላቀቂያም ሆነ ፈቃድ መጠየቅ እንደማይቻል ቢያስተላልፍም እየከዱ እና እየጠፉ በሚለቁ አባላት ምክንያት አለመተማመን የመጣዉን የሰራዊቱን ቁጥር ለመጨመር በሰበብ አስባቡ በቁጥጥር ስር ያዋላቸዉን ወጣቶች በማባባል እና በማስገደድ ወደ ስልጠና ለማስገባት ሙከራ እያረገ ይገኛል ሲሉም ተደማጠዋል።
ከአመት በፊት ጀምሮ ሰራዊቱን እየለቀቁ የሚሄዱ አባላት ቁጥር በተለይ ህዝባዊ ትግሉ ከተጀመረ በሁዋላ በመጨመሩ፤የህዋት መንግስት በየክልሉ የመከላከያ ሰራዊትነት ምዝገባን ለማካሄድ ከጥሩ የደሞዝ ክፍያ ጋር ጥሪ ቢያደርግም የሚመዘገብለት ማጣቱ በሌሎች አስገዳጅ መንገዶች ወጣቶችን በማታለል በግዳጅ ወደ መከላከያ ያስገባበት ሁኔታ መኖሩን ሲዘገብ መቆየቱ ይታወሳል።

ነጭ በሬ ሆኜ ቆሜልሃለሁ እና ጨፉጭፈኝ! – ደመቀ ገሰሰ የኔአየሁ (PhD)

 

Ethiopiaእንደሚታወቀው ህወዓት ፋሺስት ጣሊያን አያቱ ሊፈፅም አቅዶ ያልተሳካለትን ኢትዮጵያን የማፈራረስ ፕሮጀክት በ1983ዓም ይዞ ብቅ በማለት ፋሺስት ጣሊያን ኢትዮጵያን ከፋፉሎ ለመግዛት በብሄር ተከፋፉሎ የተሰራውን የፋሺስት ጣሊያን ኢትዮጵያ ካርታ ከወዳደቀበት ፉርስራሽ አቧራውን አራግፎ አያቱ ጀምሮ ያልተሳካለትን ኢትዮጵያን የማፉረስ አጀንዳውን ይዞ ብቅ በማለት አንቀፅ 39 የሚባል እስከመገንጠል መብት በህገ-መንግስቱ ውስጥ በማስቀመጥ የአያቱን ፋሺስት ጣሊያን ፕሮጀክት ከዳር ለማድረስ አልሞ እና አቅዶ መነሳቱ ይታወሳል።

ፉሺስት ጣሊያን ለከፋፉለህ ግዛው ፕሮጀክቱ ትልቅ ደንቀራ ሆኖ የገጠመው ሃይል ቢኖር በአገሩ እና በሃይማኖቱ ድርድር የማያውቀው የአማራው ነገድ ነበር። ፋሺስት ጣሊያን እኛ የመጣነው የአውሮፓን ስልጣኔ እና ጥበብ ልናስተምራቹህ ነው እያሉ በመደስኮር ነበር። ይህ ዲስኩር ገና ምእራባውያን እራቁታቸውን በጢሻ ሲኖሩ የአለም ስልጣኔ ቀንዲል የሆነ ህዝብ መሆኑን እና ይህን ዲስኩርህን አይገባኝም ብሎ አሻፈረኝ ያለው የአማራው ነገድ በጣሊያኖች እይታ “ይህ የማይገባው መንቻካ ህዝብ አህያ ነገር ነው” ሲሉ ማጥላላታቸውን ተያያዙት። በተቃራኒ ከፋሺስት ጣሊያን ጋር የወገኑ እና በባርነታቸው ውስጥ የገባውን ባንዳ ወይም አስካሪ ደግሞ “እናንተ ትምህርት ቶሎ የሚገባቹህ ስልጡን ህዝብ ናቹህ” እያሉ የሰሜን ዘመዶቻችንን ማቆላመጡን ተያያዙት።

“ስልጣኔ አልገባው ያለው” የአማራ ችኮ ህዝብ ግን በአገሩ እና በማተቡ ቀልድ የለም ብሎ በሚያመልከው አምላኩ ምሎ እና ተገዝቶ ወራሪው ፋሺስት ጣሊያንን አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ ሊያደባያቸው መላው የኢትዮጵያን ህዝብ ከዳር እስከዳር በማስተባበር ባርነትን ሊጭኑብን የመጡትን ባእዳን በአድዋ ተራሮች ስር አጥንቱን ከስክሶ እና ደሙን አፉስሶ አፈርድሜ በማስጋጥ ሃያልነቱን እና አልበገር ባይነቱን አሳያቸው።

የአማራው ህዝብ ኢትዮጵያ ሃገራችንን ባህር አቋርጠው የመጡትን ባእዳን ሁሉ ሌላውን ኢትዮጵያዊ ሁሉ እያስተባበረ እና ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር እየተባበረ ይቺን አገር ለዚህ ትውልድ ዋጋ ከፉሎ ያቆየ ህዝብ ነው። የአማራው ህዝብ በታሪኩ አንድም ቀን ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቹ ተለይቶ ብቻውን በመቆም የተዋጋው የውጭ ወራሪ ሃይል አልነበረም። የልቁንም እኒህ አርቀው የነገውን ያስቡ የነበሩት ቅደመ-አያቶቻችን በተናጠል የሚደረግ ትግል ውጤታማ እና ዘላቂ ትብብርን የማያመጣ እንደሆነ በመረዳታቸው ሁሉንም ኢትዮጵያዊ እያስተባበሩ ነበር ዳርድንበራቸውን ሲቆጣጠሩ የኖሩት።

በርካታ ጊዜ አገራችንን ቅኝ ለመያዝ የቋመጡት ፋሺስት ጣሊያንን በመመከት ዛሬ ላይ በአለም ህዝብ ዘንድ አንገታችንን ቀና ብለን እንድንሄድ አኩሪ ታሪክ ሰርተውልን አልፈዋል። በአደዋ ላይ አይቀጡ ቅጣት ቀምሶ የተመለሰው ጣሊያን ተመልሶ በሁለተኛው የአለም ጦርነት መባቻ ላይ አገራችንን ሲወር ከአደዋው ጦርነት እጅግ በተሻለ ዘምነው በሰማይ እየበረሩ እኛ ግን አሁንም የነበረንን እንደያዝን በመውዜር እና በአጋሰስ ብቻ ገጠምናቸው። ይህ የነበረው የትጥቅ አለመመጣጠን እንደማያዋጣን አብዝተው የተገነዘቡት አያቶቻችን ትልቁን ዲፕሎማሲ በመስራት እንግሊዝ ከጎናችን እንድትሰልፉ እና ለዳግም ድል እንድንበቃ አድርገውናል።

ይህን ታሪክ ወደኋላ ሂደን እንድናስታውስ አስፈላጊ የሆነበትም ምክንያት ዛሬ ላይ አማራው ምን ማድረግ እንዳለበት ለማስታወስ ነው። ህወዓት የትግራይን ሪፕብሊክ ለመመስረት አቅዶ ትግሉን ቢጀምርም እድል ቀንቶት የደርግን መንግስት ከሻብያ ጋር ተባብሮ እንደሚጥለው ሲገባው መገንጠሉ እንደማይጠቅመው በመረዳት ኢህዴግ የሚባል የድርጅቶች ስብስብ በመፉጠር ኢትዮጵያዊ መስሎ ከች አለ። ወያኔ ያኔ በለሱ እንደቀናው ትግራይን ገንጥሎ ቢሄድ ኖሮ ምን ሊደርስበት ይችል እንደነበር ለማወቅ ነብይ መሆን አያስፈልግም። የልቁንም ይህ ችግር የገባቸው ህወዓቶች ኢትዮጵያን ጌታቸው ፋሺስት ጣሊያን ለከፋፍለህ ግዛው አላማ ፈጥሮት የነበረውን የብሄር ካርታ አቧራውን አራግፎ አገሪቱን በብሄር ከፋፉሎ እየው እስከዛሬ ድረስ ኢትዮጵያዊ ካባ ለብሶ ሁሉንም ብሄሮች ለራሳቸው የውስጥ ባንዳ የሚሆኗቸውን የየብሄሩ ተወላጆች በፓርቲ ስም በማዋቀር እየገዙ ይገኛሉ። እዚህ ላይ ማስተዋል ያለብን ህወዓት 25ዓመት ሲገዛ ብቻውን በህወዓት ስም አይደለም። የልቁንም ብሄር ብሄረሰባችን መብት አስከብሬአለሁ በማለት የሁሉንም ዘውጎች ተወካዮች በመያዝ ነው። ብአዴን፣ደህዴን፣ኦህዴድ እና መሰል የብሄር ተቀፅላ ፓርቲወችን ከጎኑ በማሰለፉ ነው።

ህወዓት አሁን የሚደረገውን የነፃነት ትግል ለማፈን የቀረበው ህወዓት ብቻ ሆኖ አይደለም። የልቁንም አብዛኛው የመከላከያ እና ፓሊስ ሰራዊት ከትግራይ ውጭ በሆኑ ሌሎች ኢትዮጵውያን አደራጅቶ የመሪነቱን ቦታ ደግሞ ለሚያምናቸው የትግራይ ሰወች በመስጠት ነው እየወጋን ያለው። ህወዓት ብቻውን ከኢትዮጵያውያን ጋር የሚዋጋ ቢሆን ኖሮ ይህን ያህል ዋጋ ባልተከፈለ ነበር። እውነታው ግን ይህ አይደለም። ይህ ማለት ወያኔ ኢትዮጵያውያንን ይዞ ሲወጋን ወያኔን ልናሸንፉ የምንችለው እንደ ኦነግ ወይም የብሄር ድርጅቶችን በማዋቀር በብሄርህ ብቻ ስትደራጅ ሊሆን አይችልም። ከ25 ዓመት በላይ የአገሪቱን ጠቅላላ ሃብት በበላይነት በመቆጣጠር እና በስመ ፀረ-ሽብር አጋርነት ከምእራባውያን በሚደረግለት ልገሳ እና ስልጠና የፈረጠመን ሃይል እና ሌላውን ኢዮዬጵያውያን ይዞ በኢትዮጵያ ደረጃ ሲገጥመን እኛ አማራ ነፃ አውጪ ድርጅት፣ ኦሮሞ ነፃ አውጭ ድርጅት፣ወዘት እያልን በብሄር ጠበን ስንወርድለት የበለጠ ነጭ በሬ ሆነን ህዝባችንን ኑና ጨፉጭፉልን ከማለት ያለፈ ትርፉ ሊኖረው አይችልም። ትላንት ኢትዮጵያውያንን በማስተባበር የአገራችንን ዳር ድንበር ከጠላት ሲከላከል የነበረው ትልቁ የአማራ ነገድ ወያኔ በፈጠረለት የብሄር ቋት እንሶ በመደራጀት አማራውን ነፃ ሊያወጣ የሚችልበት ምድር ላይ ያለ እውነታ አይደለም። ይህ ዝም ብሎ ሳያሰላስሉ እና ኢትዮጵያ የተሰራችበትን የታሪክ ምህዳር ሳያገናዝቡ፣የቀጠናውን ጂኦ ፓለቲካል አሰላለፉ ምን እንደሆነ ሳያስተውሉ እና ወያኔ አሁንም በኢትዮጵያ ካባ ስር ሌላውን ኢትዮጵያዊ አስተባብሮ እየወጋህ እያለ አንተ ከነበረህ የታሪክ ደረጃ ወርደህ በአማራነት ስትደራጅለት ለወያኔ ድግስ እና ምላሽ ሆንክለት ማለት ነው። እንዲያውም ይኽውልህ እያለ የበለጠ ከሌላው ጋር ያላትምህ ይሰራል እንጂ እንዲህ በቀላሉ ሽር የሚባልበት መንገድ አይመስልም።

በአማራ ብሄርተኝነት ስም እንደራጅ ብለው የሚያስቡ ቡድኖች ሃሳባቸው ትክክል ሃኖ ሳለ አሁን ላለንበት እውነታ ውጤታማነቱ እጅግ አስቸጋሪ ነው። ወያኔ እና ሻብያ ብሄር ተኮር አጀንዳ ይዘው ሲታገሉ ድል የቀናቸው ትልቁ ምክንያት በዘመኑ የነበረው የቀዝቃዛው ጦርነት ትልቅ አስተዋዖ ነበረው። ዛሬ ላይ የጎረቢት አገሮች ሳይቀር በወያኔ ቀኝ እጅ ውሥጥ ባሉበት በአሁኑ ወቅት፣ በፀረ-ሽብር ምክንያት ህወዓት-ኢህዴግ ከምእራባውያን ሃያላን ጋር እጅ እና ጓንት ሆኖ እየሰራ ባለበት ወቅት፣ እራሱ ወያኔ ኢትዮጵያዊ ካባ ለብሶ እየታገለን ባልንበት በዚህ ሰዓት እንደ አማራ ነፃ አውጭነት፣እንደ ኦሮሞ ነፃ አውጭነት ወዘተ ሆነን ዳር ልንደርስ አንችልም። እያየነው ያለውም ሃቅ ይህ ነው። በብሄር ተደራጅቶ ሊሳካ የሚችል ቢሆን ኖሮ ኦነግ ከ40ዓመት በላይ ሚሊዮን ኣሮሞወችን ነጭ በሬ ሆኖ በመቆም ለእልቂት ዳረገ እንጂ ያተረፈው ትርፉ የለም። አማራውም የተለየ ሊሆን አይችልም ።ቅደመ አያቶቻችን ጠላትን በህብረት ተፋልመው አሸነፉት እንጂ በተናጠል አልሄዱም።

ዛሬ ላይ የተለየ እውነታ የለም። የልቁንም ዛሬ ላይ ወያኔ ያልገደልው እና ያላሰቃየው ህዝብ የለም። ሁሉም ህዝቦች የወያኔ ጭካኔ ደርሶባቸዋል። የኦሮሞው ወጣቶች አብዬት እና የአማራ ህዝብ ተጋድሎ እያሳየን ያለው ነገር ቢኖር ወያኔን ዘረኛ ቡድን አድርጎ በያሉበት እየተፋለሙት ይገኛሉ። ወያኔ ዛሬ ላይ በኢትዮጵያዊ ካባ የተጀቦነበት ካብ እየተናደ ተነጥሎ እየተመታ ነው። ይህ ሃቅ ሆኖ ሳለ ልክ እንደ ቅድመ-አያቶቻችን ተባብረን በአንድ ላይ ለፉትህ እና እኩልነት መታገል በእኔ እይታ ብቸኛ አዋጪ መንገድ ይመስለኛል። ነገር ግን የአለምን የፓለቲካ ሚዛን ሳይመረምሩ፣ምድር ላይ ያለውን ሃቅ ሳይመለከቱ በኢሞሽን ብቻ በመነዳት የአማራ ብሄርተኝነት የአማራውን ችግር ይፈታል የሚል እምነት የለኝም። የልቁንም በወያኔ ክፉ በትር የተጎዱ እና እየተጎዱ ያሉትን ሌሎች ወገኖቻችን ጋር በመተባበር ፉትህ የሰፈነባት ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት መታገል አውጭው መንገድ ነው።

እስኪ አስቡት ወያኔወች ኢትዮጵያ ሆነው ሲገጥሙን በምን መስፈርት ነው አማራ በአማራነት ሆነን ልንገጥማቸው ያሰብን? እናም እናስተውል! የአንድ ድርጅት ስኬት የሚለካው ይዞት የተነሳው አላማው አዋጪነቱ(feasibility) ሲኖረው ነው። ለሚደረገው ትግል የአለም አቀፉ የትብብር ድጋፉ ሊያገኝ መቻል አለበት። የጎረቢት አገሮች ሚና ተለይቶ መታየት አለበት። የአማራው ስነ-ልቦና መታወቅ አለበት። እውነት ለመናገር ይህ በአማራነት ብቻ ተደራጅቶ የአማራንም ህዝብ ሆነ ኢትዮጵያን ነፃ ማውጣት የሚቻል እንኳ ቢሆን እጅግ እረጅም አመታትን የሚፈጅ እና ኪሳራውም የከፋ ነው የሚሆነው።

ይህን ስል አማራው መደራጀት የለበትም እያልኩ አለመሆኔ ሊሰመርበት ይገባል። አማራው አሁን እያደረገ ያለውን ተጋድሎ ተቀናጅቶ መቀጠል ይኖርበታል። ነገር ግን የአማራ ነፃ አውጭ ብሎ እራስን ነጭ በሬ አድርጎ ለጥቃት ማጋለጥ ሳይሆን እንደ ቅድመ አያቶቻችን ሌሎችን ብሄሮች ተባብሮ እና አስተባብሮ ወያኔ ነጥሎ ለመምታት ሲቻል ብቻ ነው። ወያኔ በህብረ-ብሄራዊ ጭንብል ኢትዮጵያዊ ሆኖ ሲገጥመን እኛ ወርደን አማራ ሆነን ልንገጥመው ማሰብ ለወያኔ የሞራል ልእልና ካርድን መሸጥ ብቻ ሳይሆን በራሳችን ወገን ሳይቀር ወያኔ አስተባብሮ ልክ በኦነግ እና ኦብነግ ላይ ያደረሰውን የጭካኔ በትር በእኛ ላይ እንዲዘምትብን ነጭ በሬ መሆን ነው።

አንድ አማራውን የሚወክል ፓለቲካል ፓርቲም ቢኖር መላክም እንጂ ችግሩ አይታየኝም። አንድ ጠንካራ የአማራ ፓለቲካ ፓርቲ ካለ ለሽግግር መንግስትም ሆነ በዘላቂነት የአማራውን ፉላጎት እና ጥቅም የሚያስከብር ፓርቲ ሊኖር ይገባል። በእኔ እይታ የአማራውን ህዝብ ችግር እና ትግል የሚዘክር እና የአድቮኬሲ ስራ የሚሰሩ እንደ ሞረሽ-ወገኔ አይነት ድርጅቶችን ማጠናከር፣ ህዝባችን ከሌሎች ኢትዮጵያዊ ወገኖቹ ጋር ሆኖ የሚያደርገውን ተጋድሎ መርዳት እና ማገዝ ወቅቱ የሚፈልገው አዋጪ መንገድ እንደሆነ አስባለሁ።

ቸር ይግጠመን!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ከህዝቦቿ ጋር በክብር ትኑር!

 

“መፍራትና መጠንቀቅ ሰንደቅ ዓላማ ለብሰው ሀገር የሚያፈርሱትን ነው” (ይገረም አለሙ)

ይገረም አለሙ

ከስራ አምስት አመት በፊት ነው ኤዴፓ በቅሎ ቤት በሚገኘው ጽ/ቤቱ  እለተ ግንቦት 20ን አስመልክቶ አንድ ፕሮግራም አዘጋጅቶ ተገኝተናል፡፡ ከተናጋሪዎቹ አንዱ የነበሩት የወቅቱ የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ ባደረጉት ንግገር ውስጥ  መፍራትና መጠንቅ ካለብን ሰንደቅ ዓላማ ለብሰው እኛኑ መስለውና ተመሳስለው ሀገር የሚያፈርሱትን በመካከላችን የሚገኙትን ነው የሚለው አረፍተ ነገር  በአእምሮየ ተቀርጾ አብሮኝ ይኖራል ፡፡

ከሰፊው ኢትዮጵያዊ ማእድ ይልቅ በትንሽ ገበታ መብላት አስመኝቶአቸው ይህንኑ ያሳካልናል ባሉት መንገድ የሚደነቃቀፉትም ሆኑ ዛሬ እየሞተ ካለው ወገናቸው ሞት ይልቅ የዛሬ መቶ አመት ተፈጸመ የሚሉት በፈጠራ ድርሰት የተቀባባ በደል የሚያማቸውና  በዛን ዘመን ተፈጸመ ለሚሉት ዛሬ ማንን አንደሚበቀሉ ባይታወቅም ለበቀል ያሰፈሰፉ፣ ለመለየት የሚጣደፉ ሌሎችም ሰበብ ምክንያት እየፈጠሩ ኢትዮጵዊነትን የሚያኮስሱና ከቻሉም ሊያጠፉ የሚከጅሉ ወያኔን ጨምሮ በንግግራቸውም በተግባራቸውም ይታወቃሉና ሀገር የማፍረስ አደጋቸው አምብዛም ነው፡፡

የእነዚህ አደጋ ሊከፋም ሊሰፋም የሚችለው ኢትዮጵያን የሚለው ወገን እነዚህን ወገኖች በደንብ ለይቶ አውቆና ተጠንቅቆ ተባብሮና ተጠናክሮ ህልማቸው እንዳይሳካ መስራት ካልቻለ ብቻ ነው፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ቅዱስ አስተሳሰብ የራቃቸው ወጎኖች በቆጥር ትንሽ፣ ራእያቸው ጠባብ፣ ፍላጎታቸው ከራስ ጥቅም መሻት ያልዘለለና አንወክለዋለን የሚሉትን የህብረተሰብ ክፍል አንኳን የማያማክል በመሆኑ ኢትዮጵያን የሚለው ወገን ካልተዘናጋና እሱም ርስ በርሱ መስማማት ተስኖት ምቹ ሁኔታ ካልፈጠራለቸው በስተቀረ በምንም መልኩ ህልማቸው ሊሳካ ቀርቶ ስጋት ሊሆኑ አይችሉም፡፡

በወያኔ አብዮት ማግስት በተፈጠረ የፖለቲካ ስካር አሁን ከምንሰማቸው የባሱ ነገሮች በመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ሳይቀር ሲነገሩ ሰምተናል፤ተጽፎ አንብበናል፡፡ ግና ስካሩ ሲበርድ እንኳን ንግግሩ ተናጋሪዎቹ በቦታቸው አልተገኙም፡፡ እናም አንድ ነገር በተከሰተ ቁጥር ፍላጎታቸው የሚሳካ የሚመስላቸው ቅዠታሞች በየመድረኩ ቅዠታቸውን ቢናገሩና መሰሎቻቸው ቢያጨበጭቡላቸው እነርሱንም ሆነ ተከታዮቻቸውን ይበልጥ አንድናውቃቸውና ቀይ መስመር ውስጥ አንድናስቀምጣቸው ይረዳናል አንጂ ስጋት ሊሆኑን አይችሉም፡፡ እንደውም አንዲህ አይነቶቹን ሌሎቹንም ሰዎች ይበልጥ አንዲታወቁ በየመድረኩ እየጋበዙ ማናገር ነው፡፡ አበው ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል እንዲሉ የፖለቲከኛ ሆድ ያባውን የሚያወጣው ጭብጨባ ነውና   የውስጣቸውን አንድም ሳያስቀሩ አንዲናገሩ በጭብጨባ ማሰከር ነው፡፡ ከዛ በደንብ እናውቃቸዋለን ባወቅናቸው መጠንም አንጠነቀቃቸዋለን እንጠብቃቸዋለን ፡፡ ሰው የሚያስቸግረው ማንነቱና ምንነቱ እስኪታወቅ ነው ይባል የለ!

ይልቅ በንቃት መከታተል ቃል ከተግባር እየመዘንን መለየት ያለብን ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ ከአስራ አምስት ዓመት በፊት አንደተናገሩት ሰንደቅ ዓላማ ለብሰው ሀገር ለማፍረስ ወስጥ ውስጡን የሚያደቡትን፡፡ እንደዚህ አይነቶቹ ሰዎች ወገኔ ተበደለ፣ ሀገሬ ተጠቃ፣ ብለው እንባ ለማንባት የሚገዳቸው አይደሉም፡፡ሰንደቅ ዓላማ ለብሶ ለመፎከር ወያኔን ጥንብ ርኩሱን እያወጡ ለመስደብ ወደር አይገኝላቸውም፡፡

ይህን አድራታቸውን እያየንና እየሰማን ከእነርሱ ወዲያ ሀገር ወዳድ ለአሳር ከእነርሱ በላይ ታጋይ ከየት ሊገኝ ወዘተ በማለት አድናቆታችንን እየገለጽን ከሆኑት አይደለም ፈጽሞ ሊሆኑት ከሚችሉት በላይ እያሞገስንና እያወደሰን እውነተኛ ማንነታቸውን ለመደበቅ  ከሚለብሱት ሰንደቅ ዓላማ በላይ ከፍተኛ ሽፋን አንሰጣቸዋለን፡፡እናም ሳናውቅ እየተከተልናቸው ብቻ ሳይሆን እየደገፍናቸው ሀገር ለማፍረሰ ይህም ባይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ከአገዛዝ አንዳይላቀቅ ለሚፈጽሙት ድብቅ ዓላማቸው አባሪ ተባባሪ ስንሆን ኖረናል፣ አሁንም እንደዛው ያሉ ብዙዎች ይኖራሉ፡፡

እስቲ ዛሬ በዚህ ወሳኝ ወቅት ሳንደባበቅ ደፈር ብለን ለመነጋገር እንሞክር፡፡ ሰንደቅ ዓላማ ለብሶ የሚፎክረው፣ በወያኔ ላይ የውግዘት የቃላት ናዳ የሚያወርደው፣ ወያኔ ዜጎችን በገደለ ቁጥር ያዙኝ ልቀቁኝ የሚለው ወዘተ ሁሉ በርግጥ ለሀገር ነጻነትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የሚታገል ቢሆን ኖሮ፤ ዛሬ በምንገኝበት ሁኔታና ደረጃ እንገኘ ነበር፡፡

በእውነት ሰንደቅ ኣላማ ለብሶ ኢትዮጵያዊነትን የሚዘምረው ሁሉ ሀያ አምት ዓመታት በህዝብ ላይ የተፈጸመው ይቅርና  በዚህ አንድ መት የተፈጸመው ግድያ እስራትና ማሰቃየት የሚያመው ቢሆን ኖሮ ተቀዋሚዎች አሁን በዚህ ወቅት በሚገኙበት ደረጃ ላይ መገኘት ነበረባቸው፡፡

ሰንድቅ ዓላማ ለብሰው  የምናያቸው ፖለቲከኞች በቃላት እየደለሉ በተግባር ግን  ከሚናገሩት ተቃራኒ ዓላማ የሚያራምዱ ካልሆኑ በአደባባይ ለሚናገሩት ለአንዲት ኢትዮጵያ ነጻነትና ሁሉንም በእኩልነት የሚያስተዳድር ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመመስረት ይህን ያህል ፓርቲ/ድርጅት ያስፈልግ ነበር፡፡ በአንድ ብሄር ስም ሶስት አራት ድርጅት፣ ተመሳሳይ ሀገራዊ ፕሮግራም ጽፎ በሰዎች ምክንያት ሶስት አራት ፓርቲ መመስረት ይገባ ነበረ፣ ይህን አድርገው ደግሞ  መልሰው የእኛ አንድ አለመሆን ነው የወያኔን እድሜ ያራዘመው በማለት ያደነቁሩናል፡፡ በዚህም ፕሮፓጋንዳ ራሳቸውን ተባብሮ የመስራት ፈላጊ አድርገው በሌሎች ላይ ጣት ለመቀሰር ቅድሚያውን የሚወስዱትና በድፍረት የሚናገሩት እነዚሁ በዶ/ር አድማሱ ገለጻ ሰንደቅ ኣላማ ለብሰው ሀገር የሚያፈርሱ የተባሉቱ ናቸው፡፡

ያላችሁት በዝታችኋል፣ በተናጠልም መጠናከር ተስኖአችኋል የምትነግሩን የምታምኑበትን ከሆነ ኮከባችሁ የሚገጥም እየተመራረጣችሁ ተባበሩ ተብሎ ልመናም ጫናም ተደርጎ  ህብረት ፈጠርን ቅንጅት መሰረትን ይሉና  የዚህም መሪ ተዋናይ እነርሱ አንደሆኑ አድርገው ከተግባሩ ፕሮፓጋንዳውን አግዝፈው ይነግሩንና ውለው ሳያድሩ ወደ እምነታቸው ተመልሰው የተገናኘውን ሲያላያዩ የተባበረውን ሲፈርሱ ይገኛሉ፡፡እነርሱ ያልገቡበት ህብረት ከተፈጠረም ከዳር ሆነው ውግዘታቸው ትችታቸው ሲብስም ውንጀላቸው አያድርስ ነው፡፡ ደጋፊዎቻቸውም የሚነገራቸውን ለማስማት አንጂ የሚሰራውን ለማየት አይናቸውን አይገልጡምና እገሌን ያላከተተ ህብረት አነ እገሌ የሌሉበት ቅንጅት ወዘተ በማለት መሪዎቻቸውን ተከትለው የቃላት አረራቸውን ይተኩሳሉ፡፡ ተረዳድተውም ለማደናቀፍ ይሰራሉ፡፡

በአንድ በኩል  ብዙዎችን ወደ ጥቂቶች ለመቀነስ ሲደከም በሌላ በኩል ደግሞ አንዳንዶች አንድ ፓርቲ የነበሩት  አንደ አሜባ ራሳቸውን እያባዙ አንዳንዶች ደግሞ እኛስ ከማን እናንሳለን በሚል ስሜት በሚመስል አዲስ ፓርቲ እየፈጠሩ ልዩነቱን ያሰፉታል ችግሩን ያባብሱታል፡፡ ትግሉ ወደ ፊት ከወያኔ ጋር መሆኑ ይቀርና ሰበብ ምክንያት እየተፈጠረ የጎንዮሽ ይሆናል፡፡

ወያኔ ተንገዳግዶ ላለመውደቅ የመጨረሻ አማራጭ ያለውን  የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ባወጀበት በዚህ ወቅት በተቃውሞ ጎራ የተሰለፉት ወገኖች ሁሉም ለሀገር ነጻነትና ለዴሞክራሲዊ ሥርዓት ከሆነ ትግላቸው  ወያኔ ከተንገዳገደበት መልሶ እንዳይቃና እነርሱም ትግላቸውን ማቀናጀት ካልሆነም የጎንዮሹን ትግል ማቆም የሚያስችል ለስድስት ወራት የሚቆይ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ/ስምምነት ማውጣት በቻሉ ነበር፡፡ ግን ሰንደቅ ዓላማ ለብሰው ሀገር ለማፍረስ የሚሰሩ፣የነጻነት ታጋይ መስለው ለወያኔ እድሜ መርዘም የሚጥሩ፣የዴሞክራሲ ናፋቂ መስለው ከራስ በላይ የማያስቡ አሉና በሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻቸንን ሞት በየመድረኩ እየደሰኮሩ እነርሱ ግን ከነበሩበት አንድ ርምጃ ወደ ፊት መራመድ አልቻሉም፡፡

ኢትዮጵውያን ከወያኔ አገዛዝ እንዳንላቀቅ  የሚያደርጉን ከዚህም አልፎ እኔ ከሌለሁ ኢትዮጵያ ትበታተናለች የሚለው የወያኔ ማስፈራሪያ እውን የመሆን አጋጣሚ እንዲያገኝ የሚሰሩ፣ ኢትዮጵያ ትበታተን ብለው በአደባባይ የሚነግሩን ሳይሆኑ ሰንደቅ ዓላማ ለብሰው ሳይታወቅና ሳይነቃባቸው ሀገር የማፍረስ ተግባር ላይ የተሰማሩት ናቸው፡፡ ስለሆነም ከፍሬያቸው ታውቁዋቸዋላችሁ ተብሎ አንደተጻፈው  ሰንደቅ ዓላማ ለብሰው በመታየታቸው ወይንም  በማራኪ ቃላቶቻቸውና በአዞ እንባቸው ሳንታለል በተግባራቸው እንመዝናቸው አንለያቸው አንወቃቸው፡፡ ሳናውቃቸው የእኩይ ተግባራቸው ተባባሪ በመሆን ከኋላ ጸጸትና የአብሮ ተጠያቂነት ለመዳን መፍራትም መጠንቀቅም ያለብን በአደባባይ ወጥተው ቅዠታቸውን የሚነግሩንን ሳይሆን ሰንደቅ ዓላማ ለብሰው ከእነርሱ በላይ ሀገር ወዳድ ታጋይ የሚባልላቸውን ነው፡፡

 79 2share0

የለውጥ ሃይሎች ግልጽና……. ክፍል ሁለት [ኤርሚያስ ለገሰ]

ጆቤ እንኳን ደህና አልመጣችሁ!!
ለህዝብ ውይይት መድረክ የተዘጋጀ (ሂውስተን/ቴክሳስ)
                                                            

   ኤርሚያስ ለገሰ
       የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንና ራዲዮ(ኢሳት)
    ጥቅምት/2016
                             

                  ማስታወሻ        

ይህ ጽሁፍ ከራሴ ውጭ የምሰራበትን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንና ሬዲዮ (ኢሳት)ን ጨምሮ የማንንም አቋም አያንፀባርቅም::

መግቢያ

udj-ethiopia-satenaw-news“የለውጥ ሃይሎች ግልፅና ደፋር ውይይት ለመፍትሔና የጋራ ድል” በሚል አቢይ ርዕስ ተከታታይ መጣጥፍ እየቀረበ ነው። ከዚህ ቀደም “በክፍል አንድ” በተሰራጨው ጽሁፍ ሁለት ቁምነገሮችን ለመዳሰስ ተሞክሯል። የመጀመሪያው፦ ግልጽና ደፋር ውይይት የምናደርግባቸው መሰረታዊ ምክንያቶች ምን እንደሆኑ ለመዘርዘር ተሞክሯል። ዛሬ አገራችን ያለችበት ሁኔታ የሚያሳስበው ዜጋ ባለመኖሩና አገር አደጋ ላይ በወደቀችበት ሁኔታ በመተማመን ላይ የተመሰረተና የጋራ ድል (win- win) በሚያረጋግጥ መልኩ ምክክር መካሄድ እንዳለበት የተገለጠበት ነው። መጣጥፍ በኢትዮጵያ ውስጥ የስርአት ለውጥ መምጣት አለበት በማለት የሚንቀሳቀሱት ሁሉም የለውጥ ሃይሎች የዛሬና የነገን ኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በሚወስኑ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ምን እንደሚያስቡ ለህዝቡ ማቅረብ እንዳለባቸው የሚጠይቅ ነው።

ሁለተኛው፦ በተከታታይ ለሚቀርቡት ጽሁፎች መነሻ ከተደረጉ አምስት ታሳቢዎች ውስጥ ሦስተኛው ታሳቢ (“የአዲስ አበባ ነዋሪ የስርአት ለውጥ ይፈልጋል። ህዝባዊ ማዕበሉን ለማቀጣጠል ዝግጁነቱ ከፍተኛ ነው”) የሚለው ሃሳብ የተስተናገደበት ነው። ለማስታወስ ያህል “በክፍል አንድ” በቀረበው ጽሁፍ የቀረቡት አምስት ታሳቢዎች የሚከተለውን ይላሉ

 ታሳቢ አንድ፦ የህዉሃት አገዛዝ ይወድቃል። የሚወድቀው ግን በከባድ መስዋዕትነት ነው። ከተከፈለው ያልተከፈለው መስዋዕትነት ይበልጣል።

ታሳቢ ሁለት፦ የኢትዮጵያ አንድነት እንደተጠበቀ ይቆያል። የለውጥ ሃይሉ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ አይደራደርም።

ታሳቢ ሦስት፦ የአዲስ አበባ ነዋሪ የስርአት ለውጥ ይፈልጋል። ህዝባዊ ማዕበሉን ለማቀጣጠል ዝግጅነቱ ከፍተኛ ነው።

ታሳቢ አራት፦የለውጥ ሃይሉ ከህወሃት የቀድሞ የጦር ጄነራሎችም ሆነ አመራሮች ብዙ መጠበቅ የለበትም።

ታሳቢ አምስት፦ ከአጭር ጊዜ አኳያ የተገኘው ድል በብስለትና በፅናት ካልተያዘ ሊዳፈን ይችላል።

 

በመሆኑም በዚህ ጽሁፍ ላይ ለዋናው ሰነድ መነሻ ከሆኑት ውስጥ በ”ታሳቢ አራትነት” የለውጥ ሃይሉ ከህወሃት የቀድሞ የጦር ጄነራሎችም ሆነ አመራሮች ብዙ መጠበቅ የለበትም”) የሚለው ይቀርባል። በመጣጥፍ ሆድ እቃ ውስጥ የትግራይ ኤሊቶች በተለይም የቀድሞ የህዉሃት የጦር መኮንኖች መደ መድረኩ አሁን ለምን እንደመጡ፤ ይዘው የመጡት እጀንዳ ምን እንደሆነ፤ ወደፊት መምጣታቸው የሚያስገኘው ጥቅምና ጉዳት ለውይይት መነሻ በሚሆን መልኩ የቀረበበት ነው። ከዚህም በተጨማሪ ህሃትን ከመገርሰስ አኳያ ዋነኛ የትግል ማዕከሎችና ፓሎች (ምሰሶዎች) የትኛዎቹ እንደሆነ ለማሳየት ይሞክራል።

(“ክፍል አንድ” አግኝታችሁ ማንበብ ያልቻላችሁ ሰዎች በሳተናው፣ ኢትዮ-ሚዲያ ፎረም፣ ዘሃበሻ፣ ህብር-ሬዲዮ ድረ-ገጾች ላይ ማግኘት ይቻላል።)

(ታሳቢ አራት)

 የለውጥ ሃይሉ ከህወሃት የቀድሞ የጦር ጄነራሎችም ሆነ አመራሮች ብዙ መጠበቅ የለበትም።

ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመናት ህዉሃት በብሔር ብሔረሰቦች ዲሞክራሲያዊ መብቶች እየማለና እየተገዘተ ህዝቡን ለማታለል ብሎም ለመለያየት ቢሞክርም ያሰበውን አላማ ሊያሳካ አልቻለም። ለሁሉም ግልጽ እንደሆነው በአገራችን የሰላም እጦት ከጫፍ እስከ ጫፍ እየታየ ነው። የስርአት ለውጥና የነፃነት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተለያዩ የትግል ስልቶች ተቀርፀው ወደ ትግባር ተቀይረዋል። እየተደረጉ ያሉት ትግሎች አስተሳስረን ስንመረምር አሁን ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግልና ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ወደ መቃብር የወረደበት ሆኖ እናገኘዋለን። ከዚህ በኋላ ህዉሃት መንግስታዊ የበላይነትን ባገኘበት ሁኔታ የምርጫ ፖለቲካ አጀንዳው ተዘግቷል። የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች እንዳሉት በምርጫ ፖለቲካ መቃብር ላይ ጥቁር አበባ ተቀምጦበታል። መቃብር ፈንቅሎ ትንሳኤ ይፈፀም ይሆን ለወደፊት የምናየው ይሆናል። ተስፋ አለኝ።

ከዚህ ጋ ተያይዞ ህዉሃት መራሹ ድርጅት በየጊዜው የሚሰጠው ድርጅታዊ መግለጫና እሱን ተከትሎ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተስፋ የሚያስቆርጠው የአገሬው ህዝብና የአለም መንግስታትን ብቻ አይደለም። የስርአቱ መስራችና ባለቤት የነበሩ እንዲሁም በተለያየ ከፍተኛ የፖለቲካና ወታደራዊ ስልጣን ላይ የነበሩትን ጭምር ነው። በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚገኙ የኢትዮጵያ ሚዲያዎችን ያጨናነቁት ጄኔራል አበበ እና ጄኔራል ፃድቃን በስርአቱ ምላሽ ላይ ምን ያህል ተስፋ እንደ ቆረጡ መገመት ይቻላል። “የስርአት ችግር ስላለ፣ ኢህአዴግ የተቀባይነት ችግር ስላጋጠመው የስርአት ለውጥ መምጣት አለብት!” ብሎ የተናገረው አንደበታቸውና የከተበው ብዕራቸው ዞር ብለው ሲመለከቱ ማፈራቸው የሚቀር አይደለም። እነ ፃድቃን “ሀገሪቷ የመበታተን አደጋ ሊያጋጥማት ይችላል” ቢሉም የቀድሞ የትግል ጓዶቻቸውና የስልጣኑ ባለቤቶች “ህገ-መንግስታዊና ዲሞክራሲያዊ የፖለቲካ ስርአት በጽኑ መሰረት ላይ ተገንብቷል” የሚል ዲስኩር ያሰማሉ።

እነ ጆቤ “ህዝቡ በተስፋ እጦት ውስጥ ገብቷል” ብለው ሲፅፉ በተቃራኒው እነ አባይ ፀሀዬ “የአገራችን ህዝቦች በኢትዮጵያ የፈነጠቀውን የልማትና የዲሞክራሲ ጮራ ተማምነው በለመለመ ተስፋ ወደፊት ይመለከታሉ” የሚል ዘመን ተሻጋሪ ማብራሪያ ይሰጣሉ።  እነ ፃድቃን በቀኝ ሆነው የመቶ ፐርሰንት ምርጫ በህዝብ ማላገጥ ነው” በማለት ብዕራቸውን ሲያነሱ በግራ የተሰለፉት እነ በረከት “ኢህአዴግ ስራ በምርጫ ካርድ የተሰጠውን ሃላፊነት አደራ ለመወጣት ቆርጦ ተነስቷል” ይሉናሉ። አራንባና ቆቦ!!

እዚህ ላይ በሁለቱ የቀድሞ የጦር አዛዦችና የህዉሃት መራሹ መንግስት ሃይሎች መካከል በሁሉም ጉዳይ ተቃርኖ ውስጥ እንደገቡ የሚያስብ ካለ በደንብ ተሸውዷል። ሁለቱም ሃይሎች የህዉሃትን ብሎም የትግራይ ህዝብ ጥቅም ይነካል ብለው በገመቱት ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ አቋም አላቸው። ከዚህ አንፃር በቅድሚያ ሊነሳ የሚችለው በቀድሞ በትግራይ አስተዳደር ስር ያልነበሩና ዛሬ የተካለሉት ወልቃይትን የመሳሰሉ ቦታዎች ናቸው። የጦር አዛዦቹም ሆነ የህዉሃት ታጋይ ባለስልጣናት መጀመሪያ ሰሞን የወልቃይትና ተመሳሳይ ቦታዎች ፈጽሞ አንዳይነሱ፤ የሚዲያ ትኩረት እንዳያገኙ አድርገው ነበር። በጽሑፎቻቸውም ሆነ በመግለጫዎቻቸው በየትኛውም ቦታ ከመግለጥ ተቆጥበው ነበር። የቅማንትን ጉዳይ አጉልቶ የገለጠው “ጆቤ” ወልቃይት ላይ ሲደርስ የብዕሩ ቀለም በሚያስፎግር ሁኔታ አልቆበት ነበር። በኦሮሚያ ጥያቄዎች ላይ በምናቡ ከፈጠራቸው የኦሮሞ ልጆች ጋር ማውራቱን ሊነግረን የፈለገው ጄነራል አበበ ጠገዴና ጠለምት ፀለምት(ጨለማ) ሆነውበት ግድግዳ ተስታኮና ተንፏቆ ሲያልፋቸው ተመልክተናል።

ሁኔታዎች እየገፋ ሲመጡና የትግሉ ማዕከሉ “ወልቃይት” መሆኑ ሲረጋገጥ እየተንፏቀቁም ቢሆን የወልቃይትን አጀንዳ ማንሳት ጀመሩ። ለምን ከዚህ በፊት ልታነሡት አልሞከራችሁም ሲባሉ “ይሔ ትልቅ ጉዳይ አይደለም። መደረግም አልነበረበትም” የሚል ምላሽ ሰጡ። ቁምነገሩ እዚህ ጋር ነው። ለእነ ጄነራል ፃድቃን የቅማንት ጉዳይ ትልቅ እንደሆነ አድርገው ሊያገኑት ሲሞክሩ የማያቋርጥ የህዝብ ደም እየፈሰሰበት ያለውን ወልቃይት ንቀው እንደተውት ሊያሳዩ ሞከሩ። እነዚህ ሰዎች ይህን ምላሽ ሲሠጡ ወልቃይት “የትግል ማዕከል” እና “የኢፍትሃዊነት ማሳያ” መሆኑን ጠፍቷቸው አይደለም። ልክ አቶ መለስ በኢትዮ- ኤርትራ ጦርነት ወቅት ካድሬዎች “ለምን ባድመን ለመሰለ ቁራሽ መሬት የ10ሺዎች ደም ይፈሳል?” ብለን ሥንጠይቀው እጁን እየጠበጠበ “ባድመ የትግላችን ማዕከል የሆነችው የኢፍትሐዊነት ማሳያ ስለሆነች ነው” በማለት የንዴት ምላሽ ሰጥቷል። በመሆኑም ባድመ የኤርትራ መንግስት በሃይል ስለወሰዳት መጀመሪያ ወደቀድሞው ቦታዋ ትመለስና ህጋዊ ውሳኔ ይሰጥባት እንደተባለ ሁሉ የወልቃይትም ተመሳሳይ ነው። ወልቃይት “ኢፍትሃዊነት ማሳያ” ስለሆነች መጀመሪያ ወደቀድሞው ታሪካዊ ባለቤቷ ትመለስና ሌሎች የህዝብ ጥያቄዎች ቂም በቀል በማይፈጥሩና የጋራ ድል (Win_Win) በሚያረጋግጡ መልኩ ይፈቱ ማለት የአባት ነው። ይገባልም። ይህ ካልሆነ ግን ምንአልባት ከባድመው ባልተናነሰ በ100ሺዎች የሚጠጋ ህይወት የሚወድቅበትና ደም መቃባቱ የሚያባራ ሊሆን ይችላል።

በመቶ ሺዎች ሊገደሉ ይችላሉ የሚለውም ተራ ማስፈራራት አይደለም። ህዉሃት በተለይም የአማራ ተወላጆች ላይ የቋጠረው የቂም ቋጠሮ ከዚህ በላይ ሊገድል እንደሚችል ፍንጭ የሚሰጥ ነው። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር አሰፋ አቢዩ ከሳምንታት በፊት በሰጠው መግለጫ “99 ፐርሰንት ንፁህ ናቸው። እርምጃ የምንወስደው በተቀሩት ላይ ነው” በማለት ይፋ አድርጓል። አሁን ባለው የአማራ ክልል ንቅናቄ ከ5 ሚሊዮን የአማራ ተወላጆች በቀጥተኛ እየተሳተፉ እንደሆነ ዝቅተኛ ግምት ቢወሰድ እንኳን በኮሚሽነር አሰፋ ስሌት መሠረት ከ50 ሺህ በላይ ሠዎች እርምጃ ይወሰድባቸዋል። ህዝባዊ ማዕበሉ እየሰፋ ሲሄድ በአስቸኳይ የስርአት ለውጥ ካልመጣ እርምጃ የሚወሰድበት የአማራ ተወላጅ ሁለትና ሶስት እጥፍ ይሆናል። ስለዚህም፣ ለህዉሃት “የትግል ማዕከል” (centrifugal force) የሆኑትን ቦታዎች አሳልፎ መስጠት መቃብሩን በጥልቀት የመቆፈር ያህል ስለሚመለከተው በጅምላ ከመግደል የሚመለስ አይሆንም።

በእኔ እምነት ኢትዮጵያ ውስጥ የተቀጣጠለው ህዝባዊ ማዕበል ከህዉሃት ህልውና አንጻር በርካታ ዋልታዎች (Multi- Polar) ያሉት ቢሆንም፣ የዋልታዎቹ ምሰሶ ወልቃይት (Wolqayit Factor) ተደርጎ የሚወሰድ ነው። የኦሮሚያ፣ ጋምቤላ፣ ኮንሶ የተነሱት እምቢተኝነቶች ትላልቅ ዋልታዎች ቢሆኑም ህዉሃት ልቦና ገዝቶ በህይወት መቆየት ከፈለገ ወደ ምሶሶነት ሳያድጉ በተራዘመ ሂደት ሊያዳፍናቸው ይችላል። ለምሳሌ ህዉሃት ኤርትራ ላይ የሚያስበው (Eritrian-Factor፡ ኤርትራ በጦርነት ማሸነፍና አስመራ ላይ አሻንጉሊት መንግስት መመስረት) ከተሳካና ህዉሃት ኢትዮጵያን መምራት ከተነሳው የኦሮሚያን ጥያቄ እስከ ጫፍ በመውሰድ ምላሽ ሊሰጥበት ይችላል። ይህም በኦሮሞ ጉዳይ የተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎችንና አክቲቪስቶችን የመከፋፈል እድሉ ሰፊ መሆኑ አይቀርም። ህዉሃት እስከ ጫፍ የሚወስደውን ፍላጎት ለመቀበል አዳዲስ ሃይሎች (Emerging Powers) የሚፈልቁበት ሁኔታ ይፈጠራል። በመሆኑም ህዉሃት በሚቀደው ሀገር የማፍረስ ቦይ የሚፈሱ ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ ሰዎች ይኖራሉ። ከሰሞኑ የድል አጥቢያ አርበኛ ሆነው ብቅ ብቅ ማለታቸው አይቀርም። በጅምር ላይ ያለውን የትብብር መንፈስም ውሃ ሊቸልሱበት ይሞክራሉ።

 

ወደተነሳንበት ስንመለስ ሁለቱ የህዉሃት የቀድሞ ጦር አዛዦች በተለይም ሌ/ጄነራል ፃድቃን ወልቃይትና ሌሎች “የኢፍትሐዊነት ማሳያ” ቦታዎችና “የትግል ማዕከሎች” በተመለከተ ያስቀመጡት ምላሽ ህዝባዊ እምቢተኝነቱን የበለጠ ነዳጅ የሚጨምር ነው። ጄነራል ፃድቃን መጀመሪያ አካባቢ ባቀረባቸው ጽሁፎች በብልጣብልጥነት ሊያልፈው ቢፈልግም ቦታዎች ይበልጥ “የትግሉ ማዕከሎች” መሆናቸውን በህዝባዊ ማዕበሉ ሲመለከት ከድርቅና በተሻገረ አይን አውጣነት ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ እርስ በራስ የተምታታ ምላሽ ሰጠ። ይህ የጦር መኮንኑ ምላሽ የአማራ ህዝብ ትግልና መነቃቃት ከደረሰበት ደረጃ ጋር ፍፁም የማይመጥን ነው። የአሁኑ የአማራ ትግል የደረሰበት ደረጃ ፍልሚያው ተጧጡፎ አድማሱን በመስፋት ቅኝቱ ሙሉ ለሙሉ ተቀይሯል። ከአስር አመት በፊት ሃሰን ዑመር አብደላ በመጣጥፋቸው እንደገለጡት ቅኝትና ምቱ ከተቀየረ እስክታውም መቀየር አለበት። በመሃመድ አህመድ የትዝታ ቅኝትና ምት ጥላሁን ገሠሠን “አንቺን ነው! ሰማሽ ወይ” የሚለው አይደነስም። በ “እምበር ተጋዳላይ” አጨፋፈር ስልት የይሁኔ “ሰከን በል” አይጨፈርም። እንደዚህ ከሆነ በአራዳ ቋንቋ ሽወዳ ይሆናል። አሁን ትግሉ በደረሰበት ደረጃ ደግሞ ውሽልሽል ምክንያት ሸውዶ ማለፍ የሚችልበት ወቅት ላይ አይደለንም። አለበለዚያም እውነት መድፈር ካልተቻለና የሚያስፈራ ከሆነ (ኮንስቲትወንሲያቸውን እንደሚያጡ ይገባኛል) ምላሽ አለመስጠት ይቻል ነበር። ፃድቃን ሊጠቀምበት የፈለገው “የሽወዳ ፖለቲካ” ህዝባዊ እምቢተኝነቱን አቀጣጥሎ መስዋዕትነቱን ከመጨመሩ ባሻገር በሌሎች ያቀረባቸው የመፍትሄ ሃሳቦችም ላይ በጥርጣሬ እንዲታይ ያደረገ ነው።

ለማንኛውም ሌ/ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳይ “የትግሉ ማዕከል” በሆነው ወልቃይት ዙሪያ ለአዲስ አድማሱ ጋዜጣ የሰጠውን መግለጫ በመመልከት ፍርዱን እንስጥ። አዲስ አድማስ ጋዜጣ “በሰሜን ጎንደር አካባቢ ያለው ተቃውሞ በተለይ ከ “ወልቃይት አማራነት” ጋር የተያያዘ ነው። የወልቃይት የማንነት ጥያቄ ጉዳይ በምን አግባብ ነው መፈታት ያለበት?” ለሚለው ጥያቄ የሚከተለውን ምላሽ ሰጥቷል።

“እኔ የወልቃይት ጉዳይ ለአንዳንድ ፖለቲካዊ አላማዎች ሽፋን ነው ብዬ ነው የማምነው። እንዴት ነው የሚፈታው ላልከው እኔ የሚታየኝ ህገ- መንግስቱን መሠረት አድርጎ ነው። በመጀመሪያ ደረጃ ይሔ ትልቅ ጉዳይ መደረግ አልነበረበትም። ህዉሃትና ብአኤን ተመካክረው መፍታት የሚችሉበት ደረጃ ላይ መድረስ ነበረባቸው።…. በህጋዊ መንገድ ስንሄድም ህገ-መንግስቱን መሰረት አድርጎ መፍታት ያስፈልጋል ነገር ግን ክልሎች በሚወሰኑበት ወቅት ከፍተኛ የፖለቲካ ውሳኔ ሰጪ አካል ውስጥ ነበርኩ። በወቅቱ ቋንቋና የህዝብ አሰፋፈርን መሰረት አድርገን እንወሰን በሚል ነው የወሰነው። በዚህ መሰረት ደግሞ የተወሰነው ተወስኗል።”

አዲስ አድማስ ጋዜጣ ቀጥሎ የጠየቀው “በወቅቱ ወልቃይት እንዴት ነው ወደ ትግራይ የተላከው?” በማለት ነበር። ሌ/ጄነራሉ እንዲህ በማለት አስገራሚ፣ አሳዛኝና እርስ በራሱ የሚደባደብ ምላሽ ሰጠ።

“አሁን እየጠየከኝ ያለኸው መረጃ ነው። ይሄን መረጃ አሁን አላስታውሰውም። እንደዚህ  ሆኖ ነበር ብዬ ለማለት አልችልም። የተጠቀምንበት አቅጣጫ ግን የፌደራሊዝሙን መነሻ ነው። የህዝቦች ቋንቋና ባህልን መነሻ አድርገን ነው የከለከልነው። እኔ እስከማውቀው ድረስ እዚያ አካባቢ ያለው አብዛኛው ህዝብ ትግርኛ ተናጋሪ ነው። ባህሉ የትግራይ ነው። በትግራይ ውስጥ ሊካተት የሚችል ህዝብ ነው። የሆነውም በዚህ አግባብ ነው።”

በመሆኑም እነዚህ የህዉሃት ጦር ጄነራሎች “ህዉሃት አደጋ ላይ መውደቁን ሲያዩ ሊታደጉት መጡ” የሚለውን አባባል ለጊዜው እንተወውና የጎደላቸውን ነገር በጨዋ ቋንቋ እንንገራቸው። በእኔ በኩል  የጦር ጀነራሎቹ ወደፊት መምጣት ቢያንስ በአራት መሰረታዊ ጉዳዮች እደግፈዋለው።

አንደኛው ያልተገለጠ ማንኛውም አስተሳሰብ ስለማይታወቅ መገለጥ አለበት የሚል የፀና እምነት አለኝ። የሉቃስ ወንጌል (መዕራፍ 6 ቁጥር 45) በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፍ ይናገራል።….. ክፉ ሰውም ከልቡ ክፉ መዝገብ ክፉ ውን ያወጣል። መልካም ሰውም ከመልካም መዝገብ መልካም ያወጣል” አንዲል አንደበታቸውና ብዕራቸው የተፋው ቁምነገር ከየትኛው ልብ እንደመነጨ ማወቅ የሚጠቅም እንጂ ጉዳት የሚያደርስ አይደለም።

ሁለተኛው ምክንያት እነዚህ የህዉሃት የጦር ጄኔራሎች የቀድሞ ድርጅታቸው ምን ያህል ኋላቀር፣ ለለውጥ ዝግጁ ያልሆነ ግትረኛ፣ ፈሪ ድንጉጥ እንደሆነ በቀላሉ መረዳት ይችላሉ የሚል እምነት አለኝ። እንደጠበኩት በጥቂት ቀናት ውስጥ በህዉሃት ስፖንሰርነት የሚንቀሳቀሱት የውጭ ድረ-ገጾቻቸው ዘመቻቸውን በተጠናከረ መንገድ ከፈቱ። የአየር ሃይል አዛዥ የነበረውን አበበ ተ/ሃይማኖት በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የአውሮፕላን ግዥ ላይ ፈፀመ ያሉትን ሌብነት እየጠቀሱ  ወረዱበት። “የፈፀምከውን ሌብነት ዝም ስንልህ የረሳነው መሰለህ እንዴ?” በሚል ማስፈራራቱን ቀጠሉ። ጄኔራል ፃድቃንን ደግሞ “የስልጣን ፍላጎት የቀፈቀፈው ሃሳብ” በማለት አብጠለጠሉት። ይባስ ብለው በኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚና ማዕከላዊ ኮሚቴ ስም ባወጡት ድርጅታዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ህዝብ በሁሉም የህይወት መለኩ (መንፈሳዊንንም ይጨምራል) ከፍተኛ ለውጥ እንዳመጣ፣ ህገ-መንግስታዊ ስርአቱ ጠንካራ መሠረት ላይ እንደተጣለ፣ በዲሞክራሲያዊ ምርጫ (100%) አሽንፈው የመንግስት ስልጣን እንደተቆጣጠሩ፣ ባለሁለት አሀዝ ተከታታይ እድገት አምጥተናል….ወዘተ የሚሉ አስደንጋጭ ቃላትን በመጠቀም የጦር መኮንኖችን ቆሌ ገፈፋ።

ሦስተኛው ምክንያት የህዉሃት የጦር ጄነራሎች የሚያቀነቅኑት ሃሳብ ምን ያህል የአገራችንን ችግሮች በጥልቀት ይዳሳሳል፤ ምን ያህል ተቀባይነት ይኖረዋል፤ ከመንግስትና የለውጥ ሃይሎች ፍላጎት አንፃር የተቃኘ ነወይ፤ የደበቋቸውና ለህዝብ ይፋ ቢደረግ ራሳቸውንም ሆነ የቀድሞ ድርጅታቸውን ተጠያቂ የሚያደርግ ነገር ይገልጡ ይሆን ወይ?….. ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎች ምላሽ ያገኛሉ በሚል ነው። በግሌ የጠበኳትን አግኝቻለሁ። መኮንኖች የስርአቱ ችግር አለ መፍትሄው ስርአታዊ (systemic) መሆን አለበት ብለዋል። እርግጥ መፍትሄው አሁን ባለው የህዉሃት/ኢህአዴግ ህገ-መንግስት ማዕቀፍ ስር መሆን እንዳለበት ያስገነዝባሉ። አሁን ባለው ህገ- መንግስት እንዴት አድርጎ ስርአታዊ ለውጥ ለማምጣት እንደሚቻል እንቆቅልሽ ቢሆንም  እንደ ሃሳብ መነሳቱ የሚያበረታታ ነው። በተለይ ህዉሃት አሁን ከዚያው አቋም ሲነፃፀር ምን ያህል የሰማይና ምድር ልዩነት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ሰሞኑን አቶ በረከት የኤፈርት ኩባንያ ንብረት የሆነው ሬዲዮ ፋና በጠራው ኮንፈረንስ ላይ አይኑን በጨው አጥቦ “18 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን መክረው የተጻፈ ህገ-መንግስት፣ በአለም ላይ ካሉ ጥቂት ምርጥ ህገ- መንግስቶች አንዱ የሆነ” በማለት ዲስኩር ሲያሰማ እንደነበር ለሁሉም ግልጽ ነው። ህገ-መንግስታዊ ፍርድቤት የሌለው፤ ፍርዱን የሚሰጡት እነ አባዱላ፣ ሙክታር አህመድ፣ አባይ ወልዱ፣ ገዱ አንዳርጋቸው…… ወዘተ የሆኑበት ህገ-መንግስት ምርጥነትን ለመናገር በበረከት የአስተሳሰብ ደረጃ ዝቅ ማለት ይጠይቃል።

አራተኛው ምክንያት፡ የህዉሃት የጦር መኮንኖች በአንዳንድ የለውጥ ሃይሎችና በአለም አቀፍ ተቋማትና ሀገሮች ያለው ግንዛቤ በጣም አደገኛ መሆኑ ላይ ነው፡፤ እነዚህ ግለሰቦችና ተቋማት የጦር መኮንኖች የውስጥ አዋቂ አድርገው ስለሚቆጥሩ እንደ ዋነኛ የመፍትሄ አካል አድርገው የሚወስዱበት ሁኔታ በተደጋጋሚ ይታያል። ይህ አረዳድ በጣም አደገኛ ከመሆኑም ባሻገር የተጀመረውን የለውጥ እንቅስቃሴ ወደኋላ የሚመልስበት እድል ሰፊ ነው። የም ዕራብ ሐገሮች በተለይም ሰሜን አሜሪካ (ለምሳሌ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት) በተለያዩ ጊዜያቶች ህዉሃት አደጋ ውስጥ ሲወድቅ እነዚህን የጦር መኮንኖች እንደ አማራጭ የሚያማትሩበት ሁኔታ መኖሩ የሚታወቅ ነው። በምርጫ 97 ማግስት (አቶ በረከት ስምኦን ያጫወተኝ ስለሆነ በከፊል እመኑኝ) የቅንጅት አመራሮች ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መ/ቤት ጋር በሚወያዩ ሰዓት ጄኔራል ፃድቃን ገ/ተንሳይ እንዲያካትቱ ጠይቀዋቸው እንደነበረ በንዴት ውስጥ ሆኖ አውግቶኛል። ይሄ የበረከት አገላለጥ እውነት ይሁን ውሸት ታሪክ የሚገልጠው ቢሆንም ዊክሊክስን ያገላበጠና የአሜሪካ ኤምባሲ ከቀድሞ የህዉሃት አመራሮች ጋር ያደረጉትን ሚስጥራዊ ውይይት ለተመለከተ አሜሪካኖቹ የሚይዙት የተሳሳተ አመለካከት እንደሚኖር መገመት ይቻላል።

 

አንዳንድ የለውጥ ሃይሎች ነን የሚሉና አለም አቀፍ ተቋማትና ሀገራት የጦር መኮንኖቹን እንደዋና መፍትሄ የሚወስዱ ከሆነ በጣም አደገኛ ሁኔታ የሚፈጥርበት የተለያዩ ምክንያቶች አሉ። ከእነዚህ ውስጥ የመጀመሪያው የህዉሃት የጦር መኮንኖች ህዉሃት የኢህአዴግ የፖለቲካ አስኳል መሆኑን ሌሎች የኢትዮጵያ ማህበረሰቦችና የውጭ ሃይሎች እንዲያውቁ አይፈልጉም። ጄኔራሎቹ በጠመንጃ፣ በደህንነት፣ በኢኮኖሚና ፖለቲካ የበላይነት የአገሩ ባለቤት የሆነውን የትግራይ ነፃ አውጪ (ህዉሃት) ወደ ጎን ትተው የህይወት እስትንፋስ የሌለውን ኢህአዴግ እንደ መፍትሄ አመንጪና ተጠያቂ አድርገው ያቀርባሉ። ለስሙ ቦታውን የያዙትንና አንዳችም ስልጣን የሌላቸውን ከህዉሃት ውጪ ያሉ ባለስልጣናትን ከፍ ከፍ በማድረግ የተለየ ምስል ለመፍጠር ጥረት ያደርጋሉ። በተለይም የአየር ሃይል አዛዥ የነበረው ጄኔራል አበበ ተ/ሃይማኖት በሙት መንፈስ የሚመራውን ሃይለማርያም ደሳለኝ ብዕሩን ባነሳ ቁጥር ሲያንቆለጳጵስና ሲያሞካሽ ማየት የተለመደ ሆኗል። “ይድረስ ለክቡር አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝየጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ” የሚል ርዕስ በመጠቀም “ለሰራዊቱ ግንባታ የተዘጋጀው መጽሀፍ አግዱልኝ!” በማለት ተማፅኖ ሲያቀርብ ይስተዋላል። ጀቤ ይሄን የሚያደርገው የሃይለማሪያምን “የህዉሃት ትሮይ ፈረስነት” አጥቶት አይደለም። ኢህአዴግ የሚባለው አደረጃጀት ለህዉሃት ጭምብልነት የተፈጠረ መሆኑን ዛሬም የሚመራበት መርሆ በጫካ የተቀረፀና ከዘመኑ ጋር የማይሄድ፤ ሸረሪት የሚሯሯጥበትና ያደረበት መሆኑን ጠንቅቀው ያውቃሉ።

ከጄኔራል ፃድቃን አስተያየት ሳልወጣ አድናቆቴን መግለጽ የምፈልግበት አንድ አረፍተ ነገር አለ። ጄኔራሉ በሌሎች የህዉሃት ታጋዮች ባልተለመደ መልኩ አሁን ያለውን ሁኔታ ሲገመግሙ “የትግራይ ህዝብ በተለይም በከተሞች አካባቢ በሌሎች ማህበረሰቦች የመገለል ሁኔታ አጋጥሞታል። መተማመኛውንም የስልጣን የበላይነት አስጠብቆ ማቆየትና በመከላከያና ሌሎች የፀጥታ ሃይሎች ተከልሎ መኖር”እንደሆነ ገልጧል። ይሄንን ግምገማ ሙሉ በሙሉ የምቀበለው ነው። ለረጅም ጊዜያቶች ይሄ ችግር እየመጣ እንደሆነ ደጋግመን ስንለፈልፍ በህዉሃት ጎራ ያሉ ሰዎች “ዘረኞች” የሚል ታፔላ ተለጥፎልን ነበር። ዛሬ የጦር መኮንኑ በግላጭ ሲያወጣው በህዉሃት መንደር የተፈጠረ ብዙም መንጫጫት አይታይም። ታዲያ! ጄኔራል ፃድቃን በዚህ ጉዳይ ላይ ይሄን ያህል ርቀት መጓዝ ከቻለ ከጥያቄው ጋር አብረው ለሚነሱት ሌሎች ጥያቄዎች ምላሽ ቢሰጥበት እኛንም ከስድብና ውርጅብኝ ያድነናል። ጥያቄው የትግራይ ህዝብ በተለይ በከተሞች ውስጥ በሌላው ማህበረሰብ እየተገለለ መሄዱ እውነት ሆኖ ሲያበቃ፤ የመገለሉ መንስ ኤና መሰረታዊ ምክንያት ምንድነው? መገለሉስ ከመቼ ጀምሮ የተፈጠረ ነው? ተጠያቂው ማነው?…. ወዘተ የሚሉ ናቸው። ይህንን ቁልፍ ጉዳይ መመለስ ከተቻለ ወደ ቁልፍ መፍትሄው የምንሄድበት መንገድ አልጋ በአልግስ ይሆናል።

ከዚህኛው ክፍል ከመውጣቴ በፊት ሁለቱን የህዉሃት የጦር ጄኔራሎችም ሆነ እነሱን ተከትለው ሃሳባቸውን በሰፊው ተቀብለው ያራመዱ የአገር ውስጥ ሚዲያዎች የቀጣይ እጣፈንታ ምን ሊሆን ይችላል የሚለውን የራስ ግምት አስቀምጬ መሄድ እፈልጋለሁ። ከልምድ ማየት እንደሚቻለው ህዉሃት በአንድ መሰረታዊ ጉዳይ ላይ አቋም ወስዶ መግለጫ እስኪያወጣ ድረስ የቀድሞ አባላቱንም ሆነ በግል ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ የሚንቀሳቀሱ (ሸገር 02) ድርጅቶች ትንሽ ለቀቅ ያለ ሃሳብ የሚያራምዱበት በር ገርበብ ይደረግላቸዋል። የዛን ሰሞን አፋችንን ይዘን በመገረም “በሸገር ካፌ” ላይ ወይዘሮ መዓዛ ብሩና ጓድ አብዱ የጄኔራል ፃድቃንን “የስርአት ለውጥ” አስተሳሰብ ተገቢ እንደሆነ በአድናቆት ሲነግሩን ነበር። እርግጥ የደርግ ዘመን ጥያቄና መልስ ላይ “አብዮታዊ” ማብራሪያ ሲሰጥ የምናውቀው ጓድ አብዱ በእያንዳንዱ ንግግሩ ሟቹ መለስ ዜናዊን ሲያንቆለጳጵስ መደመጥ ብዙዎችን አስገርሟል። በጣት ቆጠራ አልፈው ካልሆነ በስተቀር ጓድ አብዱ ከሰባት ጊዜ በላይ ባደርገው የሟች ጥሪ በስላሴ 24 ሰዓት ቁጭ ብለው መቃብር የሚጠብቁ የህዉሃት ዋርድያዎችን ሳያስበረግግ አይቀርም።

ወደ ገደለው ጉዳያችን ስንመለስ የህዉሃት የቀድሞ ጄኔራሎችም ሆነ እንደ ሸገር ያሉት የሚዲያ ተቋማት ህዉሃት/ኢህአዴግ መግለጫ ካወጣ በኋላ ቀስ በቀስ ወደ ኋላ መንሸራተታቸው የግድ ይሆናል። ያለ አንዳች ጥርጥር ጄኔራሎቹ ወደ አፎታቸው ይገባሉ። ሸገርና ተመሳሳይ ሚዲያዎች ደግሞ ወደ ሰገባቸው። ይህን ማድረግ ካልቻሉ “የአበራሽን ጠባሳ ያየ በእሳት አይጫወትም” የሚለው ብሂል ወደተግባር ተገልብጦ ለመመልከት ሩቅ አይሆንም። ለነገሩ ጆቤና ጓድ አብዶ በአክሮባት የሚታሙ ስላልሆነ ካናዳው ለማምለጥ እንደ አቦሸማኔ መሮጣቸው ሳይታለም የተፈታ ነው።

የትግራይ ኤሊቶች፣ የህዉሃት የቀድሞ የጦር ጄኔራሎችም ሆነ የቀድሞ ታጋይ ባላስልጣናት ከህዉሃት በፍጥነት ተፋተው ለአዲስ የስርአት ለውጥ ዝግጁ የማይሆኑባቸው ሌሎች ተጨማሪ መሰረታዊ ምክንያቶች አሏቸው። ከዚህ ውስጥ የቅድሚያ መስመር የምትይዘው ኤርትራ ናት (Eriteria-Factor)። ህዉሃት ከኢርትራ ጋር የገባበት ጦርነት ፍፃሜ የረጅም ጊዜ የመጠባበቂያ ህልሙን ያጨለመ ነው። ለሁሉም ግልጽ እንደሆነው ከጦርነቱ በፊት ከኤርትራ መንግስት ጋር ለአመታት የተካሄደው ድርድርም ሆነ የጦርነት ውሳኔ የተወሰነው በህውሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ ነው። ወደ ጦርነት ከተገባም በኋላ የመሪነቱን ሚና የጨበጡት ህዉሃቶች ናቸው። በጦርነቱ ምክንያት የአገሪቱ ካዝና በተራገፈና ሙጥጥ ባለ ሰዓት መንግስት ከሶስት ቢሊዮን ብር ያላነሰ የተበደረው ከህዉሃት የኢኮኖሚ ኢምፓወ ከሆነው ኤፈርት (ትእምት) ነበር። ለጦርነቱ የሚሆነውን የጦር መሳሪያ (ታንክ፣ ሮኬት፣ ሚሳየል፣ የውጊያ አውሮፕላኖች……) በየአህጉራቱ የተሽከረከሩ የሚገዙት የህዉሃት አመራሮችና የጦር አዛዦች ናቸው።

(በነገራችን ላይ በአውሮፕላን ግዢ ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ ከነበራቸው የጦር አዛዦች ግንባር ቀደሙን የሚይዘው የቀድሞ አየር ሃይል አዛዥ የነበረው ሜ/ጄኔራል አበበ ተ/ሃይማኖት ነው። አበበ የክፍፍሉ መጀመሪያ ወቅት እንቡር እንቡር ቢልም የአንጃዎቹ መጨረሻ ኩምሽሽ አድርጎታል። “አይተነው ጊዜ ወደሚያደላው” አይነት ባህሪ ያለው አበበ ገልብጦ የመለስን ቡድን ይቅርታ ቢጠይቅም የመለስን የቃሪያ ጥፊ ከማግኘት አልታቀበም። ከአዛዥነቱ በንፋስ ፍጥነት ተባረረ። ከዛ በኋላ ጆቦ በሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ከኪሱ በማውጣት አሜሪካን ሀገር ተማረ። በትምህርቱም “የአሰብ ኢትዮጵያዊነት” ተገለጠለት። መገለጡ ቀልብ ይስባልና በኢትዮጵያ አየር ሃይል ላይ በተነው። ጆቤ! ዛሬ በወር 150ሺህ ብር የሚከራይ ቪላ አለው። ያውም በአዱገነት እምብርት! ለ100 አመት ይዞ ቢቆይና ከደሞዙ ሰባራ ሳንቲም ባያወጣ አሁን ያለውን ሀብት ሩብ አይኖረውም። እርግጥ ከርቀት እንደሰማነው ባለቤቱ ብቸኛዋ ሴት ጄኔራል ሆናለች።)

 

እዚህ ላይ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ውጤት ለህዉሃት የበላይነት መምጣትና የትግራይ ተጠቃሚነት ዋስትና የፈጠረው አደጋ ለህዉሃት መሰንጠቅ መሰረታዊ ምክንያት ቢሆንም ሌሎች ተጨማሪ ምክንያቶች አሉት። እነዚህ አደጋዎች ከህዉሃት አፈጣጠር፣ የዘረጋው ስርአት ባህሪና ውስጠ- ድርጅት ሁኔታ ጋር የተያያዘ ነው። ህውሃት የበላይነቱን ያረጋገጠባት ኢትዮጵያ ካልቀጠለችና የአገር መበተን ካጋጠመ “የትግራይ ሪፐብሊክ” ነፃ ሀገር ፈጥሮ መኖር እንደ መጨረሻ ግብ ያስቀመጠ ቢሆንም ከኤርትራ ጋር የገባበት ቁርሾና ደም መፋሰስ ይህን ፍላጎቱን ከሞላ ጎደል ዝግ አድርጎታል። Eriteria-Factor የተባለው አንዱ ገፅታ ይሄ ነው። የጎንደር፣ አፋር፣ ወሎ ህዝብ ከታች ኤርትራ ከላይ ሆነው ትግራይን ሳንድዊች የሚያደርጉበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ከዚህ በኋላ “የትግራይ ሪፐብሊክ” ከህልም የዘለለ አይሆንም። ትግራይን ገንጥለን በሰላም እንኖራለን የሚባል ህልም ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣……ወዘተ ወደ ትግራይ የተከለሉ ሰአትና የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በተነሳ ሰአት ወደ መቃብር ወርዷል።

የኢትዮ- ኤርትራ ጦርነት አጨራረስ በአንድ በኩል ነፃ ሀገር ለመመስረት ህልም የነበረችውን የህዉሃት አመራሮች ወሽመጥ የቆረጠ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ኢትዮጵያዊነቱን አጥብቆ ለሚፈልገው የትግራይ ህዝብ ትልቅ ብስራት ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው። በአጭሩ ኢትዮጵያን ወዳድ ለሆነው የትግራይ ህዝብ የጦርነቱ አጨራረስ በመጥፎ ሁኔታ ውስጥ የሚፈጠር ጥሩ አጋጣሚ ነው። Blessing in disguise!!

 

የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት አጨራረስ ህዉሃትን ለሁለት ሰንጥቋል የሚባልበት መሰረታዊ ምክንያት ይሄ ነው። የስዬ አብርሃ ቡድን የኢትዮጵያን ህዝብ ሀብትና ደም መከታ አድርጎ ኤርትራ በመደምሰስ አሻንጉሊት መንግስት ለመመስረት ሲያስብ ሌሎች አላማዎችን ለማሳካትም ጭምር ነበር። ህዳጣኑ ህዉሃት ከትግራይ ውጭ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ መግዛት ካቃተውና ህዝባዊ ማዕበሉ ካናወጠው ያለ ኤርትራ ስጋት “ነፃ የትግራይ ሪፐብሊክ” መመስረት ይችላል። የስዬ ቡድን ኤርትራ ላይ ለራሱ ተጠሪ የሆነ አሻንጉሊት መንግስት መመስረት አለመቻሉ በክፉ ጊዜ መጠጊያ የምትሆነውን “ሪፐብሊክ ትግራይ” የመመስረት ራዕይ ተጨናገፈበት። በተለይ በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ ህዝብ ልጆቹን በመገብሩ ቁጭት ላይ የወደቀ መሆኑና ከዚህ በኋላ ጋሻነቱ ባከተመበት ሁኔታ ከኤርትራ ጋር ጦርነት መግጠም ማለት የህዉሃት ፍፃሜ መሆኑ አይቀርም። በሌላ በኩል ጓድ መለስ በስልጣን ለመቆየት ካለው ጥማት በመነሳት ጦርነቱ ሊገፋበት አለመቻሉ እዛው ሳለ የትግራይን ነፃ መንግስት ህልም ባጭሩ የቀጨ ሆኗል። ይህ በመሆኑ ምክንያት በህዉሃት/ኤህአዴግ ህገ-መንግስት ውስጥ የሰፈረው አንቀጽ 39 ከህዉሃትና ትግራይ ህዝብ አኳያ ከወረቀት አንበሳነት የዘለለ አይሆንም። የህዉሃት አፈጣጠር መነሻ የሆነው “የትግራይ ነፃ ሪፐብሊክ” መመስረት እውን ሊሆን የሚችለው ሁለት መሰረታዊ ጉዳዮች ሲሟሉ ብቻ ነው። አንደኛውወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት….. የመሳሰሉ መሬቶችን ለባለቤታቸው ሲመልሱ ይሆናል። ሁለተኛው ኤርትራ ላይ (Eriteria-Factor) ዳግም ጦርነት በመክፈትና ኤርትራን ወደ ዳግም ሱማሊያ መውሰድ፤ ከተቻለም ለህዉሃት ተጠሪ የሆነ አሻንጉሊት መንግስት በመመስረት በተራዘመ ጊዜ በኮንፌደሬሽን መዋሃድ። የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምትና ሌሎች ቀድሞ በትግራይ ክልል ያልነበሩ ቦታዎች ወደ ቀድሞ ቦታቸው ይመለሳል የሚለው ጥያቄ “በህዉሃት መቃብር” ላይ ብቻ የሚፈፀም ነው። ለዚህም ነው ከየትኛውም የኢትዮጵያ ቦታዎች በበለጠ ሁኔታ እነዚህ አካባቢዎች “የትግሉ  ማዕከል” ናቸው የተባለበት ምክንያት። ኤርትራን በጦር ገጥሞ ለህዉሃት ተገዢ የሆነ አሻንጉሊት መንግስት በአስመራ እናቋቁማለን የሚለውም ፍላጎት ያስቀና የደቀቀ ተደርጎ ባይወሰድም ወደ ዜሮ የቀረበ እድል (Probability) ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው።

 

እርግጥ ሌሎች ህዉሃትን ለሁለት የሰነጠቁ እንጭፍጫፊ ምክንያቶች እዚህ ላይ ሊጨመሩ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩ እሙን ነው። የህዉሃት የፍጥረቱ የመጨረሻ ግብ ከመኮላሸቱ ጎ ለጎን የዘረጋው ስርአት ባህሪና የውስጠ- ድርጅቱ ሁኔታ ለመሰነጣጠቁ ምክንያት ነው። ህውሃት የዘረጋው ስርአት የፓርቲውን የበላይነትና የትግራይን የተለየ ተጠቃሚነት ዝርፊያ (ሙስና) አንዱ መለያ ባህሪው ነው። መንግስት እንደመሆኑ መጠን ወረራና ዝርፊያው “መንግስታዊ” መሆኑ አይቀርም። “መንግስታዊ ሌብነት”…. “መንግስታዊ ዝርፊያ”…. “መንግስታዊ ሙስና”…. “መንግስታዊ ውንብድና!”…. በመሆኑም የህዉሃት አንዱ መሰረታዊ መለያ ባህሪ በአዋጅ፣ በህግ፣ በመመሪያ የሚፈፅም የቡድን ዝርፊያ (“መንግስታዊ ሙስና”) ነው። ህዉሃት ገና ከጠዋቱ ቁልፍ ቁልፍ የሆኑ የመንግስትና ድርጅታዊ የስልጣን ቦታዎችን በቁጥጥር ስር ያዋለው በዚህ ምክንያት ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ውጭ ጉዳይ፣ መከላከያ፣ ደህንነት፣ ፖሊስ፣ ሚዲያ፣ የድርጅት ቢሮ፣ የክልሎች ሞግዚት በመሆን አይናቸውን በጨው ያጠቡት ለዚህ ነው።

ይህም ሆኖ የህዉሃት ስርአት በትግራይ ህዝብና ልሂቃን ዘንድ ያለው አረዳድ ከሌላው አካባቢ ጋር ተመሳሳይ አይደለም። አሁን ባለው ነባራዊ እውነታ ከትግራይ ህዝብ የወጡት ህዉሓቶች በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ፈላጭ ቆራጭ በሆኑበት፤ ገዳዩ አሳሪው ገራፊውና መርማሪው እነሱ በሆኑበት፤ የመንግስት ስልጣንን በመጠቀም ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም በገነቡበት፤ በትግራይ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅና ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እልፍ አእላፍ ፋብሪካና የኢኮኖሚ አውታሮች በተገነቡበት፤ በጠብታ ኢኮኖሚ መልኩ በትግራይ ክልል የተገነቡት፤ መሰረተ ልማቶችና ማህበራዊ ፍትህ ማምጫ ተቋማት….. ወዘተ በፍጥነት ወደ ህዝባዊ እምቢተኝነቱ ሊቀላቀላቸው አይችልም። ራሳችንን ማምሸት ካልፈለግን በስተቀር የትግራይ ህዝብ በህዉሃት አገዛዝና አፈና ተማሮ ሊሆን ይችላል እንጂ “አዲስ ስርአት” ለመቀበል ዝግጁነቱ አይታይም። የህዉሃት አገዛዝ በፓርቲ መዋቅሩ አማካኝነት የሚፈጥረው ጭቆና፣ የዘመድ አዝማድ አድሎአዊ አሰራር፣ ኋላቀርነት፣ “አህያ ቢራገጥ” የሚመስል አይነት ቂም በቀል፣… አሰልቺ ስብሰባዎች እና መዋጮ….. ወዘተ የትግራይን ህዝብ ሊያስመረምረው ይዝል ይሆናል እንጂ ለስር-ነቀል ለውጥ የተዘጋጀ አይደለም። ግፋ ቢል ከአጭር ጊዜ አኳያ “ላም እሳት ወለደች” ከሚለው ብሂል የሚርቅ አይደለም። ይህ የብዙሃኑ የትግራይ ተወላጅ ፍላጎት አድርገን ልንወስደው የምንችል ነው።

 

ኦሮሞ ዴ. ግንባር፣ አርበኞች ግንቦት 7፣ የአፋር ህዝብ ፓርቲና የሲዳማ ህዝብ ዴ. ንቅናቄ የትግራይ ነጻ አውጪን መንግስት ለማፋለም የፊታችን እሁድ የጋራ ንቅናቄያቸውን ይፋ ሊያደርጉ ነው

 

ethiopian-people-unity

(ዘ-ሐበሻ) በሌንጮ ለታ እና በምክትላቸው ዲማ ነገዎ የሚመራው የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግምባር፣ በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የሚመራው አርበኞች ግንቦት 7፣ በዶ/ር ኮንቴ ሙሳ የሚመራው የአፋር ህዝብ ፓርቲና አቶ በቀለ ዋዩ የሚመራው የሲዳማ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ የትግራይ ነጻ አውጪውን መንግስት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ገንድሰው ለመጣል የሚያስችል የጋራ ንቅናቄ እንደመሰረቱና ይህንንም የፊታችን እሁድ ኦክቶበር 30, 2016 ይፋ እንደሚያደርጉ ለዘ-ሐበሻ የተላከው መረጃ አመለከተ::

በውስጣቸው አንጋፋ ታጋዮችን የያዙት እነዚሁ አራት ድርጅቶች የኢትዮጵያን ህዝብ “ተባባብሩ ወይም ተሰባበሩ” የሚለውን ጥሪ ተቀብለው የፊታችን እሁድ ይፋ የሚያደርጉት የጋራ ንቅናቄ ስም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ንቅናቄ እንደሚሰኝ የደረሰን መረጃ ጠቁሟል::

የፊታችን እሁድ ኦክቶበር 30/2016 የአራቱ ድርጅቶች መሪዎች በዋሽንግተን ዲሲ የፊርማ ስነ-ስርአት እንደሚደረግ የታወቀ ሲሆን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከአስመራ ተነስተው አሜሪካ መግባታቸውን እንዲሁም አቶ ሌንጮ ለታ፣ ዲማ ነገዎ፣ ዶ/ር ኩንቴ ሙሳ አሜሪካ መግባታቸው ለዘ-ሐበሻ መረጃ ደርሷታል::

የፊታችን እሁድ በሚደረገው የፊርማ ስርነ ስርዓት ላይም ሕዝባዊ ስብሰባ እንደሚኖር ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለክታል::

ያስፈራል፤ ግን ኢትዮጵያ አትፈርስም! | ከፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም

 

mesfin

ይቺ ኢትዮጵያ የምትባል አገር ስንት የመከራ ወንዞችን ተሻግራለች! ገና ስንት ትሻገራለች! ስንት የግፍ ተራራዎችን አቋርጣለች! ገና ስንት ታቋርጣለች! ስንት የበደል ሰይፎችንና ጦሮችን አምክናለች! ገና ስንት ታመክናለች! ስንት የውጭ ኃይሎችን አሳፍራለች! ገና ስንቱን ታሳፍራለች! ስንት አምባገ- ነኖችን እያለቀሰች ቀብራለች! ገና ስንቱን ትቀብራለች! ጭቆና ከኢትዮጵያውያን ደም ሙልጭ ብሎ ወጥቶ በነፃነት፣ በእኩልነት፣ በዳኝነት በጠራ ደም እስቲተካ ድረስ “ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ዘርግታ” ትጸልያለች! እግዚአብሔርም ቃል ኪዳን አለበት ይሰማታል! የኃያላን ኃያል ኢትዮጵያ እንድትፈርስ አይፈቅድም!

የኢትዮጵያን መፈራረስ የሚመኙ ግለሰቦችም መንግሥቶችም ሞልተዋል፤ ኢትዮጵያ እንድትፈራርስ የሚመኙ ጭንጋፍ ልጆችም አሏት፤ ማኅጸንዋ እየደማ እየረገማቸው ሰላምና እንቅልፍ አጥተው አብጠው ይፈነዳሉ፤ የኢትዮጵያን መፈራረስ የሚመኙ መንግሥቶች ሁሉ ከዚህ በፊት ቀድመው ፈራርሰዋል፤ ወደፊትም ይፈራርሳሉ።

የአገራቸው ፍቅር፣ የእርስበርሳቸው ዝምድና፣ የተራራውና የሸለቆው፣ የሜዳውና የገደሉ፣ የበረሀውና የለምለሙ፣ የዝናቡና የወንዙ፣ የዓየሩና የነፋሱ፣ የበዓላቱና የድግሱ፣ ያለውን አብሮ መቋደሱ፣ ተዝካሩ፣ ሙታዓመቱ ለሞቱ፣ መላእክቱ፣ ቅዱሳቱ፣ ሰማዕታቱ፣ እየተሸከሙ ያደረሱት ጸሎቱ፣ ለምዕተ-ዓመታት የተከማቸው እምነቱ፣ ሃይማኖቱ፣ በዚህ ሁሉ የተገነባው ኅብረቱ እንዴት ይፈርሳል! ማን ችሎ ያፈርሰዋል! አፍራሾች ቀድመው ይፈርሳሉ!

አንዳንዶች ቢጨነግፉም፣ አንዳንዶች ቢክዱም፣ አንዳንዶች ሆዳም ቢሆኑም፣ አንዳንዶች ቢወላውሉም፣ ኢትዮጵያ ልጆች አሏት፣ አሁንም የሚሞቱላት፣ ያልበሏት፣ የሚሳሱላት፤ ያልሸሿት፤ አፈሯን የሙጢኝ ብለው አፈርሽ እንሁን የሚሏት፣ ደሀነትም ሆነ ጭቆና ካንቺ አይለዩንም የሚሏት፤ ኢትዮጵያ ዛሬም ልጆች አሏት ስትፈርስ ቆመው የማያዩ፣ ሲያማት ነፍሳቸውን ዘልቆ የሚያማቸው፣ ሳልፈርስ አትፈርስም ነው ቃል ኪዳናቸው!

ቱርክና ግብጽ መጥተው ሄደዋል፤ ፖርቱጋል መጥቶ ሄዷል፤ እንግሊዝ መጥቶ ሄዷል፤ ኢጣልያ መጥቶ ሄዷል፤ ጠላቶች እየመጡ በመጡበት ተሸኝተዋል፤ ወዳጆች በጨዋነት ተስተናግደው ተዋኅደዋል፤ ቤተ ሙሴ፣ ቤተ ክርስቲያን፣ ቤተ እስልምና ኢትዮጵያዊ ሆነዋል፤ ዛሬ እንግዳ አይደሉም፤ ዛሬ ባዕድ አይደሉም፤ ኢትዮጵያ በፍቅር ለመጣ ፍቅር ነች፤ ምቹ ነች፤ በጠብ ለመጣ እሾህ ነች፤ ትዋጋለች።

ኢትዮጵያ፣ ነቢዩ ኢሳይያስ ለአንቺ የተናገረው ይመስለኛል፤ ‹‹ብርሃንሽ መጥቶአልና፣ የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻልና ተነሺ፤ አብሪ፤ እነሆ ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማም አሕዛብን ይሸፍናል፤ ነገር ግን በአንቺ ላይ እግዚአብሔር ይወጣል፤ ክብሩም በአንቺ ላይ ይታያል፤ አሕዛብም ወደብርሃንሽ፣ ነገሥታትም ወደመውጫሽ ጸዳል ይመጣሉ። ዓይኖችሽን አንስተሽ በዙሪያሽ ተመልከቺ፤ እነዚህ ሁሉ ተሰብስበው ወደአንቺ ይመጣሉ፤ ወንዶች ልጆችሽ ከሩቅ ይመጣሉ፤ ሴቶች ልጆችሽንም በጫንቃ ላይ ይሸከሙአቸዋል፤ በዚያን ጊዜ የባሕሩ በረከት ወደአንቺ ስለሚመለስ፣ የአሕዛብም ብልጥግና ወደአንቺ ስለሚመጣ አይተሽ ደስ ይልሻል፤ ልብሽም ይደነቃል፤ ይሰፋማል፤ የግመሎች ብዛት የምድያምና የጌፌር ግመሎች ይሸፍኑሻል፤ ሁሉ ከሳባ ይመጣሉ፤ ወርቅንና ዕጣንን ያመጣሉ፤ የእግዚአብሔርንም ምስጋና ያወራሉ፤ የቄዳር መንጎች ሁሉ ወደአንቺ ይሰበሰባሉ፣ የነባዮትም አውራ በጎች ያገለግሉሻል፤ እኔን ደስ ሊያሰኙ በመሠዊያዬ ላይ ይወጣሉ፤ የክብሬንም ቤት አከብራለሁ።›› (60፡1-7)

ኢትዮጵያ ትወድቅ ይሆናል፤ ግን ያለጥርጥር ትነሣለች፤ በፊትም ወድቃ ተነሥታለችና፤ ኢትዮጵያ ትሰነጠቅ ይሆናል፤ ግን ያለጥርጥር ትገጥማለች፤ በፊትም ተሰንጥቃ ገጥማለችና፤ ለኢትዮጵያ በጎ የማይመኙላት የአየሉ ቢመስሉም የንስሐ ጊዜ ስትሰጣቸው ነው፤ ኢትዮጵያ ዕብሪተኞችንም ትሕትና ታስተምራቸዋለች፤ ዕብሪተኞች ከነዕብሪታቸው በራሳቸው እሳት ቀልጠው እስቲያልቁ ኢትዮጵያ ትእግስትዋ አያልቅም፤ ኢትዮጵያ ትእግስት ነችና።

በበጎ መንፈስ እስከተመራን ድረስ፣ ፍርሃትንና አለመተማመንን፣ ጥላቻን፣ ጠብንና ድብድብን፣ ሊዘሩብን ከሚፈልጉ ርኩሳን መናፍስት ከራቅን ኢትዮጵያችን አትፈርስም፣ የደፈረሰውም ቶሎ ይጠራል።

ሰበር ዜና . . .  በሊቦ ከምከም ወረዳ የተገደሉ የወያኔ ወታደሮች ብዛት ከ100 በላይ ሆኗል፤

Amhara - satenaw 2በሊቦ ከምከም ወረዳ ሊቦ፣ ማርታዲዮስና አመኖ በሚባሉ ቀበሌዎች ያሉ ዐማሮችን ትጥቅ ለማስፈታትና በጎበዝ አለቆች ላይ እርምጃ ለመውሰድ ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ የተንቀሳቀሰው የወያኔ ጦር ሙሉ በሙሉ መደምሰሱን ኦፕሬሽኑን ሲመሩ የነበሩ የጎበዝ አለቆች አስታውቀዋል፡፡
 በወረዳው አመኖ በሚባለው ቀበሌ አቶ አድነው መርሀግብር የተባለን የአካባቢ የጎበዝ አለቃ ለመየዝ ሙከራ ያደረገው የወያኔ ጦር ከፍተኛ ዕልቂት ደርሶበታል ተብሏል፡፡ አቶ አድነው በጀግንነት የከበቧቸውን ከዐሥር ያላነሱ ወታደሮች አብዛኛዎቹን ገድለው እንደተሰዉ ሰምተናል፡፡ በዚህ የተናደደው የወያኔ ጦር የአቶ አድነውን ሦስት ሙክቶች አርዶ መብላቱን የታወቀ ሲሆን በጎበዝ አለቆች እርብርብ አንድም ወታደር በሕይወት ሳይወጣ መቅረቱን ለማወቅ ችለናል፡፡
 ሪፖርቱን እንዳቀረቡልን የጎበዝ አለቆች ከሆነ በአመኖ እና በሊቦ ቀበሌዎች ያልተነሱ የወያኔ ወታደሮች አስከሬን እስካሁን መኖሩን ነው፡፡ ከገበሬዎች በኩል ሁለት ሰዎች መሰዋታቸውንም ለማወቅ ችለናል፡፡ ተጨማሪ ሁለት ኦራል ጦር ወደ ሊቦ ቀበሌ መውጣቱንም አክለው ገልጸውልናል፡፡
 ይህ በዚህ እንዳለ በዓለፋና ጣቁሳ ወረዳዎች በተለይም በሻውራና የደልጊ ከተሞች ከ60 በላይ ወጣቶች ጥቅምት 16 ቀን 2009 ዓ.ም. መታሰራቸው ታውቋል፡፡ የጎበዝ አለቆች በከተማ በመቀመጥ እጃቸውን አጣጥፈው ለወያኔ እስር የሚደረጉ ወጣቶች ወደ ማጥቃት እንቅስቃሴ መግባት እንዳለባቸው መክረዋል፡፡
 የዐማራ ተጋድሎ ያሸንፋል//
Muluken Tesfaw

በኦሮሞ ስብሰባ የአማራ እስክስታ (ዳኛቸው ቢያድግልኝ)

ዳኛቸው ቢያድግልኝ
biyadegelegne@hotmail.com

“…. ወደዱ እንዋደድ አፍቅሩ እንፋቀር
ድግግም ላይኖረው አንዴ ብቻ ሊኖር
በዩ በዩ እያለ የሚነግረኝ ልቤ
መስክሪ ዘምሪ የሚለኝ አሳቤ
አንድነት ትብብር ፍቅር ነው ቋንቋዬ
ከቶ አይሰለቸኝም አረ እንደምን ብዬ…”

ዛሬ የደረስንበት ለመድረስ ብዙ የተጓዝን ቢሆንም ገና እጅግ ብዙ መሄድ የሚያሻን መሆኑን መገንዘብም ይኖርብናል። በዚህ ጎዳና ላይ አንድነትና ፍቅርን የሰበኩና ኢትዮጵያዊነትን ከፍ አድርገው የዘመሩ ከግራና ቀኝ ወከባና የደቦ ጥላቻ ቁም ስቅል ያሳያቸው እንደነበር እናውቃለን። ቀላሉ ነገር ጥልቅና ውስብስብ ሆኖብን ግራ በተጋባ አመለካከት መመካከር ሲገባን መካረርን በመረጡልን ልሂቃን እርስበርሳችን እንድንፈራራና አልፈንም እንድንጠፋፋ ተገፍተን ነበር ።

ኢትዮጵያውያን ግን አለም ከመሰልጠኑ በፊት አብሮነትን መረዳዳትን ከዘርና ጎሳ ባለፈ በፍቅር ስንሰለት ተሳስረው ተጋብተውና አንድ ሆነው መኖርን ያስተማሩ መሆናቸውን ዘንግተን ጠላት በሰፋልን የዘር ከረጢት እንድንገባና የሁዋልዮሽ እንድንሄድ ተገደን ቆይተናል። የዚህ መርዝ ተጎጂው በአብዛኛው ፊደል ቆጥረናል ፖለቲካ ገብቶናል የሚለው የህብረተሰብ ክፍል ነበር/ነው። የዚህ ጽሁፍ መነሻ ወዳጄ እመለከተው ዘንድ የጠቆመኝ የሀኒሻ ሰለሞን የዘፈን ክሊፕ ነበር። https://www.youtube.com/watch?v=WwhFSp1elrk&sns=fbEthiopian singer, Hanisha Solomon

አዎን አደንቃታለሁ ድልድይም ሰንሰለትም ሆና ሁሉን ለማቀራረብ የሞከረችባቸውን ስራዎቿንም አውቃለሁ።ዜማዎችዋ ልብ የሚመስጡ መልዕክቶችዋም አስፈላጊና ወቅታዊ በመሆናቸው የድምፅ ወይም የሙዚቃ ጥራት የአጀብ ብዛትና የመሳሰሉትን የማይሻ በማንም ልብ ሊቀር የሚችል መሆኑንም አውቃለሁ። ይህ ልዩ የሆነብኝና እጅጉን ያስደሰተኝ ግን የመድረኩ አይነትና የታዳሚዎቹ ሁኔታ ነበር። አዳራሹ የኦሮሞ ልጆችና ወዳጆች የታደሙበት ስብሰባ ይመስላል። የማያቸው አርማዎችም የዚህ ምስክር ናቸው። ቢሆንም ቢሆንም ከልብ የመነጨ በክህሎቱም ግሩም በሆነ መልኩ የኦሮሞ ወንድሞችና እህቶች እስክስታ ሲወርዱ ማየት ይህን ያህል ብርቅ ይሆንብኛል ብዬ አላሰብኩም ነበር። አንድነታችን ከልብ የመነጨ በመንፈስ የተቆራኘ መሆኑን የሚመሰክር ሁኔታን ዛሬ ላይ ሆኖ እንደማየት የሚያስደስት ነገር የለም። ወያኔዎች ወይም አናሳ አስተሳሰብ ይዘው በችጋራምነት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ የሚያራምዱት በልቶ አይጠረቄ የትግሬ ወሮበሎች የቀመሙት የጥፋት መርዝ እንዴት በዚህ መድረክ ላይ እንደረከሰ ማየትን ያህል የሚያስደስት ነገር ከየት ተገኝቶ? ስሜትን ፈንቅሎ ትከሻን የሚያንቀጠቅጥ እስክስታ ምንጩ ውስጣዊ ነውና አንድነትን ፍንትው አድርጎ ያሳየ መድረክ ነበር።

ምናልባት እኒህ መድረኩን የሞሉ ወንድምና እህቶች እንኳንስ እስክስታ መውረድ አማርኛ መስማት ወይም አማራ ማየት እስከመጥላት የደረሰ የፖለቲካ ስሜት ውስጥ ሆነው ከወገናቸው ጋር ተራርቀው ጠላት በፈረቃ እንዲወቃን እድል ለመስጠት የተገደዱ ሊሆኑ ይችላሉ። ዛሬ ግን ሁኔታው ሁሉ ተቀይሮ ወደ አንድ ጎራ መጥተናል። ለዚህ አስተዋጽኦ ላደረጉ እያደረጉም ላሉ እንደ ሀኒሻ ፀጥታውን ሰብረው ሀሜትና ነቀፋውን ችለው አደባባይ ለወጡ ሁሉ ምስጋና ይገባል።

“…. ወደዱ እንዋደድ አፍቅሩ እንፋቀር…. ድግግም ላይኖረው አንዴ ብቻ ሊኖር… አንድነት ትብብር ፍቅር ነው ቋንቋዬ… ስትል እውነትም እንደ ስምዋ ማር የሆነች የፍቅር አምባሳደር እንደሆነች መመስከር ይቻላል። በእለቱ መድረኩን የሞሉትና ለዚህ ውብ ዜማ ሞገስ የሆኑት ወንድም እህቶችም ሊመሰገኑ ይገባል።

ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ነች ነፃነቷን አስከብራ ሳትንበረከክ የቆመች ታላቅ አገር የምንላት ከሆነ ደግሞ የኦሮሞ ደምና አጥንት ያንን ታላቅነት ቸሯታል። ያንን የራሱ የሆነ አገር ቅኝ ተገዝቼ ነው እንጂ አገሬ አይደለም እስከሚልበት ድረስ ያደረሰው ፖለቲካ አሁን ታሪክ ሆኖ ማነው አገሬን የሚነጥቀኝ? ወደሚል እምቢተኝነት መምጣቱ ታላቅ እመርታ ሲሆን ፖለቲከኞቹን ወደዚህ አቅጣጫ መልሶ ያመጣው ሕዝብም የምንኮራበት ነው።

ታሪክ መቦትረፍ፣ ተራራ መስረቅ፣ ባንክ መዝረፍ፣ ፋብሪካ ነቅሎ መሮጥና ለሊቱን ማጋዝ የችጋራሞች ፖለቲካ ነው። አገሬ ነው ከሚልና ሕዝቡ ወገኔ ነው ከሚል የሚጠበቅ ድርጊት አይደለም። ያንን ሁሉ ክፋት እንደሚሰሩ እየታወቀ ሕዝቡ መሀል ተሸሸገው የሚያስተኩሱና የሚያስገድሉት ላይ እንኳን የከፋ የበቀል እርምጃ የማይወስድና እባካችሁ ሰብሰብ በሉ ብሎ የሚለምን ሆደ ሰፊ ሕዝብ ደግሞ ያኮራል። አሽመድምደን ገድለነዋል ያሉት አማራ ከራሱ አልፎ የወገኑ ደም ደሜ ነው ብሎ የተነሳው በጭንቁ ሰዐት ነበር። ዳግም አንድ ላይሆኑ ተለያይተዋል በማለት የዘር ስም ያለበት መታወቂያ በማደል አማራውን ይጨፈጭፋሉ ተብለው የሚጠበቁት ኦሮሞዎች ታሪክን ለታሪክና ለጊዜ ትተና ዛሬን ሀይላችንን ወደ ጠላታችን የትግሬ ፋሺስቶች እናዞራለን ሲሉ መስማት ኢትዮጵያውነት አንዳች ትልቅ ሀይል ያለው የሕዝብ ቁርኝት መሆኑን ያስተምራል። አሮሞና አማራ አንድ ነን ጠላታችን ወያኔ ብቻ ነው ማለታቸው የአስቸኳይ አዋጅ እስኪለፍፉ ድረስና ፍርሃታቸውን ከማይሸሽጉበት ጥግ እነዳደረሳቸው ተመልክተናል። የነሀኒሻና የመሰል አርቲስቶች ስራ ደግሞ እጅ ለእጅ ተያይዘን አንድንሄድ ያበረታታልና ሙሉ ዘፈኑ በጥሩ ሁኔታ ተዘጋጅቶ መቅረብ ቢችል ደግሞ እጅግ ጥሩ ይሆናል። በዚህ አጋጣሚ ሀኒሻንና አዘጋጆቹን ማመስገን እውዳለሁ። ሀኒሻ አንድነትና ፍቅር መስበክ ከቶውኑ አይሰለቸኝም እንዳልሺው እንደ ቃልሽ ይሁን።

ኢትዮጵያ ታፍራና ተከብራ ለዘለዓለም ትኑር

በጎሳ ትግል ወያኔ አይወድቅም፤ ቢወድቅም ውጤቱ አያምርም (ከመሳፍንት ዘፈረንሳይ ለጋሲዮን)

ከመሳፍንት ዘፈረንሳይ ለጋሲዮን
tmesafint@gmail.com

በኦሮሚያ ተቀጣጥሎ ወደተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ለተዛመተው ሰላማዊ የፍትህ ይገባኛል ጥያቄ የግድያና የእስራት ምላሽ እየሰጠ ያለውና በቅርቡም ግለሰቦች፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የእምነት ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙሃንና ዲፕሎማቶች ሳይቀሩ የመብት እንጥፍጣፊ እንዳይኖራቸው “በባርነት አዋጁ” የደነገገው የወያኔ ስርዐት ለሩብ ምዕተ ዓመት ሲሰራ የቆያውንና አሁንም እየሰራ ያለውን ሁሉ ያስተዋለ በሀገራችን የተከሰተውን ስር የሰደደ የፖለቲካ ቀውስ መረዳት አያዳግተውም።The Green, Yellow and Red Ethiopian flag in Gondar

ይህ የጥቂት ሽፍቶች ስርዐት አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ በሚዳክርበትና ሀገራችንን ወደለየለት የጥፋት ጎዳና በፍጥነት እየጋለበ ባለበት በዚህ አሳሳቢ ወቅት ኢትዩዽያችን ከልጆቿ የምትጠብቀው አስተውሎት የተሞላበት እርምጃ ብቻ ነው። ሀላፊነት የሚሰማውና ለሀገር ተቆርቋሪ የሆነ ሁሉ እጅ ለእጅ ተያይዞ በፅናት በገዢው ቡድን ላይ የሚደረገውን ጫና ማጠናከርና ለወደፊቷ ኢትዩዽያ የሚበጀውን በማሰናዳት ስራ ላይ መጠመድ አለበት። በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እየሆነ የምናያውም ይህንኑ ነው።

ይሁን እንጂ ምስኪኑ ኢትዩዽያዊ ሀገሩን ከሰው በላው መንጋጋ ለማላቀቅ ክቡር ህይወቱን እየከፈለና ከወገኑ ጋር ወንድማማችነቱን በደሙ ማህተም እያረጋገጠ ባለበት በዚህ ወቅት ከየአቅጣጫው በመሰማት ላይ ያሉ ጎሳ ተኮር የአደረጃጀትና የትግል ቅስቀሳዎች እጅግ አሳሳቢና አስፈሪ ናቸው። ኢትዩዽያ ውስጥ በወያኔ የግፍ በትር ያልተገረፈ፤ ሰብዐዊ መብቱ ያልተደፈጠጠ፤ ወንድም፣ እህት፣ ወላጅ፣ ዘመድ አልያም ጓደኛው በግፍ ያልታሰረበትና ያልተገደለበት እንዲሁም ሀብት ንብረቱን ያልተዘረፈ የህብረተሰብ ክፍል ፈልጎ ማግኘት ከቶ አይታሰብም። ይህንን ወደር የለሽ ግፍና በደል ጎሳ ተኮር አድርጎ መቀስቀስና ማራገብ ከባድ አደጋ ያጭራል። ይህን ዓይነት ኋላቀር፣ ጠባብ፣ ኃይልን የሚበታትን፣ የጊዜዉን ነባራዊ ሁኔታ ፈፅሞ ያላገናዘበና የሀገራችንን ችግር የማይፈታ የትግል ስልት ገዢው ቡድን ሕዝብን በመጨፍጨፉ እንዲተጋና ስልጣኑንም እንዲያራዝም ይሁንታ ከመስጠት አልፎ የሀገርንና የሕዝብን አንድነትና ደህንነት አደጋ ላይ ሊጥል የሚችል ነው።

ሰፊው ኢትዩዽያዊ የሚያሰማው ጩኸትና የሚያካሂደው ትግል አንዳንድ የፖለቲካ ልሂቃን በሚያራግቧቸው ሸውራራ መልዕክቶች ሊቀለበሱ አይገባም። ጎሳ ጎሳ የምትለውን ጨዋታ ብቻ መጫወት የሚመርጡ ልሂቃን ለሩብ ምዕተ ዓመት በወያኔ ጥላቻንና መለያየትን ሲሰበክ የኖረው ህዝብ ከሚያሳየው የአንድነት መንፈስና ትግል ለመማር ቢሞክሩ መልካም ነበር።

አሁን ላይ ሆነን ሊያሳስበንና ሊያወያየን የሚገባው ጉዳይ የእንጀራ ገመዱ በፍጥነት እያጠረ የሚገኘው ይህ ስርዐት ከተወገደ በኋላ ስለምንረከባት ኢትዩዽያ እጣ ፈንታ እንጂ ተለያይተን ስለምንበታትናት ሀገር መሆን የለበትም። ሀገራችንንና ሕዝቧን ሊመጣ ከሚችለው ጥፋት ለማዳን የጎሳ ተኮሩ አስተሳሰብ በኢትዮጵያዊነት መንፈስና በጋራ ዓላማ መተካት አለበት። በጎሳ አሰላለፍ ወያኔን ታግሎ መጣልና ኢትዩዽያን ከጥፋት ማዳን ፈፅሞ አይቻልም። ይህ ወቅት የተጣመሩትን ኢትዩዽያውያን እጆች ይዘን ሩቅ ለመጓዝ የምናልምበት ነው። ወያኔ የዘመተው በኢትዩዽያውያን ሁሉ ላይ እንደመሆኑ ልንዘምትበት የሚገባው ኢትዩዽያውያን ሆነን ነው። ዘረኛው ስርዐት የተከለብንን የዘረኝነት መርዝ ነቅለን እስካልጣልን ድረስ ይህ አገዛዝ በጭራሽ አይወድቅም፤ ቢወድቅም ውጤቱ አያምርም።

አምላክ ኢትዩጵያችንን ይጠብቅ።

ሰበር ዜና . . .  የህወሃት ሰራዊት ባለ ቀይ መስመር የአርማጭሆ ወረዳዎችን ተቀማ!

50454082በጎንደር ሰሜን ምእራብ ኢትዮጵያ በሱዳን ጠረፍ አዋሳኝ በደቡብ ተከዜ አቅጣጫ ሰሜን ጎንደር ዞን ታች አርማጭሆ የላይኛዉ አርማጭሆን ጨምሮ ተሰማርቶ የነበረዉ የህወሃት ጦር በደረሰበት ተደጋጋሚ ጥቃት ምክንያት የጥቃት ወረዳዎቹን ባጠቃላይ እየተነጠቀ ይገኛል ።

ጀግናዉን የአማራ ገበሬን ትጥቅ ለማስፈታት ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ያደረገዉ ህወሃት በ14/02/2009 ማምሻዉን የተጠናከረ ሐይሉን ቢያሰማራም በለሱ አልቀናዉም! ወደፊት ለማጥቃት የማይመቸዉ የአማራዉ የነጻነት ምድር አርማጭሆ! ጀግናዉ ህዝብ ከነጻነት ሀይሎች ጋር በመተባበር ዙሪያ ገጠም እሳት በህወሃት ሰራዊት ላይ አርከፍክፏል

ሄሊኮፍተሮች ቢያንባርቁ! ዝቅ ብለዉ ለመብረር እንዳይችሉ የነጻነት ሐይሎች ዙ23 እና ሞርተሮች ከተራራዎች ስርቻ እየተስፈነጠሩ የህወሃትን አየር ሐይል መድረሻ ያሳጡት ሲሆን። የጦር መሳሪያ ድምጽ የሰሙ የአካባቢዉ ገበሬዎች ከየአቅጣጫዉ በማጥቃታቸዉ ምክንያት ወደ ሗላ ማፈግፈግ ያልቻለዉን የወያኔ ሐይል አኮላሽተዉታል።

ከፍተኛ መሰዋትነውት በመክፈል ትጥቅ በማቀበልና በመተባበር ድል የቀናቸዉ የነጻነት ሐይሎች ቆላ ድባትን ጨምሮ ዙሪያ ቁልፍ የጥቃት ወረዳዎችን በቁጥጥራቸዉ ስር ማድረጋቸዉን የህወሃት ወታደራዊ አስተዳደር መርዶዉን ዛሬ የተረዳ ሲሆን መልሶ ጥቃት ለመፈጸም የ 25ተኛ እና ሌሎች ተጨማሪ ክፍለ ጦሮች ተዉጣጪ ወታደሮችን እንዲያሰማሩ መመሪያ ወጥቷል።

ህወሃት ወያኔ በአካባቢዉ ላይ በቀሰቀሰዉ ጦርነት የቆሰሉ ወታደሮችን በሄሊኮፍተር በማመላለስ ከመጠመዱ ባሻገር ቁጥራቸዉ 200 የሚጠጉ የጦር አባላቱ የነጻነቱን ትግል ከነሙሉ ትጥቃቸዉ ተቀላቅለዋል።

እጁን ለነጻነት ሐይሎች በፍቃዱ የሰጠ በቅጽል ወዲ ሳንጃ የተባለ አንድ የ24ተኛ ክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራር እንድተናገረዉ

” የምንዋጋዉ አርሶ ካበላን ካሳደገንና ካጎለበተን አባት ገበሬ ጋር ነዉ ጸጉሩ ሸበት ያለ ፊቱን ቅጭም አድርጎ በብርቱ አይኖቹ አሻግሮ የሚመለከት አዛዉንት አባት ላይ ከመተኮስ እጅ መስጠቱና ወደ ህወሃት መዞሩ አዋጪ ሆኖ አግኝቼዋለዉ ” በማለት የገበሬዉን ብቃት አረጋግጧል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !

 

ልዑል አለሜ