በኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ላይ ወያኔያዊ የክተት ዘመቻ (ነፃነት ዘለቀ)

ነፃነት ዘለቀ – አዲስ አበባ

በሁሉም የሀገራችን ግዛቶች ውስጥ በወያኔ ቅልብ ጦር የጭካኔ እርምጃ ሕይወታቸውን ያጡና አሁንም ድረስ እያጡ ያሉ ወገኖቻችን ነፍሳቸውን ፈጣሪ ተቀብሎ ከፃድቃን አጠገብ እንዲያስቀምጥልን መልካም ፈቃዱ ይሁንልን፤ በየማጎሪያ ቤቶች የሚገኙ ወገኖቻችንንም ጽናቱን ይስጥልን፡፡ የመከራችንን ደብዳቤም እንዲቀድልን ሁላችን ተግተን እንጸልይ፡፡ በዘር፣ በጎሣና በሃይማኖት  ሳንከፋፈል በአንድ ላይ ጸንተን ከቆምን የወያኔ ዕድሜ ከአንድ ደቂቃም ያጠረ ነው፡፡ ነገር ግን አንድ እንዳንሆን ወያኔ የሚጥልብን ደንቃራ ቀስፎ ስለያዘን ይህን ሁኔታ በእስካሁኑ አካሄድ መቀየር አልቻልንም፡፡ ስለዚህ በመከባበር መደማመጥ እንደሚኖርብን እንረዳ፡፡ መጪው ጊዜ ብዙ ደም የማይፈስበትና በተቻለ መጠን በትንሽ መስዋዕትነት ታላቅ ሀገራዊ የነፃነት ድል የምንቀዳጅበት የትግል ዘመን እንዲሆንልን እመኛለሁ፡፡  

በቅድሚያ እንደምን ሰነበታችሁ፡፡ እኔ መሰንበት ከተባለ ደህና ሰንብቻለሁ፡፡ የሀገራችን ወቅታዊ ጉዳይ ከምንጊዜውም በላይ እየተንተከተከ ያለ ይመስላል፡፡ እነወያኔዎችም ሰይጣን ይሁን እግዚአብሔር የፈቀደላቸውን ሀገርንና ሕዝብን እንደእባብ የመቀጥቀጥ ሥራ አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ ዛሬ ደግሞ በአዲስ አበባ ታክሲዎች ሥራ አቁመው ሠራተኛውና ጥቃቅኑ ነጋዴ ከማለዳው ጀምሮ እየተቸገረ ነው፤ በእግሩም እየኳተነ ይታያል፡፡ የደኅንነትና የትግሬዎች ታክሲዎች ግን እየሠሩ እንደሆነ በግልጽ ይታያል፡፡ ከሕንጻውና ከንግዱ በተጓዳኝ አብዛኛው የትራንስፖርት መስክ በትግሬዎች በመያዙ ይህ ዐድማ ብዙም ፋይዳ ያለው አይመስልም፡፡ እነሱ ያልያዙትና ያልተቆጣጠሩት ነገር የለም – ዕድሩም፣ ዕቁቡም፣ ሰንበቴውም፣ መረዳጃ ማኅበሩም፣ ምኑም ምናምኑም በነሱው ቁጥጥር ሥር ነው – የጽዳትና ጥበቃ ኃላፊውንና የቆሻሻ ገንዳ ጠባቂውን ሣይቀር ብትመለከት ከአሥር ዘጠኙ ትግሬ ነው፡፡ አሥርን ካነሳሁ አይቀር ከአሥር ሕንፃ ዘጠኙ፣ ከአሥር ሠርግ ዘጠኙ፣ ከአሥር አውቶሞቢሎች ዘጠኙ፣ ከአሥር ሱቆች ዘጠኙ፣ ከአሥር ሱፐርማርኬቶች ዘጠኙ፣ ከአሥር ኢንቬስተሮች ዘጠኙ፣ ከአሥር ኮንዶሚኒዮሞች ዘጠኙ፣ ከአሥር የመንግሥትና የመያድ ባለሥልጣናት ዘጠኙ፣ ከአሥር … ዘጠኙ ሀብት ንብረቱ የወያኔ ትግሬዎች ሀብትና ንብረት ነው – ሰዎቹም እነሱው ናቸው፡፡ በመያድ ለመቀጠር ትግሬ መሆን አለብህ፤ በመንግሥት ለመቀጠር ትግሬ መሆን አለብህ፡፡ በደርግ ዘመን “ምርጥ ምርጡ ለሕጻናት” የሚል (የውሸት) መፈክር በየግድግዳው ይጻፍ እንደነበር አስታውሳለሁ፤ ዛሬ ደግሞ “ምርጥ ምርጡ ለትግሬ ወያኔ “ የሚል በህቡዕ የሚሠራጭ (የእውነት) መፈክር ሀገር ምድሩን ሞልቶት አለ – ዘይገርም ሻሸመኔ ትብስ ኮፈሌ ማለት አሁን ነበር፡፡ ፡ ኢትዮጵያ ከአሥሩ ዘጠኟ — አይ … ዘጠኝ ብቻ? … ከአሥሩ ዘጠኝ ነጥብ ዘጠኟ የወያny ጥገት ላም ናት፡፡ ሌላው በድርቅ እያለቀ ነው፡፡ ወያኔ እየተንደላቀቀና እየተምነሸነሸ ሌloch በጠኔ እየተንጠራወዙ ናቸው – ዕድል ቀንቷቸው ከተገደሉት ውጪ ማለተይ ነው፡፡ ቧይ! ፈጁን እኮ!

በአዲስ አበባ በረንዳ አዳሪውና እሥር ቤቱን የሞላው ማን ነው? ዐማራውና ሌላው ነው፡፡ … በየዝጉብኝ ዊስኪና ቮድካ ሲጨልጥ፣ ጮማ ሲቆርጥ የሚያመሽና የሚያረው ማን ነው? በየጥሩ ት/ቤቶች የሚማሩ ልጆች የነማን ናቸው? በጫት ገረባ ሰክረው በየበረንዳው እጅብ ብለው የሚውሉና የሚያድሩተ ልጆችስ የነማን ናቸው? አሁን ማን ነው እየኖረ ያለው? ማንስ ነው እያጣጣረ ሞትን በመናፈቅ ላይ የሚገኘው? የሀገሪቱን ሀብትና ንብረት በግል ተቆጣጥረው እየተዘማነኑባት ያሉት ወያኔዎች ብቻ ናቸው፡፡ አዲስ አበባንና ዐይ ዐይን ቦታዎቿን ካለ ገልማጭና ቆንጣጭ የተቆጣጠሩት ትግሬዎች ናቸው – ብልጣብልጥ ወያኔ ትግሬዎች፡፡ ጉራጌ ከማርካቶ ተፈናቅላ ትግሬ ተቆጣጥሮታል፡፡ ሌሎችነን በግብርና በኪራይ ፈነቃቅለው ለስደትና ለራስን ማጥፋት ክፍት የሥራ ቦታ አጋልጠው እነሱ የሁሉም አዛዥ ናዛዥ ሆነዋል – ይህን የሰው ልጅ ቅለት እያየሁ ከምኖር በበኩሌና ማን ከለከለህ እንዳትሉኝ እንጂ ሞቴን ብመርጥ ይሻለኛል፡፡ በወያኔ ትግሬዎች ምክንያት የሰው ልጅ ኅሊናዊና ሰብዓዊ ዕድገት እንዳለ ጥያቄ ውስጥ እንደገባ ይሰማኛል፡፡ “እነዚህ ‹ሰዎች› በርግጥም ሰዎች ይሆኑ እንዴ?” እያልኩ ብዙ ጊዜ እጨነቃለሁ፡፡ በአጥንትና ደም አነፍናፊነታቸው ከእንስሳትም በታች ይወርዳሉ፡፡

እኔም ዛሬ ታክሲ አጥቼ በመኪና ነው ወደመሥሪያ ቤቴ የሄድኩት – ማለቴ በልመና መኪና፡፡

ሲያልቅ አያምር ይባላል፡፡ የኛ ይሁን የነሱ ማለቂያ የደረሰ ይመስላል፡፡ በዚህ መልክ የምንጓዝበት ዘመን ማክተሚያው የተቃረበ ለመሆኑ ብዙ ምልክቶች እየታዩ ነው፡፡ አንድ ቄስና አንድ ሼህ ያንጀት ጓደኛሞች ነበሩ አሉ፡፡ ሼሁ “መምሩዋ ለመሆኑ እስቲ በነቢ ይሁንብዎና ሃቂቃውን ይንገሩኝ – ከእስላምና ከዐማራ(ከክርስቲያን ማለታቸው ነው) ማንኛቸው ይጠድቃሉ?” ብለው ቄሱን ይጠይቃሉ አሉ ዱሮ በደጉ ዘመን፡፡ መምሩም መለሱና “ኧረ በእግዝትነይቱ እንዴት ያለ ጥያቄ ጠየቁኝ ሸኽዬ – መቼስ ከሁለት አንድኛቸው እንታናቸውን ሳይበሉ አይቀሩም!” ብለው መለሱ አሉ፡፡  የዚህን ወግ ጭብጣዊ መልእክት  ወደወያኔ አምጡልኝ፡፡ እንጂ ከጽድቅና ኩነኔ አኳያ ብንነጋገር እኔ በበኩሌ ተቋማዊ መዳን እንደሌለ ወይም ቢያንስ ሊኖር እንደማይገባ ማመን ከጀመርኩ ቆይቻለሁ፡፡ የመዳን መንገድ አንዲት ብቻ ስለመሆንዋ ደግሞ ብዙም አላውቅም፡፡ መዳኛውን አንድዬ ብቻ ያውቃል – “ሁሉም የየራሱን ሲያደንቅ እሰማለሁ፣ የኔም ለኔ ዕንቁ ናት እኮራባታለሁ.…” የምትል የቆየች የንዋይ ደበበ ዘፈን አሁን በጆሮየ ውልብ አለችብኝ – በዚህ አጋጣሚ ነፍስ ይማር ንዋይ ደበበና ኃይሌ ገ/ሥላሤና ሠራዊት ፍቅሬና መስፍን በዙና ሙሉጌታ አሥራተ ካሣና ገነት ዘውዴና … ኦ! የክፉ ቀን ምርጥ ምርጥ ዜጎቻችንን ዘርዝሬ አልጨርሳቸውም – አንድዬ ግን የሚሣነው ነገር የለምና እርሱ ይጨርስልኝ፡፡ ወደገደለው ልሂድ እባካችሁ፡፡ ቀልድና መጠጥ ቤት ያጠፋል፡፡

ሰሞኑን ወደ ትግራይ ሄጄ ነበር – ከምር፡፡ ትግራይ ውስጥ ወንድ ልጀ ያለ አይመስልም፡፡ ሁሉም ተነቅሎ ለማያዳግም አጠቃላይ ክተታዊ የወረራ ዘመቻ ወደተቀረችዋ ኢትዮጵያ የተበገሰ ይመስላል፡፡ በተለይ በገጠር ቤቶች – ብዙዎቹ የድንጋይ ቤቶች – ተንሻፈው ተንጋደውና ፈርሰው ካለሰው ብቻቸውን ይታያሉ፡፡ አንዳንዶች ተዘግተዋል፤ አንዳንዶች ክፉኛ ፈራርሰዋል፡፡ ብዙዎቹ የገጠር ከተሞች የተወረሩ ይመስላሉ፤ የሚገርመው ግን ያን ሁሉ በረሃና የድንጋይ ጫካ እያቆራረጠ በየርሻውና በየፈፋው ብቅ እያለ የሚታይ ንጹሕ የመጠጥ ውኃ ቧምቧ አለ፤ ኦ! ትግራይ ታስቀናለች፤ ልጆቿ ክሰዋታል፡፡ ሥልኩ፣ ውኃው፣ መንገዱ፣ ት/ቤቱ፣… ሁሉም ከሞላ ጎደል ተሟልቶ ይታያል – እንደሚባለው አይደለም፤ በተንጣለለው ገደላማ ኹዳድ እንደዘንዶ ተጋድሞ የሚታየውን ወፍራም የውኃ ቧምቧ ስታዩ “ምነው ይህን መሰል ነገር በጎጃምና በጎንደር ገጠሮች ማየት በቻልኩ?” ሳትሉ አትቀሩም እንደኔ በ“ዐማራነት ልክፍት ከተነደፋችሁ”፤ ወይ ወያኔ ለካንስ ይህን ያህል ቀንድ ማነው ዐይን አውጣዎች ኖረዋል? ችግሩ ግን እነዚያ የገጠር ሥፍራዎች ሰው አይኖርባቸውም – ትግሬ ያለውስ አዲስ አበባ ላይ ነው ወንድሞቼ፡፡ ቅናት አይደለም – ከሆነም በመንፈስ ቀናሁ ልበላችሁ፡፡ እንዲህ የሚያኮራ ውድብ ቢኖረኝ ብዬ ከመዓንጣየ – ካንጀተቴ – ቀናሁ፡፡ በፈርሳሙ ብአዴንም ኮራሁ፤ ኧረ በዐማራው በረከት ስምዖንም አምርሬ ቀናሁ! በስድብ ባቦነነኝ በአረምነው መኮንንም ቀናሁ፡፡  በዐማራው አካባቢም ስላለፍኩ ብአዴን ስላልሠራቸው የልማት ንድፎች ክፉኛ ኮራሁ፡፡ ቀንደኛው ድርጅታችን ባልሠራልን ነገር ካልኮራን በምን እንኩራ? ብቻ በየገጠሩ ያሉ ብዙ ትግሬዎች  ተለቃቅመው “ሪፓብሊኳ”ን በመተው ወደምድረ ገነት ወደ “ኢትዮጵያ” ሄደዋል፡፡ ከሞላ ጎደል ሕይወት ያላት የምትመስለው መቀሌ ማለትም መቐለ እንጂ ሌሎቹ ኦና ናቸው፡፡ ምሥጢሩ ታዲያ ወዲህ ነው፡፡…

ዛሬ ለዚህች ማስታወሻ መጻፍ ምክንያት የሆነኝ ነገር አለ፡፡ በመጣሁበት መኪና ውስጥ ሰዎች ሲያወሩ የሰማሁት ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ሕወሓት ያመጣባትን ዳፋ ትግራይ ከፍላ ለመጨረሽ በሺዎች የሚቆጠሩ ዓመታትም አይበቋትም፡፡ ወያኔ ትግራይን በሰው ደም፣ በሰው አጥንት፣ በሰው ላብና ወዝ፣ በሰው ሀብት፣ በሀገር ንብረትና ወደር በሌለው ግፍ አጨቅይቷት  -እንደ እግዚአብሐየር ፈቃድ – ኢንሻአላህ – በጣም በቅርቡ መሰናበቱ ስለማይቀር ወዮ ለትግራይና ሕዝቧ!!! ለማንም ፈርቼ በማላውቀው ሁኔታ ፈራሁላት፡፡ ትዕቢትና ዕብሪት ጥፋትንና ውርደትን ቀድማ ትመጣለችና እነኚህ የዲያብሎስ ሽንቶች ሒሣባቸውን የሚያወራርዱበት ዘመን በፍጥነት ሲመጣ ይታየኛል፡፡ የኛ መጥፎ ሥራ እነሱን እንዳመጣብን ሁሉ የነሱ ግፍና በደል ደግሞ እነሱ ቀርተው ትግራይ ልትሸከመው የማትችለውን የመከራ ዶፍ እንደሚያመጣ የእግዜሩን ትተን ታሪክን ብቻ በማጣቀስ መረዳት ይቻላል፡፡ መተት ይረክሳል፤ ደንቃራ ይከሽፋል፡፡ የላላ ይጠብቃል፤ የጠበቀ ይላላል፡፡ የተራቡ አልቅቶችና መዥገሮች ወፍረውና አብጠው ይፈነዳሉ፡፡ ከብቶችም ያኔ ነፃ ይወጣሉ፡፡ የመዥገሮችና የአልቅቶች ዘመን ሲገባደድ የከብቶችና የደገኛ እንስሳት ዘመን ይብታል፡፡ ያኔን ለማየት ዕድሜና ጤና ብቻ ይስጠን፡፡

ታዲያ ሰው የሚያስፈልገን አሁን ነው፤ ትልቅ ሽማግሌ ትግሬ፣ ትልቅ ሽማግሌ ዐማራ፣ ትልቅ ሽማግሌ ኦሮሞ የሚያስፈልገን አሁንና አሁን ብቻ ነው፡፡ ከደፈረሰ በኋላ ማቄን ጨርቄን ቢሉ ዋጋ ዘይብሉ ከምዝብሃል ኢዩ ሀወይ፡፡ ሦርያንና “ታላቋን” ሶማሊያ ያዬ በእሳት አይጫወትም፡፡ እርግጥ ነው ከተራበ ለጠገበ አዝናለሁ እንዲባል የነዚህ መሬት የጠበበቻቸው ዐይነ ሥውራን ትግሬ ገዢዎቻችን አይተውት ቀርቶ አስበውት የማያውቁት እርዚቅ ውስጥ በታሪካዊ ጠላቶቻችን ሁልአቀፍ ዕርዳታ ታግዘው ሲነከሩበት ጊዜ ቀን የማይገለበጥ መስሏቸው ከሰማይ በታች የማይሠሩት የበደል ዓይነት ጠፋ – በአንድ በኩል እነሱም ያሳዝኑኛል ታዲያ፡፡ ሰው በእርኩስ መንፈስ ካልተሞላ በስተቀር መቼም እነሱ የሚሠሩትን ዘግናኝ ነገር በሰውኛ ተፈጥሮ መሥራት የሚሞከር አይመስለኝም፡፡ ለይቶላቸው ዐበዱ እኮ! ምድራዊ ንዋይና ሥልጣን እስከዚህ ያሳብዳል? እንዴ፣ እንደዚያ እንደፈረንሣዩ አንድ ንጉሥ ‘after me the deluge’ (እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል …) እንዳለው ይሉኝታና ሀፍረት በጭራሽ አጥተው የለየላቸው ጅቦችና ዓሣሞች ሆኑ እኮ፡፡ እኔ እምለው ከዚህኛው ወገን ባይገኝ ወይም ለመስማት ፈቃደኛ ባይኑ ከነሱ በኩል “ኧረ ይ ነገር አያዛልቅም!” ብሎ የሚመክራቸው ሃይ ባይ ምራቅ የዋጠ ሰው እንዴት ይጥፋ? ለነገሩ በምን ጆሮ ይሰማሉና! ጆሯቸው በበቀልና በጥላቻ እንዲሁም በሀብት አራራ ያበደ ፍላታቸውን እንጂ ሌላ ነገር መች ያዳምጥና? …

እንዲህ ሲሉ ሰማሁ አብሬያቸው የመጣሁት ሰዎች፡፡ በ2004 ዓ.ም አካባቢ አዲስ አበባ ውስጥ አንድ አካባቢ ጥቂት ሰዎች የጨረቃ ቤት ይሠራሉ፡፡ ጥቂት ጊዜ ቆይቶ ግን ቀበሌና ክፍለ ከተማው መጥተው ያፈርሱባቸዋል፡፡ ከነዚያ ከፈረሰባቸው ሰዎች ውስጥ ብዙዎቹ ትግሬዎች ነበሩ፡፡ እነዚያ ትግሬዎች ወደ ክፍለ ከተማ ይሄዱና አብዚሎ ቅብዚሎ ይላሉ፡፡ የቀሪዎቹ (ባጋጣሚ ሆኖ ዐማሮች ናቸው) ጩኸት የቁራ ጩኸት ሆኖ ሲቀር እነዚያኞቹ – የመጀመሪያ ደረጃ ዜጎቹ “አይዟችሁ፡፡ …” የለም ይህን ነገር በትግርኛ ልበለው – “አጆሃትኩም አህዋትና! ወዲተጋሩ ኮይንኹምስ ዝትንክፈኩም የለን፡፡ ውፅዔት ቃልሲኩም ስለዝሆነ ንኣሃትኩም ዝከውን ነገር በቅልጡፍ ተመኻኺርና ገለ ነገር ክንግብረልኩምኢና ቃል ንኣቱ… ብትዕግስቲ ክትፀብዩና ይግብኣኩም ድማ … ንኣሃትኩም ዘይኮነ ነገር …” አሉና እነዚያን ዐማሮች አመናጭቀው ካባረሩ በኋላ – እንዲህ ጭምልቅል ያለ ነገር ስናገርና ስጽፍ ተገድጄ የወረድኩት መውረድ እእየታየኝ ራሴን በራሴ እንዴት እንደምጸየፈው አትጠይቁኝ – ለትግሬዎቹ ሌላ መንገድ ፈለጉና አሁን እነዚያ ትግሬዎች ቢጠሯቸው የደነቆሩ ሚሊዮነሮች ሆነዋል – “ሀ” ራስህን አድን ለጫማው በኋላ ይታሰብበታል እንደተባለው ማስታወቂያ ነው ነገሩ፡፡ ከጨረቃ ቤት ባዶ ሕይወት ወደሚሊዮነርነት፡፡ እንደትግሬ ወያኔ ያለ ደደብና ደንቆሮ ቀትረ ቀላል ቡድን በዓለም ታይቶም ሆነ ተሰምቶ አያውቅም፡፡ በነገራችን ላይ እነዚያ ዐማሮችም ከተፈረደባቸው የዘር ማጽዳትና ጭፍጨፋ ማምለጣቸውና ጨረቃ ቤት በማጣት ብቻ መታለፋቸው ትልቅ ነገር ነው፡፡ ዓለመኛ ዳቦ ቅቤ ቀቡኝ ይላል እንዲሉ ሆኖ እነዚያ ምስኪኖች አዲስ አበባ ላይ በመገኘታቸው እንጂ ሌላ ቦታ ቢሆን ጠገባችሁ ተብለው ይረሸኑ ነበር፡፡ እየሆነ ያለው ነገር ሁሉ እኮ እኮ ደም አፍልቶና አንተክትኮ ወደ ጋዝነት የሚለውጥ ነው፡፡

እነፕሮፌሰር መስፍን ግን እንዳይቆጡኝ እፈራለሁ፡፡ እርሳቸው አንዲት አፓርትማ ውስጥ ተወሽቀው የኛን የተራ ዜጎችን እንግልትና የትግሬዎችን የዱባ ጥጋብ ማየት ስላልቻሉ በፍርደ ገምድል ብይናቸው እነሱም እንደኛው አልተጠቀሙም ይላሉ፡፡ ማለቴ እኛ በትግሬ አገዛዝ እንዳልተጠቀምን ሁሉ እነሱም አልተጠቀሙም ባይ ናቸው፡፡ ሰው መቼም መስማትና ማየት የሚፈልገውን ብቻ እሰማለሁና አያለሁ ብሎ ከቆረጠ  ከዚህ ዓይነቱ ሞገደኛና ሸውራራ አመለካከቱ ፈጣሪ ነፃ እንዲያወጣውና እውነቱን እንዲያመላክተው ከመጸለይ በስተቀር ምን ማድግ ይቻላል? ሆ! ትግሬ አልተጠቀመም? ድራማዊ አስቂኝ ዐረፍተ ነገር፡፡

የባዳ ልጆች ጉድ ሠርተውናል፡፡ የተሰባበርነው ሁሉ እንዴትና መቼሰ እንደሚጠገን ሳስበው ይጨንቀኛል፡፡ ኢትዮጵያ የሌሎቹም ያልሆነች ያህል ሌሎች እንዲህ ባይተዋር ሆነው ስታዩ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር እንደጪስ በንና ጠፋች ወይ ትላላችሁ፡፡ በርግጥም ኢትዮጵያ አሁን የለችም፡፡ ሌላው ሁሉ የትግሬ አሽከርና ገረድ ሆኖ ትግሬዎች የጠገቡ ጌቶች ሆነዋል፡፡ ጥጋብን የማያውቅ ሰው ደግሞ አይግጠምህ፡፡ የተሸናፊ አሸናፊ አይግጠምህ፡፡ ከአፍ እስካፍንጫው ማሰብ የማይችል “አሸናፊ ጀግና” አይግጠምህ፡፡ ብሃጺሩ ቀን አይጉደልብህ፡፡ ምን ዓይነት ጉዶች ናቸው በል? መጥኔ ለጤናማ ትግሬዎች! ሀፍረቱን እንዴት ይችሉት ይሆን? የ16 ዓመት ታዳጊ ከትግራይ ገጠር አዲስ አበባ መጥቶ በሣምንት ውስጥ ሚሊዮነር ሲሆን የሚታዘብ ጤናማ ትግሬ በሀፍረት እንደሚሸማቀቅ መቼም ግልጽ ነው፡፡ አይ… እኔ እንኳንስ በግማሽ ብቻ ትግሬ ሆንኩ! ሙሉ በሙሉ ብሆን ኖሮ ነገን በማሰብ ከአሁኑ ነበር አንገቴን ደፍቼ በሰቀቀን የምሞተው፡፡ ውይ ወያኔዎች ሲያሳፍሩ! ሱቅ እንደገባ ሕጻን ዓይነት ሁሉንም ለራሳቸው አፍሰው ሌላውን ባዶ ሲያስቀሩ ስታዩ እነዚህ ሰዎች ምን እንደነካቸው በማሰብ ታዝኑላቸዋላችሁ፡፡ ደግሞም እምብርት የሚባል ነገር አልፈጠረባቸውም፡፡ እንዴ – አንድ ሰው እኮ በልቶ ይጠግባል፤ ጠጥቶ ይረካል፡፡ ሲያመነዥኩና ሲጋቱ መዋል የጤንነት ምልክት አይደለም፡፡ ለከት የሚባል ነገር አለ፡፡ የሁሉም ነገር ዳር ድንበር አለው፡፡ ለፍቅርም ለጥላቻም ወሰን አለው፡፡

መጨረሻቸው ሦስት ክንድ ለሆነው ቦታ እነሱ 50 እና 60 ቦታ ይዘው አይረኩም፡፡ ከአንድ እንጀራ የማያልፍ ሆድ ይዘው በሚሊዮኖችና በቢሊዮን የሚገመት ገንዘብ በደቂቃዎች ውስጥ ሲያገለባብጡ በዚህም አይረኩም፡፡ ከምን ተፈጠሩ? ገድለው የማይረኩ፣ በልተውና ጠጥተው የማይረኩ፣ አሥረውና ደብድበው የማይረኩ፣ በሕይወት ያለን ገድለውም ስለማይረኩ ዐፅምን ሣይቀር ከመቃብር አውጥተው የሚቀጠቅጡና በዚያም ዕርካታን የማያገኙ፣ ህግን መሬት ላይ ጥለው በመደፍጠጥ መጫወቻ እስሚያደርጓት ድረስ ቢዘልቁም በዚያም የማይረኩ፣ ዐማራን ጨፍጭፈው የማይረኩ፣ ቂምን ከ40 ዓመታት በላይ በልባቸው ቋጥረው በመያዝ እየታደሰ በሚሄድ በቀልና ጥላቻ ሀገርንና ሕዝብን በታትነው የማይረኩ፣ድንበርንና መሬትን ለባዕዳን ሸጠው በሚያገኙት ሥፍር ቁጥር የሌለው ገንዘብ የማይጠግቡ፣ ዓለምን በማታለል ወደር ያልተገኘላቸው እነዚህን የሲዖል ትሎች ፈጣሪ ከየት ላከብን? ለመሆኑ እነዚህን መሰል የእሳት ጅራፎች በሺህ ወይ በሁለት ሺህ ዓመታት ስንቴ ይሆን ወደ አንድ ሕዝብ ለቅጣት የሚላኩት? ይህ ዓይነቱስ ቅጣት አመክሮ የለውምን?

እነፕሮፍ አንዴ ስሙኝማ – ለታሪክ ምሥክርነት ትሆኑ ዘንድ መከላከያን፣ ደኅንነትን፣ ውጭ ጉዳይን፣ ፖሊስን፣ ጉምሩክን፣አየር መንገድን፣ አየር ኃይልን፣ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤችን፣ ንግድ ቤቶችን፣የከተማ ቦታዎችን፣ ሕንፃዎችን፣ የትምህርት ተቋማትን፣የንግድ ማዕከላትን፣ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን፣…. ለጥቂት ጊዜ ጎብኙ፡፡ ከዚያ እውነትም ለአካለ ዘረፋ የደረሰ ወጣት ወያኔ ትግራይ ውስጥ እንደሌለ ያኔ ትረዳላችሁ፡፡ መጥኔ ለወደፊቷ ትግራይ! ኹልና ጥዑይ ውልቀሰባት ተጋሩ ህጅ እዩ ብዙህ ማሰብ ዜድልየና፡፡ እዚዮም አሻታት ንኣዲና ከምዘሃሰቡ መሲሎምሲ ከመይ ገይሮም ከምዝቀተልዋ ህጅ እዩ ምህሳብን ምጭናቅን፡፡ ጊዜ ካለፈ በኋላ የፈሰሰ አይታፈስምና በነዚህ ወራዳ የባንዳ ልጆች ምክንያት ትግራይ መከራና ስቃይ ስትዝቅ ይታየኛል – አሁን ትግራይ ያለች የመሰለችው በባንዳዎቹ ልች ጥንካሬ ሣይን በፈጣ ቸርነት ብቻ ነው – ነገር ግን ይህ ትዕይንት እንዳለ እስከመጨረሻው አይቀጥልም – ሁልጊዜ ፋሲካ ደግሞ ኖሮ አያውቅም፡፡ ፈጣሪ ክፉዎቹም ደጋጎቹም ሁሉም ልጆቹ ስለሆኑ ለክፉዎቹም ለደጋጎቹም እኩል ዕድልን እንደሚሰጥ መረዳት ይገባል፡፡

እኔ ግን በኅሊና ሠሌዳየ አሁን የሚታየኝ ክፉ ነገር ሲፈጸም ከማየቴ በፊት አሁኑኑ ብሞት ሞትኩ አልልም – በርግጥም ዐረፍኩ እንጂ፡፡ ሰው ሰውነቱን ለምን ይነጠቃል? ሰው በመግደልና በማሰር፣ በመዋሸትና በመቅጠፍ፣ በመዝረፍና ሁከትን በመፍጠር እንዴት ይደሰታል? አንድ ጭቅላ ሕጻን ዐማራ የሚል ወያኔያዊ ታርጋ ስለለጠፉበት ብቻ ካለምርጫው በተወለደበት ዘውግ ምክንያት ከነሕይወቱ በበደኖ ገደል የሚለቀቀው ገዳዩና አስገዳዩ ስንት ሺህ ዓመት ሊኖሩ ነው? ወደኅሊናችን እንመለስና ራሳችንን እንመርምር – አሁኑኑ!!

በሌላ አቅጣጫ ጅሎችና ነሁላሎች ኢትዮጵያውያን በሌለች ሀገር ሲጨቃጩ መስማት የሚገርም ነው፡፡ ጠላት ባቆመላቸው የጡት ቁራጭ ሀውልት፣ በፈጠራ ተደርሶ ዘወትር በሚነበነብ ስብከት ፣ በጠላት ሠርጎ ገቦች መሠሪ ውትወታ፣ በሆድ አዳሪዎች የኅሊናቢሶች ሸርና ተንኮል… የጋራ ትግሎች እየመከኑ የተናጠል ትግሎችም እየተውተበተቡ እህት ነፃነት ከአድማስ ባሻገር ቆማ በምናብ ስትታይ መታዘብ ኢትዮጵያዊ ሆኖ መፈጠርን እስከወዲያኛው ያስረግማል፡፡ ሥልጣን በሬኮማንዴ ውጪ ሀገር ይሄድ ይመስል መቶና ሁለት መቶ ድርጅት በውጪ ሀገራት መመሥረቱ ደግሞ ጥቅም እንደሌለው ከታወቀ ቆይቷል፡፡ በዚህ የተበላ ዕቁብ የሚጃጃሉ ወገኖች ቁጥርም ቀላል አይደለም፡ አየ ኢትዮጵያ! የዕንቆቅልሽ ሀገር፡፡

Ethiopia: Kickin’ it with Reeyot Invictus and……. By Alemayehu G. Mariam

Reeyot-Eskedar-pix-30

Author’s note: This is Part I in a forthcoming series relating my conversations with Reeyot Alemu and her amazing story in the defense of press freedom in Ethiopia. It is also about conversations with an extraordinary group of young Ethiopians living in Las Vegas who are dedicated to building good governance in a New Ethiopia founded on a strong foundation of democracy, the rule of law, human rights protections and accountability.

How I “met” Reeyot

When Reeyot was arrested and imprisoned by the personal order of the late T-TPLF  capo di tutti capi (boss of all bosses) Meles Zenawi  in June 2011, I was outraged but not surprised. I had no idea who she was; never heard of her name.

Following the 2005 election in Ethiopia, Meles Zenawi ran around like a rabid dog biting every journalist who did not sing him praises. My policy has always been to defend any journalist attacked by Meles Zenawi and his T-TPLF.  That is how I “met” Reeyot.

I became Reeyot’s No. 1 fan and self-appointed spokesperson in the court of international public opinion shortly after Meles Zenawi told his make believe parliament that Reeyot was a world class terrifying terrorist who had planned on attacking “infrastructure, telecommunications, and power lines in the country with the support of an unnamed international terrorist group and Ethiopia’s neighbor, Eritrea.” He said Reeyot is a “messenger” of terrorists, blah, blah, blah…

I laughed at Meles Zenawi’s allegations because I could prove beyond a shadow of doubt that his allegations were not only laughable but also demonstrably false.

At the time Meles made the allegation, his T-TPLF (Thugtatorship of the Tigrean People’s Liberation Front) regime had already destroyed Ethiopia’s telecommunications structure.

It is a historical fact that Emperor Menelik II was the first African leader to introduce the telephone and telegraph on the African continent in 1889, thirteen years after Alexander Graham Bell patented his “apparatus for vocal sounds”.  When anxious clergymen told Menelik the telephone was the “work of Satan” and should be banned, Menelik declined and Ethiopia’s telecommunication infrastructure building began in earnest.  Menelik insisted adoption of modern technology is vital “to enable us to exist as a great nation in the face of the European powers” and to meet our “need for educated people.”

In 2016, 127 years later, Ethiopia has the worst telecommunication infrastructure in the world.

Is it not incredible that, all things being equal, Ethiopia had a much better communications infrastructure in 1899 than in 2016? What a low down, dirty shame!

In 2013, Freedom House reported, “Ethiopia has one of the lowest rates of internet and mobile telephone penetration in the world, as meager infrastructure, a government monopoly over the telecom sector, and obstructive telecom policies…”

In 2014, the Wall Street Journal reported that while farmers in Ethiopia have cell (mobile) phones, “The trouble is, they have to walk several miles to get a good signal.” Ethiopia has the second worst internet service in Africa. Kenya, some 450 miles south of Addis Ababa, in 2012 had the second highest internet speed in Africa after Ghana, according to Freedom House. In 2016, growth in Kenya’s telecommunications sector is described as “nothing short of phenomenal.”.

It is the worst telecommunication system in Africa that Meles Zenwai claimed Reeyot was planning to destroy! Aye, aye, aye! Meles the “visionary”!

Anyway, following Reeyot’s arrest, I made sure I was kept informed on her situation in Meles Zenawi Prison (sometimes referred to as “Kality Prison”).

I am recounting my conversations with Reeyot in this series not to show the heroism of Reeyot and her extraordinary family (God bless her parents for giving us Reeyot and her sister Eskedar), but in the fervent hope that Reeyot’s story of commitment to truth, courage, patriotism, sacrifice, virtuousness, honesty, decency and humanity will inspire all young Ethiopians to stand up for their beliefs.  She has certainly inspired me.

I am also recounting my conversations with Reeyot so the world can see through Reeyot’s eyes the crimes against humanity committed against her and continue to be committed against all political prisoners in Ethiopia. What happened to Reeyot happens to every political prisoner in Ethiopia. Reeyot does not feel she is some  special victim of T-TPLF crimes against humanity. She is just one of many thousands of political prisoners held by the T-TPLF. Her struggle is not for her personal liberty; it is for the liberty of all Ethiopians without regard to ethnicity, religion, language,  region, gender and so on.

It is hard and easy to describe Reeyot.

Reeyot is in many ways a larger than life figure. Meles Zenawi jailed her when she was 31 years old. When I met her in person a few days ago, she was beyond anything I had imagined her to be.

The way Meles Zenawi spoke of her to his make-believe parliament, I was expecting someone fearsome, fire-breathing, frightful and intimidating. I was expecting to meet a terrifying figure. (Maybe “terrifying” is the wrong word to use in this context.)

Reeyot is a young woman in a small frame.

When I first laid eyes on her, the first words I said to her were, “You are Reeyot?! I am not scared of you!” She busted out laughing.

I wasn’t really trying to be funny. I just blurted out the

Taxi Drivers of Addis Ababa on Strike (Zone 9)

 

Taxi strike
Following the announcement of a new decree to execute Regulation Number 208/2010 that the Federal Transport Authority is said to implement on drivers, taxi drivers in the city of Addis Ababa have called for and started a strike that will last for two days. As the news of strike started circulating, Transport Authority announced its plan to postpone the implementation of the decree for three months to ‘create awareness’ in advance.

As witnessed by Zone 9 bloggers in some parts of the city such as Sidest Kilo, Arat Kilo, Piassa, Megenagna, Awutobus Tera, Mexico square and etcetera blue minibus taxis were not seen in their usual terminals. Thus, long queues were seen in the streets while government deployed its public buses. In addition, officials are seen registering plate numbers of taxis that joined the strike in street conjunctions.

Fana Broadcasting Corporate, on its news feed, has interviewed people from the Associations of Taxi Owners where they claimed the strike was called without their consent and urged the drivers to end their strike and start serving the public immediately.

Meanwhile, as reported on social media, drivers out of Addis Ababa has also joined the strike.
For further news feedbacks on the strike, please follow ‪#‎AddisTaxiStrike‬.
Photo curtsy of the regulation and a call for the strike, © Social media

1936331_959968767424949_1311334162337464703_n12805999_959968690758290_8725408933430619695_n

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ህክምና ተከልክሎ እየተሰቃየ ነው

woubshet-taye-new-photo3

(ሳተናው) በዝዋይ ወህኒ ቤት የሚገኘው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በኩላሊት ህመም በመሰቃየት ላይ የሚገኝ ቢሆንም የወህኒ ቤቱ አስተዳደር
ህክምና እንዳያገኝ ማድረጉን ውብሸት ሊጎበኙት ለሄዱ ወዳጆቹ ተናግሯል፡፡
ከአራት ዓመት በፊት የጸረ ሽብር አዋጁ ተጠቅሶበት ለእስር የተዳረገው ውብሸት 14 ዓመት ተፈርዶበት በዝዋይ ወህኒ ቤት የእስር ጊዜውን እያሳለፈ ይገኛል፡፡
በወህኒ ቤቱ ለታሳሪዎች የሚቀርበው የመጠጥ ውሃ ንጽህናው ያልተጠበቀ በመሆኑም ብዛት ያላቸው እስረኞች ለኩላሊት ህመም እንደሚዳረጉ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ውብሸት ወደዝዋይ ከመውረዱ በፊት የኩላሊት ህመም እንደማያውቀው የሚናገሩ የቅርብ ሰዎቹም ህመሙን ከወህኒ ቤቱ ማግኘቱን ይገልጻሉ፡፡
በዝዋይ ወህኒ ቤት ለእስረኞች የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ ለመስጠት የተቋቋመ ክሊኒክ ቢኖርም የክሊኒኩ ሰራተኞች ለሁሉም አይነት በሽታዎች ፓራሲታሞል የሚያዙ በመሆናቸው ለጋዜጠኛው የኩላሊት ህመምም ፓራሲታሞል ማዘዛቸው ታውቋል፡፡
ውብሸት ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ የተሻለ ህክምና እንዲያገኝ በክሊኒኩ ሪፈር ተጽፎለት የነበረ ቢሆንም የወህኒ ቤቱ ኃላፊዎች መኪና የለንም በማለት ለወራት ለስቃይ ዳርገውታል፡፡ውብሸት በመጨረሻ ወደ አዲስ አበባ ቂሊንጦና ቃሊቲ ወህኒ ቤቶች ቢያመራም ወህኒ ቤቶቹ ህክምናውን ሳያገኝ ወደ ዝዋይ እንዲመለስ አድርገውታል፡፡
የቀድሞው የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በዝዋይ የሚገኙትን ጋዜጠኞች ተመስገን ደሳለኝንና ውብሸት ታዬን ለመጎብኘት ወደስፍራው ባመሩበት ወቅት የፓርቲው አመራሮች ተመስገንን ለመጠየቅ ባይፈቀድላቸውም ውብሸትን ማግኘታቸው ታውቋል፡፡
ውብሸት ለቀድሞዎቹ የአንድነት አመራሮች ‹‹በኩላሊት ህመም እየተሰቃየሁ ቢሆንም ህክምና እንዳላገኝ ተደርጊያለሁ›› ማለቱን የፓርቲው የህዝብ ግኑኝነት የነበረው አቶ አስራት አብርሃም በማህበራዊ ድረ ገጹ አስፍሯል፡፡

ኢትዮጵያ ሀገራችን የሰብአዊ መብት ተሟጋች ልጇን አጣች

በሰብአዊ መብት ተሟጋችነታቸው፣ ለሰላምና ለዲሞክራሲ መስፈን ታጋይነታቸው የሚታወቁት

ዶር ማይገነት ሽፈራው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።


Center of womenn
ዶር ማይገነት ሽፈራው ስለ ሰላም የሰበኩ ያስተማሩና የጻፉ ቀንዲል ኢትዮጵያዊ ነበሩ። ድህነትና በሽታ፣ ርሐብና ስደት፣ አምባገነንትና ጦርነት እያለ የኢትዮጵያ ሴቶች መብት መከበር፣ የሰብአዊ መብት መረጋገጥ፣ ዲሞክራሲና ሰላምን ማስፈን አይቻልም በሚል እምነታቸው በጽናት ታግለው ያታገሉ የዘመናችን ጣይቱ ነበሩ። የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ፣ የመናገር የመጻፍ የመሰብሰብ የመደራጀትና በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞን የማሰማት መሠረታዊ መብቶች እውን እንዲሆኑ እንዲሁም ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሰብአዊ መብት መከበር፣ ለሃገራችን ሰላም፣የሃገራችን የፖለቲካ ችግር በዲሞክራሲ፣ በመቻቻልና በሰከነ ውይይት እንዲፈታ፣ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ እድሜያቸውን ሙሉ ታግለው ያታገሉ እናት፣ እህትና ወገን ነበሩ።

ዶር ማይገነት ሽፈራው (Ethiopian Women for peace and development (EWPD) ) እ.ኤ.አ. በ 1991 ዓም ከመሥራቾቹ አንዷ በመሆን ለ21 ዓመታት ያገለገሉ ሲሆን በ2012 ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ሴቶች ጉባኤ ባደረገውም ተከታታይ ስብሰባ የኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ማዕከልን (Center for Rights of Ethiopian Women (CREW) ) ሲመሠረት ሀሳቡን ከመጠንሰስ ጀምሮ በምሥረታው ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካደረጉትና ከመሥራቾቹ አንዷ ናቸው። ከተመሠረተም በኋላ በተደጋጋሚ በመመረጥ ድርጅቱን በብቃት የመሩ የመሪነት ችሎታቸውን በተግባር ያስመሰከሩ ናቸው።

Maygenet
ዶር ማይገነት ሽፈራው

ይህ አዲስ የተወለደው የሴቶች ማዕከል የተነሳበት ዓላማና የሚታገልላቸው ጥያቄዎች የኢትዮጵያ ሴቶች የሰላምና የልማት ድርጅት (EWPD) ለ21 ዓመታት ሲታገሉላቸው ከነበሩት ዓላማዎች ጋር አንድ በመሆናቸው ተመሳሳይ ድርጅት ለየብቻ ሆኖ ኃይልና ጉልበትን ከመከፋፈል በአንድ ላይ ሆኖ ያለውን ጉልበትን አሰባስቦ ጠንክሮ ለውጤት በመሥራት የተሻለና ጠንካራ የሴቶች ድርጅት በመሆን ለኢትዮጵያ ሴቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማህበራዊ ፍትህ፣ ለሰብአዊ መብት መከበር፣ ለዲሞክራሲ መብት መስፈን እየታገሉ የሴቶችን በራስ የመተማመን አቅም ለማጎልበት እጅ ለእጅ ተያይዞ መሥራት የወቅቱ ቁልፍ መፍትሔ መሆኑን በማመን ለ21 ዓመት በጽናት የቆዬውን የኢትዮጵያ ሴቶች የሰላምና የልማት ድርጅት የሠራቸውን ሕዝባዊ ሥራዎችንና ያካበተውን የትግል ልምድ ይዞ ኢትዮጵያ ሀገራችን የሰብአዊ መብት የሚከበርባት፣ የሕግ የበላይነት የሚያብባት፣ ሰላም የሰፈነባትና የሴቶች ስብእናቸው የሚከበርባት አገር እንድትሆን በጋራ ቆሞ ለመሥራት ከኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ማዕከል ጋር አንድ በመሆን ሲዋሃድ ዶር ማይገነት ሽፈራው ውህደቱን እውን እንዲሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታዋል::

ዶር ማይገነት ሽፈራው የኢትዮጵያ ሴቶች ጠንካራ ተቋም እንዲኖራቸውና በሃገራቸው የፖለቲካ፣የኤኮኖሚና የማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲኖራቸው በነበራቸው ከፍተኛ አላማና ምኞት ንቃተ ህሊናቸውን ለማሳደግ የመጀመሪያው እርምጃ ሴቶች ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄዱ እንዲማሩ የሚያበረታቱና የሚያስተምሩ ኃላፊነት የሚሰማቸው አብነታቸው ብዙዎችን የሚያነሳሳ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሴቶችን ለመሪነት ማብቃት ለነገ የማይባል ግዴታችንና ኃላፊነታችን ነው ብለው የሚያምኑ ለዚህም ሳያሰልሱ ያስተማሩ ምርጥ መምህር ነበሩ።

የኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ማእዕከል (CREW) መሪውን በማጣቱ የተሰማውን ከፍተኛ ኃዘን እየገለጸ ዶር ማይገነት በተውሉንን መልካም ሥራዎቻቸውንና በጎ ሀሳባቸው እየተጽናናን  የደከሙበትንና የታገሉለትን አላማና አርማ ቀጣዩ ትውልድ በማንሳት የነገይቱ ኢትዮጵያ  የሃገራችን የፖለቲካ ችግር በዲሞክራሲና በሰከን ውይይት ተፈትቶ የሴቶች መብት የሚሰፍንባት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሰብአዊ መብት የሚከበርበት፣ የመልካም አስተዳደር መሠረት የሚጥልበት እንደሚሆን ጥርጥር  አይኖረንም።

“ዞሮ ዞሮ ከቤት ኖሮ ኖሮ ከመሬት” የማይቀርበት የህይወት ጉዞ ነውና ለዶር ማይገነት የሰላም እረፍትን እንዲሆንላቸው እየጸለይን፤ እንዲሁም ለባለቤታቸው፣ ለልጆቻቸው፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ብርታትና መጽናናትን እንመኛለን።

የኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ማእዕከል (CREW)

FEBURARY 29, 2016

 

የዶ/ር ማይገነት ሽፈራው  የቀብር ስነስርአት ፕሮግራም የሚካሄደው ሰኞ ፌብሩዋሪ 29 2016 ነው፡፡

የቤተክርስትያን ስነስርአት የሚፈዐመው ፡ ከ 10፡00 ኤ.ም -1፡00 ፒ.ኤም

ቦታው፡ ቅዱስ ገብርኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን

አድራሻ2601 Evarts St. N.E Washington DC 20018

የቀብር አገልግሎት የሚከናወነው፡ 2፡00ፒ.ኤም

የቀብር ቦታ አድራሻ፡ 9500 Riggs RD Adelphi, MD, 20783

ከቀብር ስነስርአቱ ፍፃሜ በኋላ የምሳ ፕሮግራም በቅዱስ ገብርኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ተዘጋጅቷል፡፡

ጆሮ አይሰማው የለ! ኢትዮጵያ ቅኝ ተገዝታለች ተባለ!!! – ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

Ethiopia  RAND1908ፋሽስት ጣሊያን 1888ዓ.ም. አድዋ ላይ ድባቅ መትተው ድል በመምታት የደረሰበትን ታላቅ ውርደትና ሽንፈት ለመበቀል አርባ ዓመታት ሙሉ ሲዘጋጅ ስንቅና ትጥቅ ሲያደራጅ ቆይቶ በ1928 ዓ.ም. ላይ ከታንክ (ብረት ለበስ ተሸከርካሪ) እስከ የጦር አውሮፕላን (በረርት) ድረስ በገፍ የታጠቀ ዘመናዊ የጦር ኃይል በማሰለፍ ጥቅም ላይ እንዳይውል የተከለከለ አደገኛ የመርዝ ጭስን ጨምሮ በስፋት በመጠቀም ድል አግኝቶ ኢትዮጵያን ለመውረር ቢችልም እናት አባቶቻችን ከፍተኛ መሥዋዕትነት ከፍለው በወቅቱ የተፈጠረው ዓለማቀፋዊ ሁኔታም ረድቶ ከአምስት ዓመታት በኋላ በ1933ዓ.ም. ከዚህ ወረራ ነጻነታችንን ልንቀዳጅ ችለናል፡፡

ብዙ ጊዜ በብዙኃን መገናኛዎች ስለ አምስት ዓመቱ የጣሊያን ወረራና በአርበኞቻችን ተጋድሎ ነጻነታችን ስለመመለሱ ሲነገር “ነጻነት ከተመለሰ በኋላ፣ ከነጻነት በኋላ” የሚለው አገላለጽ ብዙዎችን ሰዎች በቅኝ ግዛት እንደነበርንና ነጻ የወጣነውም ከቅኝ ግዛት እንደሆነ እንዲያስቡ ሲያደርጋቸው ይስተዋላል፡፡

ለሀገራችን ታሪክ በቂ ዕውቀት ግንዛቤ የሌለው ሰው እንዲህ ቢያስብ ብዙ የሚደንቅ ባልሆነ፡፡ ተምረናል በቂ ግንዛቤ አለን በሚሉ ሰዎች ዘንድ እንዲህ ዓይነት ግንዛቤ መያዙ ነው እንጅ አስገራሚው ነገር፡፡

ዘንድሮ ትዕዛዘዝ ተሰጥቷቸው በሚመስል ሁኔታ (እንደዛ ካልሆነ በስተቀር ነገሩ የሁሉም ቋንቋ ሊሆን እንደማይችል ስለገመትኩ ነው) የወያኔ አባል መሆናቸው በግልጽ የሚታወቁና እንዲሁም የምንጠረጥራቸው ሰዎች ይሄንን ዓመት በተለያየ አጋጣሚና በተለያየ መድረክ አጋጥሞኝ እንደሰማኋቸው ኢትዮጵያ በጣሊያን ቅኝ ተገዝታ እንደነበር በሰፊው ማውራት ይዘዋል፡፡ እንደኔ ሁሉ ሌሎቻቹህንም እንዳጋጠማቹህ እገምታለሁ፡፡

ይሄንን አነጋገር በተመለከተ ከዚህ ሁኔታ በፊት የማስታውሰው ነገር ቢኖር ቆይቷል ከዓመታት በፊት ነው ምን ሆነ መሰላቹህ ከነጋሪተ ወግ (ከሬዲዮ) ጣቢያዎች የአየር ሰዓት ተከራይተው ዝግጅቶቻቸውን ከሚያቀርቡ ዝግጅቶች ስድስት ሻል ሻል ነቃ ነቃ ያሉ ሰዎች ሆነው በሚያዘጋጁትና በሚያቀርቡት ስሙን በማልጠቅሰው ከእሑድ በስተቀር በሁሉም የሳምንቱ ቀናት ዝግጅቶቻቸውን በትጋት በሚያቀርቡ ተወዳጅ ዝግጅት ላይ ያለ ሰው ነው ይህ ሰው ፒ.ኤች.ዲውን (ሊቀ ጥብናውን) እየሠራ ነበር አሁን ይያዝ አይያዝ እንጃ አላወኩም፡፡ ይህ ሰው ነው በአንድ የዓርብ ዝግጅቱ ላይ ከአንድ እንግዳው ጋራ በአምስት ዓመቱ የጣሊያን ወረራ ወቅት ስለነበረው የስፖርት (የፍን፤ ሲነበብ ን ትጠብቃለች) እንቅስቃሴ ሲያወሩ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቡድን ከጣሊያን ቡድን ጋር ተጫውተው ፍትሐዊ ባልሆነ መንገድ ስለመሸነፋቸው በሚያወሩበት ጊዜ ይሄው ሰው ምን ይላል መሰላቹህ “…ለነገሩ በቅኝ ግዛት ስር ሆነህ እነሱን ማሸነፍ ከባድ ነው!” የምትል ቃል ይናገራል፡፡

እኔ በወቅቱ ይህ አነጋገሩ ምን እንዳለ በሚገባ ሳያጤነው ካፍ አምልጦት ተሳስቶ የተናገረው ቃል መስሎኝ ለሌላ ጊዜ ከአቅሉ ጋር ሆኖ እንዲያወራ ለማሳሰብ ፈልጌ ወዲያው በስቱዲዮ (በመከወኛ ክፍል) ስልክ እሱን ለማግኘት በተደጋጋሚ ብደውልም ላገኘው ሳልችል ቀረሁ፡፡

በብዙኃን መገናኛዎቻችን በጣም ከባባድ ስሕተቶች እንደሚፈጸሙ በተለይም የአየር ሰዓት ተከራይተው በሚሠሩት ሳይሆን “የመንግሥት” ጋዜጠኞች የሚባሉት በሚያዘጋጇቸው ዝግጅቶች ሆን ተብሎ የወያኔን ፖለቲካዊ (እምነተ አሥተዳደራዊ) ጥቅም ለማስጠበቅ ሲባል በስፋት እንደሚፈጸም ሁሉም የሚያውቀው ጉዳይ ነው፡፡ አውቀው ስለሚያጠፉም እንዲታረሙ መሞከር ከንቱ መድከም ነው ብዙ ሞክሬ ስላየሁት ነው፡፡ “ታዲያ እነኝህን ለምን እርማት እንዲወስዱ ለማሳሰብ ፈለክ?” ብትሉኝ ምክንያቴ እነዚህኞቹ እንደ “የመንግሥት” ጋዜጠኞች ለአገዛዙ ጥቅም ሲባል እንዲያብሉ፣ እንዲቀጥፉ፣ እንዲያጠፉ፣ ሐሰቱን እውነት እውነቱን ሐሰት፣ የሌለውን ያለ ያልነበረውን የነበረ አድርገው እንዲያወሩ እንደማይገደዱ የራሳቸውን ነጻ ሐሳብ ብቻ አስተናግደው እንደሚወጡ ስለሚያወሩ “ይሄ ከሆነ” በሚል ነው፡፡

እናም ያንን ቀን የዕለቱ ዝግጅታቸው አልቆ እንደወጡ ለዚህ ሰው በግል ስልኩ ደወልኩለት፡፡ ከዚህ ቀደምም በሚያቀርቧቸው ዝግጅቶች ላይ አንዳንድ ነገሮች ሲኖሩ እየደወልኩ አንዳንድ እርማቶችንና አስተያየቶችን ስለምነግራቸው የሆነ ነገር ልነግረው ፈልጌ እንደደወልኩ ገባው መሰለኝ ደጋግሜ ብደውልም ሊያነሣልኝ ሳይችል ቀረ፡፡

ለባልደረባው ደወልኩ፡፡ ከሱ ጋር አወራን፡፡ ለካ ይህ ሰው ያንን ቃል የተናገረው ተሳስቶ ካፉ አምልጦት ሳይሆን አምኖበት የተናገረው ነገር ኖሯል፡፡ ባልደረባው ምን ይለኛል “አዎ አምሳሉ ልክ ነህ ነገር ግን ሀገራችን በቅኝ አገዛዝ ሁኔታ አላለፈችም ማለት ይቻላል?” ሲል መለሶ ጠየቀኝ፡፡ እኔም በፍጹም በፍጹም እንዳላለፈች ፋሽስት ጣሊያን የጭካኔ ድርጊትና ግፍ ፈጸመ ማለት ቅኝ ግዛት ገዛ ማለት እንዳልሆነ፣ የቅኝ ግዛትንና የወረራን ልዩነት፣ የአምስት ዓመቱ ወረራ ወረራ የተባለበትና ቅኝ ግዛት ያልተባለባቸውን ምክንያቶች እየጠቀስኩ አወራንና ተማመንን፡፡ ይሄንኑ ጉዳይም ለባልደረባው እንዲነግረውና እንዲታረም እንዲያደርገውም አደራ ብየው ተለያየን፡፡ ነገር ግን ቀልቤ ሊያርፍልኝ ስላልቻለ እኔው እራሴ ልነግረው በማሰብ ያንን ሰሞን ስልኩን ብቀጠቅጥም ሊያነሣልኝ ሳይችል ቀረ፡፡

አሁን ደግሞ ከስንት ዓመታት በኋላ በዚህ ዓመት ጥቅምት 2008ዓ.ም. ላይ ሌላኛው ባልደረባቸው በአንድ የመጽሐፍ መገምገሚያ መድረክ ላይ “ባይተዋሩ ንጉሥ” በሚል ርእስ የተተረጎመውን የዐፄ ኃይለሥላሴ ወጥ ቤት ሠራተኛና ኃላፊ የነበረ ኸርበርት ፎክ የተባለ አውሮፓዊ መጽሐፍ እንዲሔስ (እንዲሔስ ማለት እንኳን ይከብዳል) የመወያያ ሐሳብ እንዲያቀርብና እኛም ተወያዮችም የየራሳችንን ዕይታ እንድናወራ በተደረገበት መድረክ ላይ ያለ አንዳች መሸማቀቅ ኢትዮጵያ ቅኝ እንደተገዛች አድርጎ አውርቶ ቁጭ አይልም መሰላቹህ!

ቦግ አለብኝ በጣም ተበሳጨሁ እንደምንም ዕድሉ እስኪሰጠኝ ድረስ ታግሸ ቆየሁ፡፡ ዕድሉ ሲሰጠኝ የተሻለ የንባብ ልምድና በሳል ዕይታ ያለው ይመስለኝ እንደነበር፣ ይሄ ሳይሆን በመቅረቱና ይሄንን የተሳሳተ አባባል በመናገሩ ማዘኔን ገልጨ ሀገራችን በፍጹም በፍጹም ቅኝ እንዳልተገዛችና የነበረው ነገር ከወረራ ሁኔታ አልፎ ወደ ቅኝ ግዛት ደረጃ እንዳልተሸጋገረ የመሸጋገር አቅምም እንዳልነበረው ቅኝ ተገዝተናል ሊባል ይችል የነበረው አንድ ሁለት ሦስት ብየ በመጥቀስ እነኝህ ነጥቦች ተሟልተው ቢሆን እንደነበር ጠቅሸ መሳሳቱን ተናገርኩ፡፡

እሱም ምላሽ እንዲሰጥ ዕድሉ ሲሰጠው መሳሳቱን እንደተገነዘበ ገልጾ ስሕተቱ የተፈጠረውም በዚህ ጉዳይ ላይ ጥልቅ ግንዛቤ ስላልነበረው እንደሆነ ተናገረ፡፡ እኔ መስሎኝ የተበረው እዚህ ድምዳሜ ላይ የደረሰው የራሱ ጠንካራ የመከራከሪያ ሐሳቦች ቢኖሩት ነውና እንሟገታለን ብየ ጠብቄ ይሄ ሳይሆን በመቅረቱና ይሄንን በሚያህል ብሔራዊ ጉዳይ ላይ የሀገርንና የሕዝቧን ክብር ሊያዋርድ በሚችል መልኩ ያልሆነ ነገር በግምት ለመናገር በመድፈሩ ይባስኑ አናደደኝ፡፡

አሁን ይንን ጉዳይ እንድጽፍበት ያስገደደኝም ከሱ በኋላ በአዋጅ “በሉ” እንደተባሉ ሁሉ ሲጠየቁ ምን እንደሚመልሱ የማያውቁ ይሄንን ሐሳብ የሚያንጸባርቁ ግለሰቦች በተለያየ ቦታ በገፍ ስላጋጠሙኝና ጉዳዩ አሳሳቢ በመሆኑ ነው፡፡

የአምስት ዓመቱን ፋሽስት ጣሊያን ቆይታ ወረራ እንጅ የቅኝ ግዛት እንዳልነበረ የሚያረጋግጡ ነጥቦች ምን ምን ናቸው?

  1. ሀገሪቱ የራሷ የሆነው መንግሥታዊ አስተዳደር ተወግዶ ጠፍቶ ፈርሶ ተደምስሶ ሀገሪቱ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ለመግዛት በመጣው ኃይል አገዛዝ ወይም አሥተዳደር ቁጥጥር ስር የነበረች ብትሆን ኖሮ፡፡
  2. ሠራዊቱ እንዲሁም ሕዝቡ ሙሉ ለሙሉ እጅ ሰጥቶ ነጻነቱን አሳልፎ ሰጥቶ ባርነትን አምኖ የተቀበለ ቢሆን ኖሮ፡፡
  3. ወራሪው ኃይል ሕዝቡን ሴት ከወንድ ሕፃን ሽማግሌ ሳይል በጅምላና በገፍ ያለምንም ክፍያ በግዳጅ ሥራዎች ላይ ማሠራት ቢችል ኖሮ፡፡
  4. ወራሪው ኃይል ያለ ከልካይ የሀገሪቱን የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ሀብት እንደፈለገ ማጋዝ መበዝበዝ የሚችልበትን ሁኔታ ፈጥሮ ቢሆን ኖሮ፡፡ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

እነኝህ ጉዳዮች ቢፈጸሙ ኖሮ በርግጥም ሀገሪቱ በቅኝ ግዛት ስር ነበረች ማለች ይቻል ነበር፡፡ ማንም እንደሚያውቀው ሁሉ እነኝህ ሁኔታዎች ተፈጻሚ አልሆኑም አልተደረጉም፡፡ ስላልተፈጸሙም ነው ዓለም ሀገራችን ኢትዮጵያን “በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ ነጻ አፍሪካዊት ሀገር” ሲል ዕውቅና ሰጥቶ የሽዎች ዓመታት የነጻነት ታሪክ ያላት ሀገር በመሆኗ የምትታወቀው፡፡

ከአፍሪካ ብቸኛዋ ስል መጥራቴ ብዙዎች በስሕተት እንደሚሉት ላይቤሪያ ነጻ ሀገር ስላልሆነች ነው፡፡ ሀገሪቱን የመሠረቷት ከሰሜን አሜሪካና ከካሪቢያን ሀገራት ከባርነት የተመለሱና ከእነሱ ቢወለዱም በኋላ በአሜሪካ በወጣው ሕግ መሠረት ልጆቻቸው ባሪያ ሳይሆኑ ነጻ ናቸው የተባሉት ልጆቻቸው በቅኝ ገዥነት ነው እንደ እ.ኤ.አ. በ1822ዓ.ም. የመሠረቷት፡፡ ሀገሪቱ በአሜሪካ መንግሥት ጥበቃና ቁጥጥር ስር ነበረች፡፡ ይሄ በመሆኑ አውሮፓውያን ላይቤሪያን የአሜሪካ ይዞታ እንደሆነች በመቀበላቸው በቅኝ በመዳፋቸው እንዳትወድቅ አድርጓታል፡፡ በ1847 ከባርነት ነጻ ከሆኑ ጥቁር ቅኝ ገዥዎች ነጻ ወጣች ተብሎ ነጻነቷ ቢታወጅም እስከ 1980 እ.ኤ.አ. ድረስ ከእነዚህ አናሳ ከባርነት ነጻ ከሆኑ ጥቁር ቅኝ ገዥዎች ቁጥጥር ስር ነጻ አልሆነችም ነበር፡፡ በመሆኑም ላይቤሪያ እንደነጻነቷን ጠብቃ የኖረች ሀገር መቁጠር አይቻልም ማለት ነው፡፡

እናም ከላይ የተጠቀሱት ነጥቦች ባልተፈጸሙበት ሁኔታ ነገራችን በቅኝ ተገዝታለች ማለት በጣም ስሕተት ነው፡፡ እያንዳንዳቸውን ነጥቦች ዕንይ ካልን እርግጥ ነው አዎ የሀገሪቱ መንግሥት በመቀመጫው አዲስ አበባ ላይ አልበረም፡፡ መሪዋና ሌሎች ባለሥልጣናት ለአቤቱታ ወደ አውሮፓ ቢሔዱም በወረራው ምክንያት የሀገሪቱ መንግሥት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ ወደ ጎሬ አዛወረ እንጅ አልፈረሰም አልጠፋም፡፡

ወደ ሁለተኛው ነጥብ ስንሻገር እርግጥ ነው ሠራዊቱ ፈርሶ ነበር፡፡ ይሁን እንጅ ሠራዊቱ በመፍረሱ ምክንያት መደበኛ ጦርነት ማድረግ ባይችልም በየቦታው በጎበዝ አለቃው እየተመራ ኢመደበኛ ውጊያ በማድረግ ለወራሪው ኃይል ይበልጥ አስቸጋሪና አደገኛ ሆኖ የወጣበት ከዚህም የተነሣ ወራሪው በከተሞች ብቻ ለመወሰን የተገደደበት ገጠሩና ሰፊው የሀገራችን ክፍል ግን በአርበኞች ቁጥጥር ስር የነበረበት ሁኔታ ተፈጠረ እንጅ ፋሽስት መላ ሀገሪቱን በቁጥጥሩ ስር እንዲያደርግ አላስቻለው፡፡

ሦስተኛው ነጥብ፡- ፋሽስት ጣሊያን በነበረው ቆይታ ሕዝቡን ሴት ከወንድ ሕፃን ሽማግሌ ሳይል በጅምላና በገፍ ያለምንም ክፍያ በግዳጅ ሥራዎች ላይ ለማሠራት (ለመግዛት) የሚችልበትን ሁኔታና አቅም መፍጠር አልቻለም ነበር፡፡ አንዳንድ ሥራዎችን በሚያሠራበት ጊዜም በደሞዝና በክፍያ ያሠራ ነበር እንጅ በባርነት እንደተያዘ ሕዝብ የኢትዮጵያን ሕዝብ በብላሽ ያለ ክፍያ አስገድዶ እንዲሠራ አላደረገም ነበር፡፡ ሕዝቡም ለዚህ ዝግጁ አልነበረም፡፡ እንኳንና ሕዝቡ አሜን ብሎ ሊገዛለት ቀርቶ ወዶ ገብቶልኛል ብሎ የሚያስባቸው እንኳን በውስጥ አርበኝነት ቁም ስቅሉን ስላሳዩት ሕዝቡ አሜን ብሎ የሚገዛለት አለመሆኑን በመረዳቱና ተስፋ በመቁረጡ ግራዚያኒ ለጌታው ሞሶሎኒ “ከኢትዮጵያዊያን ጭምር ካልሆነም ያለኢትዮጵያዊያን ኢትዮጵያ ያንተ ትሆናለች!” ብሎ እስከመናገር ደርሶ እንደነበር ይታወቃል፡፡

በአራተኛነት ላነሣነው ነጥብ፡- ወራሪው ኃይል በነበረው ቆይታ ያለ ከልካይ የሀገሪቱን የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ሀብት እንደፈለገ ማጋዝ መበዝበዝ አልቻለም ነበር፡፡ በእርግጥ ይሄንን ለማድረግ በማሰብ ወራሪው ኃይል ወደ ወደብ የሚያመሩ አውራ መንገዶችን ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በመነሣት የነበረውን በማሻሻልና ተጨማሪ አዳዲስ መስመሮችንም በብዙ አሳርና መከራ ገንብቶ ነበር፡፡ ይሁንና የቆይታው ጊዜ አጭር ስለነበር መንገዶቹን አጠናቆ ገንብቶ የሀገራችንን አንጡራ ሀብት ወደ ሀገሩ በማጋዝ ላሰበው ዓላማ ማዋል ሳይችል ቀርቷል፡፡

እንኳንና የሀገሪቱን የገጸምድርና የከርሰ ምድር ሀብት ሊቦጠቡጥ ቀርቶ ለቀለቡ ስንዴ ለማምረቻነት ያሰባቸውን ወገራን (የሰሜን ጎንደር ክፍል) እና ባሌን እንኳን አርበኞቹ በሚያደርሱበት አደጋ መጠቀም ስላልቻለ ተባሮ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ ቀለቡን እንኳን የሚያመጣው ከሀገሩና ቅኝ ከያዛቸው ሌሎች ሀገሮች ነበር፡፡ እንግዲህ ወራሪው ኃይል እንኳንና ቅኝ ሊገዛ ቀርቶ ወረራውን እንኳን እራሱ በብቃት መፈጸም ያልቻለበት በአርበኞች ተቀፍድዶ የተያዘበት ሁኔታ ነበር እንጅ የነበረው ጭራሽ ቅኝ ግዛት ሊባል በሚችል ደረጃ ምንም ነገር መፈጸም የቻለበት ሁኔታ አልነበረም፡፡

በእርግጥ ወራሪው ኃይል በቆይታው ጊዜ በርካታ ዘግናኝና አረመኔያዊ ግፎችን ፈጽሟል፣ ለደኅንነቱ በመሥጋት ለጸጥታ ጥበቃ ሲል ብቻም ሳይሆን ባለበት የዘር ጥላቻ ምክንያትም ጭምር ልክ በቅኝ ግዛት ስር እንደነበሩ ሕዝቦች ሁሉ ሐበሾች የገዛ ሀገራቸው ሆኖ ሳለ አምስቱንም ዓመት ወራሪው ኃይል ባለባቸውና በገነባቸው ከተሞች መግባት አይፈቀድላቸውም ነበረ፡፡ ከዚህ ውጭ ግን ፋሽስት ጣሊያን ቆይታውን ከወረራ ወደ ቅኝ ግዛት መለወጥ የቻለ ስላልነበረና እነኝህ ሁኔታዎች ሳይፈጸሙ “ቅኝ ግዛት ነው የነበረው” ብሎ ማለት ስለማይቻል ሀገራችን በፍጹም በፍጹም ተወራ ነበር እንጅ ቅኝ አልተገዛችም ነበረ፡፡

እናም ዓላማው ምን እንደሆነ በደንብ ግልጽ ባይሆንልኝም ሀገራችን ቅኝ ግዛት ተገዝታ እንደነበር በዘመቻ እያወሩ ያሉ ሰዎች ሲያጋጥሟቹህ እነኝህ ነጥቦችን ዓለማቀፋዊ መስፈርቶችን በማንሣት ሀገራችን በጭራሽ ቅኝ እንዳልተገዛች በማረጋገጥ እንድታሳፍሩ ማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡ ስለ የነጻነት በዓል ስንናገር ወይም ነጻ ስለመውጣታችን ስንናገር አያይዘን ነጻ የወጣነው ከወረራ መሆኑን መግለጽ አስፈላጊ ነው፡፡ እንዲህ ማድረጋችን ምንም ወይም ብዙ የማያውቁ ወገኖችን ከመሳሳት ወይም ከመደናገር እንታደጋለን፡፡

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ያልያዙ ኢትዮጵያውያን ሰልፈኞች መንግስት ጎረቤቶቻቸውን እና የአገሩን ቀደምት ነዋሪዎችን እንዲገድልላቸው ጠየቁ

 

”ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም” ይላል ደጉ ኢትዮጵያዊ። አሁን አሁን መጪውን የመከራ ዘመን ለመቀበል እራሳቸውን ያዘጋጁ፣መካሪ ሽማግሌ ያጡ እና ጥጋብ የሚሰሩትን ያሳጣቸው በእሳት ሲጫወቱ ማየት የተለመደ ሆኗል።
Humera
ከእዚህ በላይ የምትመለከቱት ፎቶ አፍቃሪ ሕወሃቱ ፋና ብሮድካስቲንግ በድረ ገፁ ላይ የሰቲት ሁመራ ነዋሪዎች የአካባቢው ቀደምት ነዋሪዎች አማራ ነን ትግሬ አይደለንም  በማለታቸው ብቻ ትግሪኛ ተናጋሪዎች ሰልፍ መውጣታቸውን ከዘገበበት ገፅ ላይ የተወሰደ ነው።
በፎቶው ላይ እንደምትመለከቱት የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የለም በሚባል ደረጃ ሁለት ወይንም ሶስት ብቻ ትመለከታላችሁ።የቀረው በሙሉ ከኢትዮጵያ ጡት ያደገ በማይመስል መልክ (ተገዶ መሆኑን የሚገልፁ አሉ) የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ተሽቀንጥሮ በህወሓት አርማ ሰቲት ሁመራ ላይ ተሰልፈዋል።
ዜናውን ፋና እንዳለው ብቻ ላቅርበው እና ሰልፈኞቹ መንግስትን ጎረቤቶቻችንን ይግደልልን ማለታቸውን አንብባችሁ ፍረዱ።በመጀመርያ ደረጃ በሰቲት ሁመራ፣በታች አርማጮ የአማራ ተወላጅ ነን ትግርኛ ብንናገርም ባህላችን፣ለቅሷችን፣ ሁሉ በአማራ ባህል ነው።በሚል በሰላማዊ እና በሰለጠነ መልክ ለመጠየቅ አዲስ አበባ ድረስ ተወካይ የላከው የሁመራ ሕዝብ ተወካዮቹ ታፈኑበት።እንግዲህ ይህንን በሰላማዊ መንገድ ለተጠየቀ ጥያቄ ነው ሰልፍ ተወጥቶ እንደ ፋና አገላለፅ ሰልፈኞቹ  እንዲህ ብለዋል ይለናል-
ህዝቡ እነዚህን አካላት እስካሁን በትዕግስት ጠብቋቸዋል ያሉት ነዋሪዎቹ፥ ከአሁን በኋላ ግን መንግስት አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ እንዲወስደባቸው ጠይቀዋል።’
በትዕግስት ጠበቃቸው የተባሉት ስለ ሁለት ነገር ነው ማለት ነው? አንዱ ቀድመው ነዋሪ ስለሆኑ ባህላችን ይጠበቅ በማለታቸው ሲሆን ሁለተኛው ይህንን መብታቸውን ደጋግመው በሰላማዊ መንገድ መጠየቃቸው ነው።
ለጥያቄው ምላሽ የሕወሃቱ የምስራቅ ትግራይ አስተዳዳሪ አቶ ኢሳያስ በምላሹ እንዲህ አሉ ይላል ፋና :- ”የህዝቡን ጥያቄ ለማክበርም በእነዚህ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንወስዳለን
በቀይ ሽብር ዘመን እርምጃ ወስደናል ማለት ገድለናል ማለቱ መሆኑን ማንም ያውቀዋል።በፋና ዘገባም ሕዝብ ”እርምጃ ይወሰድ” አለ ማለት ”ይገደሉልን” ማለቱ ሲሆን ”እርምጃ እንወስዳለን” አሉ ሲል ደግሞ ”እንገላለን” ማለት መሆኑ ነው።እነማንን ሲባል ጎረቤቶቻቸውን እና ቀደምት ነዋሪዎችን።ምክንያት ባህላችን ይከበር በግድ ከመሬታችን ተገፋን ስላሉ።
ይህ አይነቱ የለየለት መንግስታዊ ፋሺዝም በኢትዮጵያ ላይ ነቅሎ ሰላም ይመጣል ማለት ዘበት ነው።በኦሮምያ በመቶ የሚቆጠሩ በጥይት እረግፈው እና የአስር እና አስራሁለት ዓመት ወጣቶች አደባባይ ወጥተው ድምፅ አሰሙ ብሎ ጥይት በተርከፈከፈባቸው እና መድረክ አዲስ አበባ ላይ ሰልፍ ለመጥራት ጠይቆ በተከለከለ ማግስት  ሁመራ ላይ የሕወሃትን ሰንደቅ አላማ የያዙ ሰልፈኞች ጎረቤቶቻችንን ግዴልልን ብለው መንግስትን ጠየቁ መንግስትም እሺ እንገላለን አለ።የሚል ዜና የሚገኘው ፋና ድረ-ገፅ ላይ ብቻ ነው።ሰልፈኞችም ባይሰልፉ ቢቀር መልካም ነበር።ሽማግሌዎች (ሽማግሌ ካለ) ተሰብስበው ቢነጋገሩ እና መላ ቢዘይዱም ጥሩ ነበር።ነበር ለማለት ነው እንጂ ለህወሓት ከሁሉ በላይ የሆነ ስለመሰለው ፋሽሽታዊ ልብሱን በደንብ እያጠለቀ ነው።ለነገሩ ከቁንጮ እስከ እግር ድረስ በአንድ አካባቢ ሰው የምትመራ አገር በፋሽሽት መሪዎች እጅ  ብትወድቅ  አይገርምም።
ይህ ስርዓት ከትናንቱ ይልቅ መጪው ፋሽሽታዊ አላማው ከመቼውም ጊዜ በላይ አሁን በግልፅ ታይቷል።

ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com 
የካቲት 19/2008 ዓም

Amnesty International Report 2015/16 – Ethiopia

Members and leaders of opposition parties as well as protesters were extrajudicially executed. General elections took place in May against a backdrop of restrictions on civil society, the media and the political opposition, including excessive use of force against peaceful demonstrators, the disruption of opposition campaigns, and the harassment of election observers from the opposition. The police and the military conducted mass arrests of protesters, journalists and opposition party members as part of a crackdown on protests in the Oromia region.Amnesty International Report 2015/16 - Ethiopia

BACKGROUND

The ruling political party, the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front, won all the seats in the Federal and Regional Parliaments in the general election.

The opposition Semayawi Party reported that the National Election Board of Ethiopia (NEBE) refused to register over half of its proposed candidates for the House of Peoples’ Representatives: of 400 candidates, only 139 were able to stand for election. The opposition Medrek coalition reported that the NEBE only approved 270 of the 303 candidates it had proposed to register.

Famine due to rainfall shortages during the main harvesting season (June to September) affected more than 8 million people in the north and east.

ARBITRARY ARRESTS AND DETENTIONS

Police and security officers arrested Omot Agwa Okwoy, Ashinie Astin Titoyk and Jemal Oumar Hojele at Addis Ababa Bole International Airport on 15 March, on their way to a workshop in Nairobi, Kenya. The workshop was organized by the NGO Bread for All with the support of the NGOs Anywaa Survival Organisation and GRAIN. The police held the three men for 161 days without bail at the Maekelawi detention centre, beyond the four months allowed by the Anti-Terrorism Proclamation (ATP), under which they were charged on 7 September.

On 12 May, security officers arrested two campaigners and three supporters of the Semayawi Party who were putting up campaign posters in the capital, Addis Ababa. They were released on bail after four days in detention.

On 19 May, Bekele Gerba and other members of the Oromo Federalist Congress were campaigning in Oromia when police and local security officers beat, arrested and detained them for a couple of hours.

Over 500 members of Medrek were arrested at various polling stations in Oromia region on 24 and 25 May. Security officers beat and injured 46 people during the elections; six people sustained gunshot injuries and two were killed.

EXTRAJUDICIAL EXECUTIONS

Four members and leaders of opposition parties were killed after the election.

Samuel Aweke, founder of the Semayawi Party, was found dead on 15 June in the city of Debre Markos. A few days before his death he had published an article in his party’s newspaper, Negere Ethiopia, criticizing the behaviour of local authorities, police and other security officials. The Semayawi Party claimed that Samuel Aweke had received threats from security officials after the article was published.

On 16 June, Medrek member Taddesse Abreha was accosted on his way home in the Western Tigrai zone by three unknown people who attempted to strangle him. He died shortly after reaching his home.

Medrek member Berhanu Erbu was found dead on 19 June near a river in the Hadiya zone, 24 hours after he was taken from his home by two police officers.

Asrat Haile, election observer on behalf of Medrek in the Adio Kaka unit, Ginbo Woreda district and Kefa zone, died after being repeatedly beaten by police officials on 5 July.

None of these deaths except Samuel Aweke’s was investigated. The Semayawi Party said the trial, conviction and sentencing of Samuel Aweke’s killer were a “sham”, intended to protect the real culprit.

FREEDOM OF EXPRESSION

In the run-up to the general elections, the government continued to use the ATP to suppress freedom of expression through the continued detention of journalists and protracted trials: it arrested and charged at least 17 journalists under the ATP. Many also fled the country due to intimidation, harassment and politically motivated criminal charges.

Police arrested Habtamu Minale, editor-in-chief of Kedami newspaper and reporter for YeMiliyonoch Dimts newspaper, on 9 July at his house. He was released on 26 July without charge.

The Public Prosecutor dropped the charges against two members of the Zone 9 bloggers’ group. On 16 October, the High Court acquitted five of the Zone 9 bloggers of terrorism charges, after they had spent over 500 days in pre-trial detention.

On 22 October, the High Court convicted and sentenced in his absence Gizaw Taye, Manager of Dadimos Entertainment and Press, to 18 years’ imprisonment for terrorism.

FREEDOM OF ASSEMBLY

On 27 January, police used excessive force to disperse a peaceful demonstration in Addis Ababa that was organized by the Unity for Democracy and Justice opposition party. Police beat demonstrators with batons, sticks and iron rods on the head, face, hands and legs, injuring more than 20 of them.

On 22 April, the government called a rally on Meskel Square to condemn the killing in Libya of Ethiopian migrants by affiliates of the armed group Islamic State (IS). When some demonstrators shouted slogans during the rally, police used excessive force, including tear gas and beatings, to disperse the crowd, which escalated the situation to clashes between protesters and police. A journalist reported that 48 people had been injured and admitted to hospital, and that many others sustained minor injuries. Hundreds were reported to have been arrested. Woyneshet Molla, Daniel Tesfaye, Ermias Tsegaye and Betelehem Akalework were arrested on 22 April and charged with inciting violence during the rally. They were convicted and sentenced to two months in prison, and were kept in custody for more than 10 days after the completion of their prison term, although courts had ordered their release. The police released them on bail on 2 July.

እባካችሁን ከባንዲራው ታረቁ – ታምራት ነገራ

12376792_558136384350717_6634417347526598899_n

ለውድ ወያኔ ወንድሞቼ እና እህቶቼ

የእስከአሁኑ ጉዞአችሁ በየትኛውም አጋጣሚ ከኢትዮጵያ ብሔርተኞች የሚመጣውን ማንኛውንም ምክር በጥሞና እንደምትሰሙ አያሳይም፡፡ ምክር ስንሰጣችሁ ፤ ምክሩን ከሰማችሁም በኋላ ከምክሩ የሚጠቅመውን እና የሚጎዳውን ሃሳብ ለመለየት አንደምትጥሩ፤ ይጠቅማል እና ይጎዳል ብላችሁ የለያችሁትን ሃሳብም መልሳችሁ ከኢትዮጵያ ብሔርተኞቸ ጋር እንደምትወያይዩበት የሚያሳይ ምንም መረጃ የለም፡፡
ይልቁንም ያለው መረጃ የሚያሳየው ከቀን ወደቀን የኢትጵያ ብሔርተኞችን ድምጽ ከየትኛውም ድምጽ እንደምትጸየፉ ነው፡፡ የኢትዮጵያን መንበር ከተቆነጣጣችሁበት ቀን ጀምሮ እኛ የኢትዮጵያ ብሔርተኞች ስልጣን መያዛችሁ ካልቀረ ኢትዮጵያን እና ሆነ የአፍሪካ ቀንድን ከእናንተ ቀድመን እንደማቅናታችን፤ ያለንን ልምድ እና እውቀት ለማካፈል አልታከትንም፡፡
በእኛ እና በእናንት መካከል ያለው የፖለቲካ ልዩነት እኛ ለአገራችን ለባንዲራችን፤ ለሉአላዊነታችን፤ ለአንድነታችን እና ለዳርድንበራችን ክብር ካለብን ተጠያቂነት ስለማይበልጥብን ከእናንተ ጋር ያለንን ልዩነት ሁሉ ችላ ብለን አብረናችሁ ልንሰራ ፈቃደኛነታችን ሁሌም ከመግለጽ ተቆጥበን አናውቅም፡፡
ይህን ትናንት ያደረግነውም ሆነ ዛሬም የምናደርገው አሽከር መሆን ስለምንመርጥ፤ አንገታችንን አይደለም በኩራት በእብሪት ቀና አድርጎ የሚስኬድ አከርካሪ ስለሌለን አይደለም፡፡ ለኢትዮጵያ ሲሆን የምንሳሳው ምንም ነገር ስለሌለን እንደሆነ እናንተም ጠላቶቻችንም ያውቃሉ፡፡ የሚኒሊክን ክቡር እና ምርጥ መንበር ስትቆናጠጡ የሽንፈት ቁስላችን ደሙ ሳይደርቅ ነበር ከሱዳን ፤ ኤርትራ እና የተለያዩ ፀረ ኢትዮጵያ አገራት ጋር የያዛችሁት ግኑኝነት እንደማያዛልቅ ማስጠንቀቂያ የሰጠነው፡፡

አያያዛችሁ ኢትዮጵያን ለመሰለ በሺ ዓመታት የሚቆጠር የተገለፀ፤ የብሔራዊ ደሕንነት ፍላጎት፤ ጥቅም፤ እውቀት እና ልምድ ላላት አገር የማይመትን የማይጠቅም እና የማያዛልቅ እንደሆነ ከላይ ከታች የጮኅነው፡፡ በአዲስ መልክ ቆራርሳችሁ የቀረፃችሁት የኢትዮጵያ ዳር ድንበር ምንኛ ቢያሳዝነን የእናንተ ስልጣን እነደተጠበቀ፤ ከነሽንፈታችን ፤አንገታችን ደፍተን የእናንተን የበላይነት ሳንቀናነቅ፤ አዲሱን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለመጠበቅ እንድተፈቅዱልን ከማንም ቀድመን ወደ ምድብ ዘባችን እንድትመልሱን ማመልከቻ ያስገባነው እኛ እንደሆንን የተመዘገበ ማስረጃ በአደባባይ አለ፡፡
ከዚህ ይልቅ የሰጣችሁን መልስ እስርቤት እና መበታተን እና መባረር ነበር፡፡ አብሮ አደጋችሁ ሻቢያ ቀን ጠብቆ ጦርነት ሲያውጅ የተማመነው አንድ ነገር ነበር፡፡ እኛ ዳር ቆመን እንደምና፡፡ የተወረረው ትግራይ ነው እንጂ ኢትዮጵያ አይደለም ብለን ጥግ የምንቆም የመሰለውን ሁሉ በሚያሳፍር መልኩ ትዳራችን በትነን ለዳርድንበራችን እንደገና መጣን፡፡

ከውጊያው በኋላ ለኢትዮጵያ ብሔርተኞች ውለታ የሰጣችሁት ምላሽ ምን ያህል አሳፋሪ እንደነበር እንደገና ማንሳት አያስፈልግም፡፡ ጥሎብን ኢትዮጵያን የምንወዳት ለምትከፍለን ውለታ አይደለም፡፡ ተረግመን ይሁን ተባርከን ለዳርድንበር የምንሰለፈው የደሞዙን መጠን አይተን አይደለም፡፡ ለኢትዮጵያ ያለን ታማኝነት ከምን እነደሚመነጭ ፤ የአገር ነገር እንዲህ ለምን እንደሚያንዘረዝረን አይደለም ለእናንተ ለእኛ ለእራሳችን በቂ እና አሳማኝ ምክንያት የለንም፡፡
በዚህ አላበቃችሁም፡፡ ከዘውድ ዘመን ጀምሮ ከአገሪቷ ጥጋ ጥግ በቆላ ሆነ በደጋ ይሄ ነው የሚባል የጡረታ መብትም ሆነ ለልጅ እንኳን የማይወረስ ደሞዝ እየተሰጠው አገሩን ሲያገለገል የነበረውን አገር ወዳድ መምር ሆነ፤ መሃንዲስ፤ ሹፌር ሆነ ተራ የቢሮ ፀሀፊ አንድ በአንድ አፈናቀላችሁት፡፡ ሲቪል ሰርቪሱን አገሩን በሚወደው ሳይሆን በሆዳሙ እና በ መንደሬ ብሔርተኛው አጨቃችሁት፡፡
ለነገሩ ይሄ አሰራራችሁ የመነጨው ኢትዮጵያን ከአንድ አገርነት ወደ ትናንሽ ብሔሮች፤ ህዝብ፤ ጎበዞች፤ ጋጦች ምናምን ስብስብ ካዘቀጣት ህገመንግስት እንጂ በድንገት ከሰማይ አልወረደም፡፡ ኢትዮጵያን እንዲህ ከፋፍሎ ማስቀመጥ እና ዜጎችን እርስ በእርስ ማጣለት ለኢትዮጵያ ዘላቂነት እነደማይከጅል ከመጀመሪያው አሳሰብን፡፡ እሱ ባይታያችሁ ለገዛ ስልጣናችሁ ዘላቂነት እንደማያዋጣ መከርን፡፡ መልሳችሁ አሁንም ብስለት የታየበት ሳሆን አሳፋሪ ነበር፡፡
እናንተ አዲስ አበባ ስትገቡ ዳዴ ይሉ የነበሩ ልጆችን እናንተን የሚጠቅም መስሏችሁ በተገቢው የኢትዮጵያዊነት ሲቪክ ሃሳብ ሳሆን በትንንሽ መንደሬነት ኮትኩታችሁ አሳደጋችኋቸው፡፡ ይሄው የዘራችሁት ለምልሞ መጣ፡፡ በኮተኮታችሁት ጠባብነት ከምድር ከሰማይ የዘረፋችሁትን እንኳን በሰላም የማትበሉበት ቀን ከተፍ አለ፡፡
እኛ የኢትዮጵያ ብሔርተኞች አሁንም አገሪቷ ላይ የተጋረጠውን አደጋ እንደቀልድ አናየውም፡፡ አሁንም ከእናንተ ጋር ካለን ቅራኔ ይልቅ ለአገራችን ያለን ፍቅር እና ታማኝነት ሺ ቢሊዮን እጥፍ ይንተገተጋል፡፡ ይህ ትንታግ ኃይል ዛሬም በመቅጽፈት ኢትዮጵያን ከማንኛውም አደጋ ለመታደግ ዝግጁ ነው፡፡
ይህን አገልግሎታችን ለማቅረብ ስልጣናችሁን አንጠይቅም፡፡ ከእናንተ ጋርም ሆነ ለእናንተ ለማገልገል ከዘረፋችሁትም ሆነ ነገ ከምትዘርፉት 5 ሳንቲም አንጠይቅም፡፡ አገልግሎታችን ነፃ ነው ማለት ፍላጎት የለንም ማለት ግን አይደለም፡፡ ፍላጎታችን በአንድ ቃል ሊጠቃለል ይችላል፡፡ ከባንዲራው ጋር ታረቁ፡፡ በቃ!!

ከኢትዮጵያ ባንዲራ ጋር በያዛችሁት ውሸታም የባንዲራ ቀን መሰል ቀልድ ሳይሆ እውነተኛ ተሃድሶ መልክ ስትታረቁ የእኛን አካል ብቻ ሳይሆን ነብሳችን ታገኙታላችሁ፡፡ ከባንዲራው ጋር መታረቃችሁን በቲቪ አውጃችሁ ሳይሆን በተግባር መታየት ይጀምራል፡፡ ቢያንስ በእነዚህ በሚከተሉት ርእሰ ጉዳዮች ላይ ከእኛ ጋር በተገቢው መልኩ በይፋ መነጋገር እና መግባባት ትጀምራላችሁ፡፡

የዳር ድንበራችን ነገር

ከሱዳን እና ኤርትራ ጋር በዳር ደንበራችን ላይ የምታደርጉትን ሽንሸና አሁኑኑ ታቆማላችሁ፡፡ የሄደው ሄዷል የቀረውን እንዴት እናርግ የሚባልም ከሆነ የትኛውን ለዛሬ የትኛውን ለነገ እነደምናሳድር እንነጋገር፡፡

የብሔር ብሔረሰቦች ነገር
ብሔር ብሔረሰቦች በቋንቋቸው መናገራቸው፤ ተገቢ መጠን ያለው ቋንቋ የፌደራል ቋንቋ መሆኑ፤ ብሄሮች የፈለጉትን ልብስ መልበሳቸው፤ በፈለጋቸው ቀን እና ስፍራ መጨፈራቸው፤ ማጓራታቸው ፤ መዝለላቸው እናም ሌላም ሌላም ባህላቸው የሚያዛቸውን ነገር ማድረጋቸው ከፍቶን አያውቅም፡፡ የእናንተን ዘመን ልዩ የሚያደርገው አስራ ሁለት የማይሞሉትም ሆነ በአስር ሚሊዮን የሚቆጠሩት አገር የመሆን ምኞት ከነ መዋቅሩ፤ ባዲራው፤ ሰራዊቱ አስረክቦ ጥግ ቆሞ ማየቱ ላይ ነው፡፡
ይህን ውሸታም እና እርባና ትዕቢት በህገመንግስት ፤ በክልሎች አወቃቀር፤ በትምህርት ፖሊሲ፤ በበጀት ሁሉ አጅባችሁ ያሳደጋችሁት እናንተ እንጂ እኛ አይደለንም፡፡ አሁንም የምታሳዩት እርምጃ ለጥያቄው በተገቢው መንገድ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ መልሶችን መስጠት ሳይሆን እሳቱን የበለጠ በሚያፋፍም ጭፍን ግድያ ብቻ ነው፡፡

ከላይ ባቀረብናቸው ጉዳዮች ከእኛ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኞች ሁኑ እንጂ አገሪቷን በጦርነትም፤ በጭፍጨፋም፤ በንግድም ፤ በጋብቻም በጭንገረድም በገበያም በጠላም፤ በጠጅም ያቀናናት እና የሰፋናት እኛው ነን እና ማን ላይ የትጋር እንዴት ምን አይነት እርምጃ እንደምትወስዱ እንደ አባይ ከረዘመው ታሪካችን እናጫውታችኋለን፡፡
እነደገና ይህን ምክር ሌላው ቢቀር የዘረፋችሁትን በሰላም የምትበሉበት እና በመቀጠልም የምትዘርፉት አገር እንዲኖራችሁ ስትሉ እንኳን አድምጡት፡፡ ውድ የአገር ልጅ ጥልሽ እንዳለው

ሳቅ ፈገግታ ደስታ ሁሌ የምናየው፤ ሀገር በነፃነት ኮርታ ስትኖር ነው
ጥሩ ልብስ ለብሰን፤ አምሮብን ተውበን የምንታየው
ሰዎች እንረዳ ቢገባን ትርጉሙ ሁሉም ባገር ነው

እና አንደገና እላለሁ ከባንዲራው ታረቁ፡፡ ከባንዲራው ከታረቃችሁ ሌላው ሁሉ ተከታይ እና ዝርዝር ነው፡፡

አሜን!

ጭፍጨፋውን ለማስቆም ሆ ብሎ መነሳት ብቸኛው መፍትሄ ነው! (አርበኞች ግንቦት7)

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyየዛሬ 79 አመት ባህር አቋርጦ ድንበር ተሻግሮ የመጣው የጣሊያን ፋሽስት ሠራዊት በአዲስ አበባ ነዋሪ ወገኖቻችን ላይ ከፈጸመው ዘግናኝ የጭፍጨፋ እርምጃ የማይተናነስ እልቂት፣ ዛሬም በኦሮሞ ወገናችን ላይ በአገር በቀል የህወሃት አልሞ ተኳሽ የአጋዚ ጦር ሠራዊት እየተፈጸመ ይገኛል።

የካቲት 12 ቀን 1929፣ በሮዶልፎ ግራዚያኒ ትዕዛዝ የአዲስ አበባን ነዋሪ ሕዝብ በደም ጎርፍ ባጥለቀለቀው ዘግናኝ ጭፍጨፋ ህጻናት፣ ጎልማሶች ፣ ሽማግሌዎች፣ አሮጊቶች፤ ነፍሰጡሮች፣ ለጋ ወጣቶች፣ በአጭሩ ኢትዮጵያዊ የሆኑ ሁሉ ዘራቸው ፣ ሃይማኖታቸውና ጾታቸው ሳይለይ በጅምላ በመታረዳቸው፣ ደማቸው በስድስት ኪሎ አደባባይ እንደ ወራጅ ወንዝ መፍሰሱን፣ ታሪክ ጊዜ በማያደበዝዘው ብዕሩ መዝግቦት ይገኛል። የግራዚያኒ ጦር በወገኖቻችን ላይ ያንን አሰቃቂ እልቂት የፈጸመው ለነጻነታቸው ቀናይ የሆኑት ሞገስ አስግዶምና አብረሃ ደቦጭን የመሳሰሉ ጀግኖች ኢትዮጵያኖች፣ የጣሊያንን ቅኝ አገዛዝ በመቃወም በጠላት ላይ የፈጸሙትን ጥቃት ለመበቀልና በጠመንጃ ሃይል የአገሪቱን ህዝቦች በባርነት ቀንበር ሥር አውሎ ሃብትና ንብረት ለመዝረፍ በማለም ነበር።

ከጊዜ ወደ ጊዜ ግልጽ እየሆነ የመጣው በፋሽስት ጣሊያንና ለጠባብ የቡድንና የግል ጥቅም የመንግሥትን ሥልጣን የሙጥኝ ባለው ህወሃት መካከል ያለው ልዩነት አንዱ ባዕድ ወራሪ ሌላኛው አገር በቀል ከመሆን ያለፈ አይደለም። ጣሊያን የኢትዮጵያን ማዕከላዊ ሥልጣን የፈለገው ለአገሩ ኢንዱስትሪ የሚሆን ጥሬ የተፈጥሮ ሃብት ፍለጋ ሲሆን፣ ህወሃት ደግሞ የአገሪቱን ለም መሬት በርካሽ ዋጋ ለባዕድ በመቸብቸብ ጭምር ባለሥልጣናቱና የጥቅም ተጋሪዎቹ ሃብት እንዲያካብቱ ከማድረግ የዘለለ ራዕይ ኖሮት እንዳልሆነ በበርካታ ተግባሮቹ አስመስክሯል።

ወያኔ አጋዚ የሚባል ልዩ ጦር አሰልጥኖና አስታጥቆ ከህዝብ የሚነሳን ተቃውሞና እሮሮ ለመጨፍለቅ የሚወሰደው ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ፣ መነሻው ለዘረፋ መሣሪያ አድርጎ የሚጠቀምበትን በትረ ስልጣን ለመከላከል እንደሆነ በተደጋጋሚ ገልጿል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኦሮሚያ አካባቢ የተጀመረውን ህዝባዊ ተቃውሞ በሃይል ለመጨፍለቅ የህወሃት ልዩ ቅልብ ጦር በህዝባችን ላይ እየወሰደ ያለው ጭፍጨፋ የፋሺስት ግራዚያን ጦር አዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ህዝብ ላይ የዛሬ 79 አመት ከፈጸመው የሚለየው በሟቹች ቁጥር እና በገዳዮቹ ማንነት ብቻ ነው። የአጋዚን ጦር አሰልጥኖና አስታጥቆ በገዛ ወገኑ ላይ ፣ እንደባዕድ ሠራዊት፣ ጭካኔ የተሞላበት ጭፍጨፋ እንዲፈጽም ያሰማራው ህወሃትም ሆነ ከአለቆቹ የተሰጠውን ትዕዛዝ በፍጹም ታማኝነት ተቀብሎ በገዛ ወገኖቹ ላይ ታሪክ ይቅር የማይል ወንጀል በመፈጸም ላይ የሚገኘው ይህ ሠራዊት፣ ላለፉት 25 አመታት ያልአግባብ ያፈሰሰው ደምና የቀጠፈው ወገኖቻችን ህይወት ቁጥር ለመቁጠር እያዳገተ መጥቷል።

በተለያዩ ጊዜዎች በኦጋዴን፤ በጋምቤላ፤ በቤኔሻንጉል፤ በአፋር፤ በአማራና ደቡብ አካባቢዎች ከደረሰው የግድያ ፍጅት በተጨማሪ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኦሮሚያ አካባቢ የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ ለመደፍጠጥ የአጋዚ ጦር ከአለቆቹ በተሰጠው ትዕዛዝ የጨፈጨፋቸው ዜጎች ቁጥር ከ300 በላይ ደርሷል:: ቁጥሩ ከዚህ በእጥፍ የሚበልጥ ቁስለኛና ከ8 ሺህ በላይ እስረኞችም እንዳሉ ገለልተኛ የሆኑ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እየተናገሩ ነው። በአልሞ ተኳሾች ህይወታቸው ከተቀጠፉት መሃል ዕድሜያቸው ገና 8ና 9 አመት የልበለጣቸው ታዳጊዎች፤ አሮጊቶችና እርጉዝ ሴቶች ይገኛሉ። ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በአምቦ ከተማ በደረሰው ጥቃት የ9 አመት ታዳጊ ህጻንን ግንባር አነጣጥሮ የመታው የአጋዚ ጦር፣ ወንድሟን ከወደቀበት ለማንሳት ጎንበስ ያለቺውን እህቱን በሌላ ጥይት በመምታት ቤተሰቦቿንና የከተማውን ህዝብ የመረረ ሃዘን ውስጥ ጥሏል፤ ተመሳሳይ ግድያ በአሰላ ከተማ ውስጥ በምትኖር የ8 ዓመት ታዳጊ ላይም ተደግሟል።

በሴቶችና በህጻናት ላይ ጥይት የሚያስተኩስ የአውሬነት ባህሪ ከየትኛው ባህላችን የመጣ ነው? ይህንን አሰቃቂ ድርጊት የተመለከተ ወይም የሰማ ሰው እንዴት አድርጎ ነው ሠራዊቱንና አዛዦቹን ከአብራኩ የተገኘ የአገሩ ዜጋ አድርጎ ማሰብ የሚችለው? የዚህ አይነት አሰቃ ድርጊት ዛሬ የጀመረ ሳይሆን በድህረ ምርጫ 97 በአዲስ አበባና በሌሎችም የአገሪቱ ክፍሎች ውስጥም ተፈጽሟል። በመለስ ዜናዊ ትዕዛዝ በወቅቱ ከተማዋን ወሮ የነበረው የአጋዚ ጦር ያገኘውን ሁሉ በጥይትና በቆመጥ ሲያዋክብ፣ ሠይድ የተባለ የ10 አመት ልጅ የጨርቅ ኳሱን ከመሬት አንስቶ ለመሮጥ ሲንደረደር አናቱን በጥይት ተመቶ እስከወዲያኛው አሸልቦአል። በስተርጅናቸው ይጦሩኛል ብለው መርካቶ ውስጥ ሽንኩርት በመቸረቸር ሁለት ልጆቻቸውን ተቸግረው ያሳደጉ የእነ ፍቃዱ እናት በአጋዚ ጥይት ሁለቱንም በአንድ ጀንበር ተነጥቀዋል:: ምንም ጥፋት እንዳላጠፋ እየመሰከሩ ባላቸውን ከእስር ለመታደግ የሞከሩ የልጆች እናት ወ/ሮ እቴነሽ ሴት ልጆቻቸው ፊት በጥይት ተገድለው ቤተሰብ የተገደሉበትን ጥይት ዋጋ ከፍሎ አስከሬን አንዲወስድ ተደርጓል። የ14 አመቱ ነብዩ አለማየሁም ባንክ ልትዘርፍ ነበር ተብሎ በግፍ ተገድሏል። ያ እሮሮ ያ ጩኸት ወያኔ ሥልጣን ላይ እስካለ ብቻ ሳይሆን እስከ ወዲያኛውም ከህሊናችን አይጠፋም። ታሪክ ራሱን ይደግማል እንዲሉ የድህረ ምርጫ 97 አይነቱ ጭፍጨፋ አሁንም የኦሮሚያ ከተሞችንንና መንደሮችን እያዳረሰ ነው። “እናቴን ለምን ገደላችሁብኝ” ያለ ወጣት ደምቢዶሎ ውስጥ በጠራራ ጸሃይ ህዝብ ፊት ተረሽኗል፤ ምንም አይነት መሣሪያ ያልታጠቁ እናትና ልጅ በአንድ ቀን በአንድ ጀንበር በግፈኞች ጥይት ለህልፈት በቅተዋል፤ በደኖ ውስጥ ፍሮምሳ አብዲ የተባለ የ10 አመት ታዳጊና ወላጅ እናቱም እንዲሁ። ምስራቅ ሃራርጌ ውስጥ ደረታቸው ላይ በተተኮሰ ጥይት ህይወታቸውን ያጡት የ60 አመቷ አዛውንት አዴ ጁሃራ ሙሳንና የሌሎች ሰለባዎችን ፎቶግራፍ በማህበራዊ ድህረ ገጽ የተመለከትን ሁሉ ልባችን በሃዘን ተወግቶአል ፤ በቁጭትም በግኗል። በመቻራ፤ በነገሌ፤ በነቀምት፤ በኮፈሌ፤ በመንዲ፤ በሆሮ ጉዱሩ፡ በቦቆጂ፤ በአሰላ፤ በሮቤ፤ በጎባ፤ በመቱ ወዘተ በየቀኑ እየፈሰሰ ባለው ደም ምክንያት ተመሳሳይ ለቅሶ ተመሳሳይ ዋይታ የአገራችንን ምድር እያናወጠ ነው። ይህ አረሜኔያዊ ጭፍጨፋ የዕለት ተዕለት በሆነበት ሰሞን ባለፈው ሰኞ ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ የኦሮሚኛ ፕሮግራም ቃለመጠይቅ የሰጠው ጌታቸው ረዳ፡ በገዛ ወገኑ ላይ እንዲህ አይነት ዘግናኝ እርምጃ እየወሰደ ያለውን የአጋዚ ጦር “በመልካም ሥነምግባር የታነጸና ህዝባዊ ወገናዊነቱን ያረጋገጠ” በማለት ሲያሞካሸው ተሰምቷል። ከሶስት አራት ቀን ቆይታ ቦኋላ ደግሞ ሃይለማሪያም ደሳለኝ በኦሮሚያ ያለው እንቅስቃሴ “የመንግሥትን ሥልጣን በሃይል ለመንጠቅ የሚደረግ እንቅስቃሴ ስለሆነ የማያዳግም እርምጃ ይወሰዳል” ሲል በቴለቪዢን መስኮት ብቅ ብሎ ዝቷል። ታዳጊ ህጻናትንና እርጉዝ ሴቶችን ግንባር አልሞ የሚመታ ሃይል ከማሰማራትና ህዝብ ከማስጨፍጨፍ የበለጠ ምን አይነት የማይዳግም እርምጃ ለመውሰድ ህወሃት እንደተዘጋጀ ሃይለማሪያም ደሳለኝ እራሱ የሚያውቅ አይመስለንም። ህዝባዊ ተቃውሞ በሚካሄድባቸው ቦታዎች ታንክና መትሬየስ እየተተራመሰ እየተመለከትን የማያዳግም እርምጃ የሚሉን እንደ ባህሪ አባታቸው ፋሽስት ጣሊያን የመርዝ ጭስ ከአየር የሚለቅ አይሮፕላን ለማሰማራት ፈልገው ይሆን ? ወቅቱ ፈቀደም አልፈቀደ ወያኔ ሥልጣኑን ለመከላከል ይጠቅማል ብሎ እስካመነ ድረስ የማይወስደው የጭካኔ እርምጃ ይኖራል ብሎ ማሰብ ቢያዳግትም፣ እንደ ሁለተኛው የአለም ጦርነት የመርዝ ጭስ በመጠቀም ሥልጣን ላይ ተደላድሎ መቀመጥ እንደማይቻል የመረዳት አቅም ያለው ወያኔ ውስጥ አለ ብሎ መዘናጋት አያስፈልግም።

በህዝብና በአገር ሃብት ጠንካራ ሠራዊት ገንብቶ ህዝብ እየገደለ፤ እያፈናቀለና እያሰደደ እስከወዲያኛው ሥልጣን መቆጣጠር የቻለ መንግሥት በታሪክ አይታወቅም። የወያኔም መንግስት የመጀመሪያው ሊሆን አይችልም:: የግራዚያኒ ቁራጭ የዛሬው ጥቁር ፋሽስት ወያኔ እራሱን የተለየ ጠንካራ አድርጎ የሚቆጥረው የአለም አምባገነኖችን ታሪክ ብቻ ሳይሆን የአገራችንን የቀደምቶቹን አወዳደቅ ታሪክ እንኳ መለስ ብሎ ለመመልከት ባለመቻሉ ነው። በጠመንጃ ሃይል በአንድ ወቅት በአንድ ቦታ የሚነሳውን ወይም የተነሳውን ተቃውሞ ማዳከም ወይም መቆጣጠር ይቻል ይሆናል። አፍኖና ነጻነት ገፎ ሥልጣን ላይ ተደላድሎ ለረጅም ጊዜ መኖር ግን በፍጹም እንደማይቻል ወያኔ እራሱ ካካሄደው የጸረ ደርግ ትግል መማር ነበረበት:: ባለመማሩም የራሱን የወደፊት ዕጣ ከቀድሞው የዩጎዝላቪያ ፕሬዝደንት ስሎባዳን ሚሎሶቪችና የአይቬርኮስቱ ሎሬንት ባግቦ ተርታ እያሰለፈ ነው:: ሁለቱም በየአገራቸው ባደራጁትና በሚመሩት ሠራዊት ተማምነው በአገርና በህዝብ ላይ ለፈጸሙት ወንጀል በመጨረሻቸው አፍንጫቸውን ተሰንገው አለም አቀፍ ፍርድ ቤት ተወረውረዋል:: የአገር መከላኪያ ጦር ዋና አላማና ተግባር የአገርን አንድነትና ሉአላዊነት ከባዕድ ወረራ መከላከል ነው። ወያኔ እየገዛት ባለችው አገራችን ግን እየሆነ ያለው በሠላም አስከባሪነት ሥም ለወያኔ መሪዎችና የጦር ጀነራሎች በውጪ ምንዛሪ ገቢ የሚያስገኝ ድንበር ዘለል ግዳጅ ተግባር ላይ መሠማራት ወይም የገዛ ወገንን መግደልና ማሠር ሆኗል:: ይህ አካሄድ በአስቸኳይ መቆም አለበት:: የወያኔን የሥልጣን ዕድሜ ለማራዘም ሲባል የሚሰጠውን ትዕዛዝ ተቀብሎ ህዝብ መጨፍጨፍ፤ ማቁሰልና ማሰር የፍርድ ቀን ሲመጣ “ታዝዤ ነው” በሚል ከተጠያቂነት ነጻ የማያደርግ ወንጀል መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል:: አሁን በኦሮሚያ ውስጥ እየተካሄደ ባለው ተቃውሞ ህዝብ በመፍጀት ለወያኔ ግዳይ ጥሎ የመሸለም አባዜ የተጠናወታቸው አዛዦች ካሉ ቆም ብለው

ማሰብና ከድርጊታቸው መታቀብ ያለባቸውም ከታሪክና ከህግ ፍርድ እራሳቸውን ለማዳን ነው።

አርበኞች ግንቦት 7 በኦሮሚያ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ጭፍጨፋ ለማስቆም ሁላችንም ሆ ብለን መነሳት፤ አምርረን በመታገል ይህን እጅግ ጨካኝ ዘረኛ ስርአት በማስወገድ ወንጀለኞቹን ለህግ ማቅረብ መቻል ይኖርብናል ብሎ ያምናል:: አባቶቻችን በፋሽስት ጣሊያን ጦር የተሰነዘረብንን ወረራና ጥቃት ለማክሸፍ ሆ ብለው በህብረት እንደዘመቱት ሁሉ፣ ይህ የኛ ትውልድም አገራችንንና ህዝባችንን ለከፋ መከራ የዳረገውን የወያኔ አገዛዝ ከላያችን አሽቀንጥሮ ለመጣል በህብረት መነሳትና መዝመት ያለብን ግዜው አሁን ነው።

በወያኔ ከፋፍለህ ግዛው ፖሊሲ ምክንያት በፍርሃትና በጥርጣሬ መተያየታችን የአገዛዙን ጡንቻ አፈርጥሞታል። አንዱ ሲጠቃ ሌላው ዝም ማለቱን ከቀጠለ ሁላችንም በየተራ ተደቁሰን በባርነት ቀንበር ሥር ስንማቅቅ እንኖራለን። ይህ እንዳይሆን የፈለገ ሁሉ ዛሬውኑ በኦሮሚያ እየተቀጣጠለ ያለውን የነጻነት ትግል ይቀላቀል። ከአሁን ጀምሮ አንዱ ሲደማ የሌላው ከዳር ሆኖ ተመልካችነት ማብቃት ይኖርበታል። አርበኞች ግንቦት 7 የወያኔን ጭፍጨፋ ለማስቆምና አገራችን ውስጥ ሠላም ፍትህና እኩልነት እንዲሰፍን የሚያካሂደውን ትግል ከጫፍ እስከ ጫፍ ያለው ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዲቀላቀሉት የትግል ጥሪውን በድጋሚ አጠናክሮ ያቀርባል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!